Get Mystery Box with random crypto!

ሀላል ትዳር👫💍

የቴሌግራም ቻናል አርማ hayu_abdi — ሀላል ትዳር👫💍
የቴሌግራም ቻናል አርማ hayu_abdi — ሀላል ትዳር👫💍
የሰርጥ አድራሻ: @hayu_abdi
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 8.54K

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2022-08-17 12:57:20 እዉነተኛ ታሪክ
#Part

ለፊርዶስ ምን ልበላት እንደባለፈዉ በቤተሰብ የመጣ አለ ብዬ ልዋሻት እንዴ ??? ወይስ እዉነቱን ልንገራት እያልኩ ሁለት ልብ ሆንክ ብዙ ካሰብኩ ቡሀላ በመጨረሻም አንድ ዉሳኔ ወሰንኩ ነገ....ፊርዶስን ሳገኛት ጓደኛየ ናት ለኔም ለወንድሟም እያሰበች አንድ ከጎኔ ላለችዉ ፊርዶስ የኔን ማንነት ከመጀመሪያዉ እስከመጨረሻዉ ልነግራት ወሰንኩ፡፡
እንደምንመ ብሎ የወፎቸ ጫጫታ ንጋትን ሊያበስር ብቅ አለ ፡፡ እኔም ቁርሴን በልቼ እናቴ የምታቃቸዉ ሰዎች ስለሞቱ ለቅሶ ደርሼ ልምጣ ቤት ጠብቂኝ ብላ ከቤት ወጣች፡፡ እኔም ጊዜ መግደል አልፈለኩም እኔ ለዙበይር እንደማልሆነዉ እራሴን እነደረከሰ ሴት ስለምቆጥር በጊዜ እኔን እንዲረሳ እኔን እንዳያስታዉስ ለእህቱ ፊርዶስ ልነግራት ወሰንኩ፡፡
ስልኬን ማታ እንዳጠፋሁት ነበር ወዳዉ ስልኬን አብርቼ ለፊርዶስ ደወልኩ
....ፊርዶስም ሂኩ ዛሬ አዳሬን ስጨነቅ እንቅልፍ ሳይወስደኝ አደረ ትናንት ለሰራሁት ስራ አዉፍ በይኝ ዙበይር ጋር ለማገናኘት መጀመሪያ አንቺን ማስፈቀድ ነበረብኝ ብላ እንባ እየተናነቃት ጠየቀችኝ
......እኔም ፊርዱ አንቺ ምንም ጥፋት የለብሽም ስታጠፊ ነዉ አዉፍ የምልሽ ...አንድ ነገር ላማክርሽ ነዉ አሁን የደወልኩልሽ የማይሽ እንደእህቴ ነዉ ደስታየንም ሀዘኔንም ልትካፈይኝ በምነግርሽ ነገር ላትርቂኝ በሆዴ አፍኜ የያዝኩትን የሆድ እሳት የሆነብኝ ሚስጥር ልነግርሽ ወስኛለሁ እኔን ልታዳምጪኝ ልትረጂኝ ዝግጁ ነሽ አልኳት
......ፊርዶስም እንደመደንገጥ ብላ እሺ ዝግጁ ነኝ አለችኝ
......አሁን ከተመቸሽ እቤት መምጣት ትችያለሽ አልኳት
......እሷም እሺ ሂኩ አሁን መጣሁ አለችኝ፡፡

ፊርዶስም ጊዜ ሳትፈጅ በፍጥነት እኛ ቤት ከተወሰኑ ደቂቃዎች ቡሀላ መጣች፡፡ ስገባ ሂኩ አሰላሙ አለይኩም ትናንትና አንቺን ሳላስፈቅድ በሰራሁት ስራ አዉፍ በይኝ ጥፋተኛ ነኝ ይቅር በይኝ እያለች እኔን መለመን ጀመረቸ፡፡
...... ወላሂ ከአንቺ ምንም ጥፋት የለም በራሴ ችግር ነዉ እንደዚህ የሆንኩት ዛሬ ኢንሻ አላህ ትረጂኛለሽ ብየ አስባለሁ ....
ፊርዱ በማወራሽ ሚስጥር እኔ እና አላህ ነን የምናቀዉ አሁን አንቺን የዚህ ሚስጥር የምታቂዉ ከአላህ ከእኔ ቀጥሎ አንቺን ላማክርሽ ልነግርሽ ነዉ ግን ስነግርሽ ጠንካራ ልትሆኝ ይገባል እንደ አጋጣሚ እንባየ ቢፈስ አንቺም ማልቀስ የለብሽም አደራ አልኳት
ፊርዶስም በመደናገጥ እሺ አለችኝ
እኔም ከረጅም ዝማታ ቡሀላ በፊት ስለትምህርቴ ስለጉብዝናየ .. ስለtelegram profile አርጌ......ሀይደር የሚባል ተዋወቄ......አምኘዉ እስከ ደብረዘይት ያሳለፍነዉን በመንታ እንባ የታጀበ እያወረሆት እንባየ ልብሴን እስከሚያርሰዉ አንድ ባንድ ነገርኳት ቂርአትም የገባሁት በዚሁ ምክንያት እንደሆነ ሁሉንም እያለቀስኩ ለፊርዶስ ነገርኳት ፊርዶስም አብራኝ ታለቅስ ነበር፡፡
ባለፈዉ ሲሀም ዘመዴ ነዉ ያለችኝ ቁጥሬን የሰጠነዉ ቢክራ ነሽ ወይ ብሎ ሲጠይቀኝ ይሄ በሆዴ ያፈንኩት ሚስጥር ስላለኝ በመዋሸት በቤተሰቦቼ የመጣ ትዳር አለ ብየ መለስኩኝ ..አሁንም ይህን ሁላ የነገርኩሽ ያለምክንያት አይደለም እኔ ለወንድምሽ ለዙበይር የትዳር አጋር መሆን አልችልም የቆሸሸ ማንነት ነዉ ያለኝ ዙበይር ከአሁን ቡሀላ እኔን ይወደኝ እንደሆነ ከአሁን ቡሀላ ከኔ ተስፋ ይቁረጥ ፡፡
እኔ ማለት ይህን ነገር ደብቄ ቤተሰቦቼ ሲጨናነቁ አንዱ ከአንዱ ከአንዱ ሀገር ወደ ሌላ ሀገር በዚሁ የተነሳ ቁርአን ይቀራብሽ ተብየ ደሴ ከተማ ድረስ እንደሄድኩ ....እናቴ ስታለቅስ ስትዉል አጎቶቼን አስጨንቄ ነዉ የኖርኩት አላህ ይምረኝ ይሆን ?? ደግሞ በሀይደር ተናድጄ ከቅርብ ቀናት በፊት ሚስቱን በFace book አግኝቻት ልነግራት የእሱንም ሂወት ላበላሽበት ወስኜ ስልኳን እስከ መቀበል የደረሰ ተግባብተን ደዉየ ልነግራት ብየ ለወለደቻቸዉ ልጆች እና የወደፊት የእሷ ሂወት አሳዝኖኝ ተዉኩት ፡፡ ፊሮዶስ የኔ ወንጀል ብዙ ነዉ አላህ ይምረኝ ይሆን?? አላህ ይምረኝ ይሆን ??
አላህ ያለልኝን እጠብቃለሁ ግን እኔ ለዙበይር የምገባ ሴት አይደለሁም ለዙበይር ሌላ ፈልጊለት እኔ መፈቀር የሚገባኝ ሰዉ አይደለሁም እኔ ማለት ከአንዱ ወንጀል ወደ አንዱ ስረማመድ አሁን ድረስ እኔ በማንነቴ የማፍር..........ብየ ንግግሬን ለፊርዶስ አስረድቼ እምባየን እየጠረኩ ከፊርዶስ ጎን ተነሳሁ፡፡ ፊርዶስ አብራኝ ተነስታ

#part 17 ይቀጥላል
156 views09:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-17 12:57:20 እዉነተኛ ታሪክ

#Part 15
ስልኬን አዉጥቼ ልደዉል አልኩና የኢክራም ቁጥር አዉጥቼ ልነግራት ወስንኩ ግን ጨነቀኝ የኔ ሂወት አንዴ ተበላሽቷል ግን የሶስት ሰዉ ሒወት ላበላሽ እንደሆነ ተሰማኝ ሁለት ልጆቿ እና ኢክራም ..ደግሞ ወደ ፍች ከሄዱ ልጁቹ ካለቤተሰብ ፍቅር ተለያይተዉ ኢክራም ወደ ቤተሰቦቻ ትሄዳለች ሌላም ችግር ፈጠርኩ ማለት ነዉ ..የቤተሰቦች ቀዉስ ስልኬን ይዤ ይሄንን አሰብኩ ግን ሀይደር የሰራኝ ስራ መልሶ አእምሮየ ጋር ብልጭ ይልብኛል፡፡ ሁሉንም ነገር ለአላህ ሰጠሁኝ ስልኬን አቅፌ እንደ ወራጅ ወንዝ ማልቀስ ሆነ ያረቢ እርዳኝ ያረቢ እርዳኝ እያልኩ
........የኢክራምን ስልክ ከContact አጠፋሁ Facebook ላልጠቀም ከአሁን ቡሀላ የሀይደርን ሚስት ኢክራምን ላላወራ ብየ ለራሴ ቃል ገባሁ በአላህ ተወከልኩ እስከአሁንም የሰራሁትን ስራ አላህ ይማረኝ..በሀይደር ከነቤተሰቦቹ እሱን ልጎዳዉ ነበር ይቅርብኝ አላህ እሱንም ያስተካክለዉ እኔንም አላህ የተሻለ ይስጠኝ ብየ ዱአየን አርጌ ለመጨረሻ ጊዜ ከሀይደር ለመበቀል ያሰብኩት ሀሳብ ሰረዝኩኝ፡፡

Face book መጠቀም አቆምኩ ግን ሀይደር የሰራኝ ጉድ ለማን ሰዉ እንደምተነፍሰዉ አላቅም አዳሬን ብቻ ማልቀስ ሁኗል ስራየ ፡፡ ከዛ የማይነጋ የለም ነጋ......ወደ ቂርአት ሄድኩ ፊርዶስን አገኘሇት ዛሬ ሂደሽ እናትሽን አስተዋዉቂኝ ብላኝ ከቂርአት መልስ እናቴን አስተዋወኳት ፊርዶስ በረፍት ሰአቷ እኛ ቤት እየመጣች ቤተሰባዊ ጓደኛም ሆነች አላህ የሰጠኝ የዲን እህቴ ፊርዶስ.....እሁድ እንደምጋብዘኝ ነገረችኝ .......ወበሪ ሆቴል....ከአሱር ቡሀላ እንሄዳለን አለችኝ፡፡ እኔም እሺ ፊርዱ አልኳት፡፡ ቀናቶች በተቆጠሩ ቁጥር እሁድ ደረሰ ፊርዶስ አሱርን እኛ ቤት መጥታ አብረን ወበሪ ሆቴል ሔድን እዛ ስደርስ ያየሁትን ማመን አቃተኝ የፊርዶስ ወንድም ዙበይር ቀድሞን መጥቶ ቁጭ ብሎ እየጠበቀን ነዉ፡፡ እኔም ዙበይርን በፊርዶስ ስልክ አፎቶ ላይ አንዴ ስላየሁት እሱ እንደሆነ ጠረጠርኩ፡፡ ፊርዶስ ግን ዙበይርም ነዉ አይደለምም አላለችኝም...እሷ ሶስት ወንድሞች ስላሏት ሀይደርም ላይሆን ይችላል ብየ ጠረጠርኩ፡፡ የሚጠጣ ነገር አዘን አንዳንድ ወሬ እያነሳን ከተጨዋወትን ቡሀላ የሚበላ የሚጠጣ ከተጠቀምን ቡሀላ እኔን ሸኝተዉኝ ወደ የቤታችን ተመለስን

ግን ማን ይሆን እያልኩ ሳስብ ሳስብ ....ዙበይር ይሆን እያልኩ ብቻየን ባዶ ቤት ቁጭ ብየ ስከራከር ዳኛ ከሌለዉ ክርክር ዉስጥ ስልኬ ጮኸ ስልኬም ከክርክሩ ገላገለኝ...ስልኬን ሳየዉ የደወለችዉ ፊርዶስ ነበረች
,,...አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱሏሂ ወበረካትሁ አለች
......እኔም ወአለይኩም ሰላም ፊርዱ ደህና ነሽ
.......አልሀምዱሊላህ በሰላም እቤት ገባሽ አለችኝ
.....እኔም አዎ ገብቻለሁ ፊርዱ
ብዙ ተራ ወሬዎች ካወራን ቡሀላ

....ሂኩየ ቅድም አብሮኝ የመጣዉ ማን እነንደሆነ አዉቀሽዋል አለችኝ
.....እኔም መቼም አንቺ ከአጂ ነብይ ጋር እንደማትሄጅ አቃለሁ፡፡ ከሶስት ወንድሞችሽ አንዱ ይሆናል ፊርዱ አልኳት፡፡
.....አዎ አልተሳሳትሽም ዙበይር ነዉ ፡፡ በአካል አገናኚኝ እያለ ረበሸኝ ምን ላርግ ፊርዱ አንቺ ነሽ እኮ አይቴ(የወንድሜ ሚስት ለማለት ነዉ) ዙበይርም ወንድሜ ነዉ ፡፡ ዙበይር ናፈቀችኝ ናፈቀችኝ ሲለኝ ነዉ እስከዛሬ በሩቅ ነበር የሚያይሽ ዛሬ ፊት ለፊት እንዲያይሽ ያረኩት አለችኝ ፊርዱ
.....እሷ ባለችኝ ነገር ደርቄ ቀረሁ የምመልሰዉ አጣሁ መልሴ ዝም ሆነ ...

....ፊርዶስም ሄሎ ሄሎ ሄሎ ሂክማ ምነዉ ዝም አልሽ ...አረ በአላህ አጥፍቼ ከሆነ ይቅርታ እንደዚህ ይከፋሻል አላልኩም ሂክማ ..አረ አናግሪኝ አስጨነቅሽኝ .....ሂክማ አረ ሂክማ እያለች እሰማታለሁ ስልኩን አልዘጋሁትም ነበር፡፡

እኔ ምንም የምመልሰዉ መልስ የለም ብቻ እንባየ ቁልቁል ሲወርድ ይታወሰኛል

ፊርዱም ሄሎ ሄሎዉ ማለቷን አላቆመችም በድንጋጤ ..እኔም ስልኩን ዘጋሁት መልሳ ፊርዶ ደወለች እኔም አላነሳሁኝ.....ፊርዶስ በመደወል ትደጋግም ይዛለች.....እኔም በtext ነገ የማወራሽ ነገር አለ ብየ በmessgae ልኬ..ስልኬን አጠፋሁት፡፡ ለፊርዶስ ምን ልበላት እንደባለፈዉ በቤተሰብ የመጣ አለ ብየ ልዋሻት እንዴ ??? ወይስ እዉነቱን ልንገራት እያልኩ ሁለት ልብ ሆንክ ብዙ ካሰብኩ ቡሀላ በመጨረሻም አንድ ዉሳኔ ወሰንኩ ነገ....ፊርዶስን ሳገኛት

ለፊርዶስ በሆዷ ያፈነችዉን ሚስጥር ሂክማ ትነግራት ይሆን ??? ለሂክማ ነገረች ማለት ዙበይር ሊርቃት ይችላል እናንተ ምን ትላላችሁ ??
በቀጣዩ ክፍል እናየዋለን፡፡

#Part 16 ይቀጥላል
156 views09:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-17 12:57:20 እዉነተኛ ታሪክ
#Part

በጣም ተናደድኩ ሀይደር የራሱን ኑሮ እየኖረ የኔን ሂወት አበላሽቶ ጨለማ አድርጎ እኔ በሂወት እያለሁ መኖር አይችልም ብየ ወሰንኩኝ አንድ ሀሳብ መጣልኝ የእሱን ሂወት ማበላሻ ......ሀይደርን ለመበቀል በጣም ቀላል ዘዴ አገኘሁ
Face book ገብቼ የfb ጓደኞች እያየሁ ሚስቱን በprofile ስላየሆት የfb ጓደኛዉ እንደሆነች ብየ መፈለግ ጀመርኩኝ፡፡ ጓደኞችን ስመለከት ብዙዎቹ ጓደኞቼ ሴት ነበሩ ገረመኝ፡፡ Fb ላይ ከ3000 በላይ ጓደኞቼ ነበሩት በስንት ድካም ልፋት ቡሀላ አንድ ፎቶ አየሁ የእሱ እና የእሷ profie የሆነ፡፡ time line ገብቼ ስመለከት የእሷ የብቻ ፎቶም አለ ፡፡ ሲጋቡ የተነሱ ፎቶዉ ላይ መብሩክ በሉኝ ብላ ፅፋለች፡፡

ያሰብኩት ተሳካ አሁን frind አርጌ የእኔን ሂወት እንዳበላሸብኝ የእሱን ላበላሽበት ወሰንኩኝ፡፡ እኔ እያለቀስኩ እሱ ስቆ እንደማይኖር ወሰንኩኝ ...frind request ላኩላት ከአንድ ቀን ቡሀላ ተቀበለችኝ ...በጣም ደስ አለኝ ሀይደር የእኔ ሂወት አበላሽቶታል የእሱንም ሒወት አበላሸዋለሁ እያልኩ ብቻየን እየዛትኩ ነዉ፡፡ face book ላይ online ቀን ቀን አትጠፋም ነበር ፡፡ ነገሮችን ሁሉ ሳስበዉ እሱ ማታ ማታ በስልኩ ይጀናጀናል እሷም ቀን ላይ ብየ አሰብኩ በትዳር በመሀላቸዉ የሆነ ክፍተት እንዳለ ያስታዉቃል፡፡ እኔም እያወረሇት ነዉ በሂደት ተዋወቅን ግን ለክፉም ለደጉም ብየ ትክክለኛ ስሜን አልነገርኳትም ፡፡ ሚስቱ የአዲስ አበባ የመርካቶ ሰፈር ልጅ እንደሆነች ስሟም ኢክራም እንደምትባልና የባሏም ስም ሀይደር እንደሚባል እና የሁለት ልጆች እናት እንደሆነች ..... የባለሀብት ልጅ ሀይደርን በጣም እንደምወደዉና በፊት ሹፌር ነበር ተዋወቅን ተዋደን ተጋባን ....ከዛም አባቴ ሀይደርን ከሹፍርና ስራ አቁም ብሎት አሁን መርካቶ ሱቅ ከፈተልን ከዛም የቤት መኪናም ዶልፊን አባቴ ገዝቶ እንደሰጠዉ አጫወተችኝ፡፡

ኢክራም በጣም ግልፅ ልጅ ናት ሁለ ነገሯ ተመቸችኝ ፡፡
አንቺስ ብላ ጠየቀችኝ እኔ ቂርአት እየቀራሁ እንደሆነ ነገርኳት፡፡ ስለ ሀይደር ምንም አላነሳሁ፡፡ ግን በጣም ገረመኝ ወንድ ልጅ ሴትን ልጅ ለማጥመድ በእጁ አድርጎ የሚፈልገዉን ለመዉሰድ የማይፈነቅለዉ ድንጋይ የለም ዉሸታቸዉ ከባድ እንደሆነ ተረዳሁ ፡፡ ጥፋቱ የኔ ነዉ የነገረኝን ማመኔ ብቻ ወደ ጆሮየ የገባዉ ሁሉ እዉነት ይመስለኝ ነበር ሚስጥሩ እያደር ገባኝ ማታ ማታ ስደዉል አይመችም ስልክ ለማንሳት በtelegram እናወራለን የሚለኝ ሚስቱ ኢክራም ሲያወራ እንዳሰማዉ እንደሆነ ገባኝ፡፡
ግን ለምን አረ ለምን ኢክራም ወዳዉ ከሹፍርና ኑሮ ገላግላዉ በቤተሰቦቿ ጥረት ሱቅ ተከፍቶለት መኪና ተገዝቶለት እሷ ባለዉለታዉ ሁና በመኪናዉ ሴት ሲሸወድ እንደ እኔ ያለዉን የተዘነጋ በማዘናጋት እንደዚህ መሆኑ ለኢክራም አዘንኩ፡፡ ወይ ጎራ ሁን ወይ ጎራ ተጠጋ አይደል የሚባለዉ ሀይደር ጎራ ተጠግቶ ይሄዉ በኢክራም ጥረት እና በቤተሰቦቻ ሀብት ለሌላ ለሀራም አላማ እየተጠቀመበት በመሆኑ ያሳፍራል፡፡ ደግሞ ለኔ የዋሸኝ ዉሸት ፊቴ ላይ ድቅን አለብኝ፡፡ ምነዉ ሀይደር ዉሸታም ነዉ ብየ ንገሪያት ንገሪያት የሚል መንፈስ ከጀርባየ አለ፡፡ ሀይደር ዉሸታም ነዉ ብየ ፅፌዉ ልልከዉ ብየ ቆይ ለሁሉም ሰአት አለዉ አልኩና ባልሽን ትወጅዋለሽ ብየ ጠየኳት
....በጣም ሀይደር ሁለ ነገሬ ነዉ በጣም እወደዋለሁ ያለ እሱ መኖር አልችልም በስራም ጎበዝ ነዉ ዉይ ሲወደኝ እኮ ብላ ታወራኝ ይዛለች በfb
......ግን ስለ እሱ መጥፎ ነገር ብሰሚ..ትጠይዋለሽ አጠይዉም ብየ ጠየኳት

.....እሷም እንዴ ሀይደር መጥፎ ነገር የለዉም የሚሰራዉን የሆነዉን ሁሉን ይነግረኛል እኔን ሳያማክር ፈፅሞ አያቅም ፡፡ በህይወቴ እሱ ነዉ የመጀመሪያየ ወንድ በጣም ነዉ የምወደዉ፡፡ ምንም መጥፎ አይሰራም እተማመንበታለሁ አለችኝ፡፡

...እኔም አይ ግን ሰርቶ ብታገኝዉስ አልኳት
.......ጭራሽ አያረገዉም ጥያቄዉ መልስ የለዉም ሁሌም ቢሆን በሀይደር የምተማመንበት ጨዋ ልጅ ነዉ፡፡አላህ በስንት ዱአ መሰለሽ የሰጠኝ አለችኝ፡፡

በጣም ደስ የምትል ሚስት አለችዉ ግልፅ ናት እኔም ማንነቴን ደብቄ እናወራ ይዘናል ከመግባባት ብዛት ስልክ ቁጥሯን ተቀበልኳት፡፡ ስልክ ቁጥሯም0911....2372 ብላ በfb text አረገችልኝ ፡፡ እቤቴ ሁኜ ማሰብ ጀመርኩኝ ሀይደር የእኔን ሂወት እንዳበላሸ ላበላሽበት ወይስ እኔን አላህ ይክሰኛል ቶብቻለሁ ለሚስቱ እና ለሁለት ልጆቹ ሒወት ብየ ልተወዉ እያልኩ ተወዛገብኩ፡፡ ያሳለፍኳቸዉ የደብረዘይት ጊዚያቶች እና አሁን ትዳር ሲመጣ የምጨነቃቸዉ ጭንቀቶች ፊቴ ላይ ድቅን ይላሉ፡፡
ይህን ጉዳይ ለፊርዶስ አላማከርኳትም ...ፊርዶስ ብሰማ ምን ትለኝ ይሆን ?
ስልኬን አንስቼ ቀጥታ ለኢክራም ልደዉል ቁጥሯን አዉጥቼ የሀይደርን ጉድ ልነግራት ወሰንኩ፡፡ ሀይደር እኔን እንደሸወደ ሚስቱን ሲሸዉድ አይኖርም ...ስልኬን አንስቼ ወደ ሀይደር ሚስት ኢክራም ልደዉል save ያረኩትን አወጣሁ....ከዛም

#part ይቀጥላል
154 views09:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-17 12:57:20 እዉነተኛ ታሪክ

#Part

ግን ለእሱ አንድ ዉሸት ዋሸሁት አላህ ይቅር ይበለኝ ሲደዉልልኝ ምን ወሰንሽ ብሎ ጠየቀኝ እኔም...በዉሸት ወንድሜዋ ቀጥታ እናቴን ጠይቂያት አይህንም እኛ ያዘጋጀነዉ አባትሽ የመረጠልሽ ልጅ አለ አለችኝ ወንድም አላህ ከኔ የተሻለ ይስጥህ ከአሁን ቡሀላ መደዋወል እና በtelegram አናወራም ለምን ብትለኝ የወደፊት የትዳር አጋሬ መሆን ስለማንችል ከቤተሰቦቼ ትእዛዝ ዉጭ መፈፀም አልፈልግም አልኩት፡፡

እሱ ጋር በዚሁ ተለያየን ክፉም ከአፌ ሳይወጣ እሱም ክፉ ሳይናገረኝ ወደድኩህ ወደድኩሽ የለአንቺ መኖር አልችልም ያለ አንተ መኖር አልችልም ሳንባባል በሀላል መንገድ ጀመርን፡፡ በሰላም ተለያየን አላህ ከእኔ የተሻለ የትዳር አጋር ይስጠዉ፡፡
........ምን ላርግ የጠየቀኝ ጥያቄ ላይ ድንግል አይደለሁም ብለዉ አላህ ወንጀሉን ነዉሩን የሸፈነ እኔ እሸፍንነታለሁ ብሏል እኔ ቶብቻለሁ በወንጀሌ ተፀፅቻለሁ ግን የእሱን ሂወት ዋሽቼ ገብቼ ማበላሸት አልፈለኩም፡፡ እኔ ሀይደር ሸወደኝና ማንኛዉንም ወንድ በክፉ አላይም፡፡ ለምን አባቴ ወንድ ልጅ ነዉ፡፡ ወንዶች ገደል ይግቡ ካልኩ እኔን ለማሳደግ ለመንከባከብ ከቤተሰብ ፍቅር ዉጭ ሁኖ የሚኖረዉ አባቴን ተሳደብኩ ማለት ነዉ ፡፡ ይህ ደግሞ የወላጆቼን ሀቅ አልተወጣሁም ማለት ነዉ፡፡ ስለሆነም ጥሩ ወንዶች አሉ በተዘዋዋሪም ጥሩ ያልሆነ ወንዶች አሉ እነሱንም ከመሳደብ አላህ ልቦና ይስጣቸዉ ግን ይህ ጭካኔ በእህቱ በእናቱ ቢሆን የማይወደዉን በሌላ ሴት ልጅ መጨዋት ግን ያሳፍራል፡፡
በየሳምንት ከጁምአ ሶላት ቡሀላ የደአዋ ዝግጅት አለ ሴቶች አሚራችን ፊርዶስ ደአዋ ታረግልን ነበር፡፡ እንደ አጋጣሚ እሷ አሟት ሳትመጣ ቀረች....
ከዛም አንቺ አድርጊ እያሉ አስገደዱኝ ደአዋ አደረኩኝ፡፡ በጣም የሚያምር ደአዋ አደረኩ የደአዋዉ ርዕስ በወንድ ተኩላዎች እንዳትሸወጅ ነበር፡፡ እኔም የተሰማኝን በደአዋዉ እያለቀስኩኝ ሀይደር የሰራኝ ስራ የሸወደኝ ትዝ እያለኝ እልክ በያዘኝ መልኩ ደአዋ አረኩላቸዉ ...የትምህርቱ ጠቃሚነት ብዙዎቹ አብረዉኝ ያለቅሱ ነበር፡፡ ደአዋዉን ሳረግ ለእህቶቼ ቢጠነቀቁ ብየ በኔ ሂወት የደረሰዉን ጠባሳ በተለያዩ ዘዴዎች የደአዋ ሲስተም ነገርኳቸዉ እንዲጠነቀቁ እና የtelegram group ጥቅም እና ጉዳቱን ዘርዝሬ ነገርኳቸዉ ከዛ ደአዋየን ጨርሼ ተቀመኩኝ፡፡

ከዛ ቡሀላ አሚራችን ፊርዶስ አንቺ አድርጊ ባለፈዉ ሳልመጣ ቀርቼ ያደረግሽዉ ደአዋ በጣም እንደሚያምር ነግረዉኛል ....እንደዚህ የደአዋ ብቃት አለሽ ማለት ነዉ ማሻ አላህ ብያለሁ አለችኝ ፊርዶስ ፡፡
እኔም እምቢ አንቺ ስለቀረሽ ነዉ ያረኩት አላረግም ብላት እንዴ አላማችን አንቺ አንቺ ልንባባል ሳይሆን ያወቅነዉን ለማሳወቅ ነዉ ሂኩ ፡፡ እኔ ማረግ በምፈልግ ሰአት አረጋለሁ አንቺ አድርጊ አለችኝ...ፊርዶስ አበረታታችኝ ጁምአ ከሶላት ቡሀላ ተሰብስበን ደአዋ አድራጊዉ እኔ ሆንኩ ...

አላህ የሰራሁትን ወንጀል እንዲምረኝ በምሰግድ ሰአት ብቻየን ስሆን ረከአተይን ከሰገድኩ ቡሀላ አላህንም ማረኝ እያልኩ ባገኘሁት አጋጣሚ እያለቀስኩ ነዉ....
ፊርዶስ አንድ ነገር አማክርሻለሁ ብላ ደወለችልኝ ከአሱር ቡሀላ ልንገናኝ ተቀጣጠርን፡፡
ከአሱር ቡሀላ ከፊርዶስ ጋር ተገናኝተን አንድ ያልጠበኩትን ነገር ነገረችኝ፡፡ ሂክማ ባለፈዉ የነገርሽኝ ነገር ሲሀም ለትዳር የሚፈልግሽ አለ ብላ እንደነገረችሽ እኔ ሳልነግርሽ አረፈድኩና ግን ዛሬ ልነግርሽ ወስኛለሁ፡፡ ወንድሜ አብረን ስንሄድ አይቶናል አንቺ ጓደኛየ እንደሆንሽ ያቃል ለትዳር እንደሚፈልገኝ ነገረችኝ ፡፡ ሂኩ ወንድሜ ዲን አለዉ አላህን ፈሪ አንቺን ከጓደኝነት አልፎ ለወንድሜ ዙበይር ብታገቢዉ ደስ ይለኛል ሂኩ ማስተዳደሪያም አልሀምዱሊላህ አላህ እርዚቅ ሰጥቶታል .... አንቺን እንዲያገባሽ እፈልጋለሁ አለችኝ፡፡ ባለፈዉ የሲሀም ዘመድ ይፈልገኛል ብለሽ ስታማክሪኝ ደነገጥኩ ወንድሜ ዙበይር እሷን ማግባት እፈልጋለሁ እያለ እኔም ወንድሜን እንድታገቢ እየተመኘሁ ያንን ወሬ ስሰማ ለዙበይር ነግሬዉ እንዴት እስከ አሁን ሳነግሪያት ብሎ ተቆጣኝ አለችኝ፡፡
.....እኔም ደነገጥኩኝ እስኪ ቆይ ልሰብበት አልኳት ከዛም
እቤቴ ሂጄ አሰብኩበት ለሚመጣዉ አመት ትምህርት የመማር እቅድ ነበረኝ..... እናቴም ብዙም ትምህርቴን እንድማር አትፈልግም...አባትሽ ተምሮ ለስራ የሚኖረዉ ደብረዘይት, ነዉ፡፡ የእኔን ፍቅር የልጁን ፍቅር ሳይሰጥ ይሄዉ እየኖረ ነዉ፡፡ መማር እንደዚህ ከሆነ ይቅር ትለኝ ነበር፡፡
መኝታ ክፍል ሁኜ ዙበይርስ ቢክራ ነሽ ወይ ብሎ ቢጠይቀኝ መልሴ ምንድን ነዉ ??? እያልኩ እያሰብኩ ነዉ፡፡

በጣም ተናደድኩ ሳላስበዉ ሸይጧን ወሰወሰኝ ሀይደር የራሱን ኑሮ እየኖረ የኔን ሂወት አበላሽቶ ጨለማ አድርጎ እኔ በሂወት እያለሁመኖር አይችልም ብየ ወሰንኩኝ ፡፡ በዙ ሀይደርን የምጎዳበት ነገሮች መኝታ ክፍሌ ሁኜ የቤታችንን ኮርኒስ እያየሁ አንድ ሀሳብ መጣልኝ የእሱን ሂወት ማበላሻ ቀላል ዘዴ አገኘሁ ...እኛን የቸገረን ኸይር መስራቱ እንጂ ተንኮል መስራቱ መቼ ያቅተናል ......ሀይደርን ለመበቀል በጣም ቀላል ዘዴ አገኘሁ እስከአሁን ትዝ ሳይለኝ ብየ ተቆጨሁ፡፡ ...የሀይደርን .....

#Part ይቀጥላል
151 views09:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-17 12:57:19 እዉነተኛ ታሪክ

#Part

አጎቴ እቤት መጥቶ አንድ መፍትሄ አለኝ ሲል ሰማሁት ለምን አታገባም ሲል መኝታ ክፍል ሁኜ ሰማሁት ....... እኔ እኮ ተማሪ ናት እያልኩ ነዉ እጂ ብዙ ሰሞች ጓደኞቼ ለራሱ ለምን አትድረንም አግብቻት እኔ ጋር ሁና አስተምራታለሁ ያሉኝ አሉ፡፡ ግን እኔ ትምህርቷን ትጨርስ ለእናንተም ማዉራት አይሆንም ትላላችሁ ብየ ዝምታን መርጬ ነዉ ብሎ ለእናቴ ሲናገር ሰማሁት ...

እናቴም እኔንም ብዙ ሰዉ ጠይቆኛል ግን ትምህርቷን ትጨርስ ብየ ነዉ፡፡ እሷም አስራሁለተኛ ክፍል ተፈትና ዉጤትም ቢመጣለት ዩኒቨርስቲ አትገባም ተነጋግረን እሺ ብላኝ ነበር፡፡ አላህ ያለዉ ሆነ እንጂ ይሄዉ ልጄ በሽታዋ ሳይታወቅ ታማለች አሁን ዱአየ አላህ እንዲያሽራት ነዉ፡፡ ጤናዋን ካገኘች ቡሃላ ስለ ሂክማ ትዳር አስብበታለሁ ብላ እናቴ እንባ እየተናነቃት ለወንድሟ ነገረችዉ ፡፡ እኔ እነሱ የሚያወሩትን ወሬ ስሰማ እዛዉ መኝታ ክፍሌ አለቀስኩ ለምን ለትዳር ብቁ አይደለሁም...ሀይደር አዋቂ መስሎ ሸዉዶኛል የወደፊት የትዳር አጋሬ ቢክራ ነሽ ወይ ብሎ ቢጠይቀኝ ምን መልስ አለኝ????
ወደ ትምህርት እንዳልመለስ ከወር በላይ አለፈኝ ካቋረጥኩ ፡፡ አንድ የትምህርት ቤት ጓደኛየ እቤት መጥታ ትምህርቱን ዘንድሮ የማቀጥይ ከሆነ ለምን ጃክሮስ ሰፈር አካባቢ ጃክሮስ መስጊድ አለ እዛዉ አካባቢ ሴቶች ተሰባስበዉ ኪታብ የሚቀሩ አሉ እነሱ ጋር ኪታብ አቀሪም ብላ አመላከተችኝ፡፡
ከዛም ቅዳሜ ቀን ወስዳ የሚቀሩበትን ቦታ እና አልፎ አልፎም መስጊድ እንደሚቀራ ነገረችኝ፡፡
እዛ ኪታብ መቅራት ጀመርኩ እንደገና ወደ ዲኔ ለመመለስ ወሰንኩኝ ፡፡
ኪታብ እየቀራሁ አላህን ማረኝ እያልኩ እያለቀስኩኝ ነዉ፡፡ ....የጀመአዉ አሚራችን ፊርዶስ ትባላለች እሷ ጋር በጣም ተግባባን ፊርዶስ ጃክሮስ ሰፈር አለፍ ብሎ ያለዉ ጎሮ የሚባለዉ ሰፈር ነዋሪ እንደሆነች ነገረችኝ፡፡
ፊርዶስ ኪታብም ታቀራን ነበር አሚራችን ናት ፡፡ እኔ ጋር ኢስላም መጀመሪያዉኑ ወንድምህን ዉደድ እና እህትሽንም ተዋደዱ ኢስላም አስተሳስሯችሇል ብሎናል፡፡
ከትምህርት ጓደኞቼ በላይ ፊርዶስን እንደእህቴ ቀረብኳት ለምን እኔ እህት ስለለኝ ፊርዶስን እንደ እህቴ ነዉ የማያት ፊርዶስ ሶስት ትልቅ ወንድሞች አሏት ፡፡ ሁለቱ አግብተዋል አንዱ ወንድሟ ግን አላገባም ፡፡
እዛዉ ኪታብ በመቅራት የተዋወቀነው ሲሀም የምትባል ልጅ አለች ሁሌ ኪታብ ቀርተን በተገናኘን ቁጥር ሂክማ የአንችን ቁጥር ስጭኝ እያለ እያስቸገረኝ ነዉ ዘመዳችን ነዉ አብረን ኪታብ እንደምንቀራ አይቶናል ቁጥሯን ስጭኝ እኔ አላማየ ቀጥታ ወደ ትዳር ብቻ ነዉ እያለ እያስቸገኝ ነዉ ሂክማ እኔ ይተዉሻል ብየ ዝም ብለዉ አኔን መቸካቸኩን አላቆመም ያለአንቺ ፍቃድ ደግሞ ቁጥርሽን መስጠት ከበደኝ እስከ ጠዋት አስበሽ ንገሪኝ አለቸኝ፡፡

ጠዋት ደረሰ ኪታብ የምቀራበት ሄድኩኝ ሲሀምን አገኘሇት ምን አሰብሽ እሱ አይቶሻል በስልክ አላስቀምጠኝ አለ፡፡ ምን ይሻለኛል ወይ ስልክሽን ፍቀጅልኝ እና ልስጠዉ እናንተ አዉሩ አለችኝ፡፡
እሺ ትንሽ ቆይቼ አሳዉቅሻለሁ ሲሀም አልኳት፡፡
ፊርዶስ ኪታብ ስጨርስ ለብቻዋ አማከርኳት፡፡ ፊርዶስም አይታወቅም የአላህ ነገር ለኸይር ይሆናል የሀራም መንገድ ሳጀምሩ ስለማንነቱ አጣርተሽ በስልክ በTelegram ሳይረብሽ ቀጥታ ወደ ሀላሉ ሊገባ ከቻለ አላህ የፃፈልሽ እሱ ጋር ሊሆን ስለሚችል ለሲሀም ቁጥርሽን እንድሰጠዉ ፍቀጅላት አለችኝ ፡፡
ፊርዶስም በመቀጠል እኔም እኮ በጣም ዲነኛ የሆነ ልጅ በቤተሰብ የመጣ በጣም ጥሩ ስነምግባር ያለዉ ነዉ አይቸዉ ፈትኘዋለሁ ቤተሰቦቼ ጥሩ ባል መርጠዉልኛል እኔም የማመቻቸዉ ነገር ስላለ ነዉ እንጂ ማግባቴ አይቀርም ...ግን አንቺ ቀድመሽኝ ካገባሽ በጣም ደስተኛ ነኝ ሂኩ አላህ ያሳካዉ ዱአ አትርሺኝ እኔም አረሳሽም አለችኝ እየተሳሳቅን፡፡

ወደ ሲሀም ሂጄ እሺ ቁጥሬን ስጭዉ አልኳት፡፡ እሷም ሰጠችዉ ...ደወለልኝ በስነ ስርአት አወራኝ ....በአካል እንደሚያቀኝ ነገረኝ እኔ ግነ አላቅህም አልኩት፡፡ ከአስር ቀን በላይ ሆነን ማዉራት ከጀመርን፡፡ የግድ መገናኘት ስላለብን ተቀጣጥረን ተገናኘን ተያየን ማሻ አላህ ቆንጆ ልጅ ነዉ ፡፡
ስሙን ከተዋወቅን ቡሀላ እኔ አንቺን ለማጀዘብ ሳይሆን ለትዳር ነዉ የምፈልግሽ አለኝ ፡፡
እያወራን የፈራሁት ጥያቄ መጣብኝ ሂክማ ያዉ ለወደፊት የትዳር አጋሬ መርጬሻለሁ አንድ ጥያቄ ልጠይቅሽ ግን ቢክራ ነሽ አለኝ???
......ምን ብየ ልመልስ ዝም አልኩት,,,,ወንዶች ማግባት የምፈልጉት በቃ እንደዚህ ነዉ አልኩት፡፡ እሱም የሌላዉን አላቅም ግን እኔ በአላህ እምልልሻለሁ እስከ አሁን ተጠብቄ አላማየም ማግባት የምፈልገዉ እንደ እኔዉ የሆነችዉን ነዉ አለኝ፡፡
እኔም እሺ በስልክ አሳዉቅሀለሁ ብየ ተለያየን፡፡

ሀይደር የኔን ሂወት አበላሽቶብኛል አለቀስኩ ድንግል ነኝ ብየ ባገባዉ ድንግልናየን ሳያገኝብኝ ቢቀር መፋታቴ ወይም ሲሰድበኝ ሲያንቋሽሸኝ ወይም የእሱ ሞራሉ እንደተጎዳ ይኖራል፡፡የሴት ልጅ ህይወት ግድ እስከ ክብሯ መገኘቱ ወሳኝ እንደሆነ ተገነዘብኩኝ ፡...ገና ከመጀመሪያዉ የትዳር ፈተና ጀመረኝ፡፡ ስለሆነም ብቻየን መኝታ ክፍሌ አሰብኩኝ ባስበዉ ባስበዉ ምንም መፍትሄ ላገኝ አልቻልኩም ያረቢ ብየ አለቀስኩ ፡፡ ግን ለእሱ አንድ ዉሸት ዋሸሁት አላህ ይቅር ይበለኝ ሲደዉልልኝ ምን ወሰንሽ ብሎ ጠየቀኝ
እኔም............

#Part ይቀጥላል
146 views09:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-17 12:57:19 እዉነተኛ ታሪክ

#Part

Face book ላይ profile pic ሳይ ደነገጥኩኝ
የምናገረዉ ጠፋብኝ እክፍል ዉስጥ ወድቂያለሁኝ
......ሀኪም ቤት እራሴን ስቼ ማን እንደወሰደኝ እንኳ የማቀዉ ነገር የለም ......የወደፊት ባሌ ብየ የሴትነት ክብሬን የወሰደዉ ሀይደር ባለ ትዳር ነዉ፡፡

...,..,fb profile እና time line ብዙ ፎቶዉች አሉ ለሰርጋቸዉ ጊዜ አብረዉ የተነሱት ....ምን ልበል ያዉ የምናገረዉ የለኝም ብቻ በማለቀዉ ድንጋጤ እራሴን ስቼ ሀኪም ቤት ገብቻለሁ፡፡
..... የተኛሁበትም ሆስፒታል እኛ ሰፈር ገርጂ አቅራቢያ የሚገኘዉ ኮርያ ሆስፒታል ነዉ፡፡ ሆስፒታል ሁኜ ልረጋጋ አልቻልኩም፡፡ አባቴም ሸዋሮቢት ሀገር የመንግት ሰራተኛ አይደል መታመሜን ሲሰማ ጊዜ ሳይፈጅ መጣ ፡፡ አልናገር ምግብ ለራሱ ብዙም አልበላም ግልኮስ ተተክሎልኛል፡፡ ብቻ በሁለቱም ጉንጬ እንባየ ሲረግፍ ነዉ የሚዉለዉ፡፡ እናቴም በእኔ ሁኔታ ተደናግጣለች የምትዉለዉ የምታድረዉ እኔዉ ጋር ነዉ...እኔ እያለቀስኩ የእናት ሆድ አያስችል አብራ ታለቅስ ነበር፡፡
....እኔስ መናገር ያልቻልኩት የዋጥኩት እሳት ነዉ የሚያስለቅሰኝ.....እናቴ ግን ልጇ ስለሆንኩ መናገር ስለማልችል ሳለቅስ ብቻ ታለቅሳለች፡፡
........ኮርያ ሆስፒታል አምስት ቀን ተኝቼ ህክምና ወስጄ ወደ ቤቴ ተመስኩ፡፡ ግን ምን እንደሆንኩ አላቅም አፌ እንደበፊቱ አቀላጥፎ ማዉራት አልቻለም ፡፡ ምን ሁነሽ ነዉ ምንሽን ይሰማሻል ይሉኛል... እኔ የሆንኩት ሌላ መልስ የሌለዉ ጥያቄ ነዉ፡፡
......አባቴም የያዛት ጅን ነዉ ተብሎ የሰፈራችን ጀመአዎች አሉ፡፡ ማታ ላይ ሳልሰማ መጥተዉ እስከ 4 ሰአት ቁርአን ቀሩብኝ፡፡ እነሱ የሆንኩትን አያቁም ...ቁርአን ቀርተዉ ምንም የጅን ምልክት ስላላገኙ ....አንዱ ቁርአን ከሚቀሩት አረ ይሄ ጅን አይደለም እናቁም ብለዉ አቁመዉ ሄዱ፡፡
...,.ግን ጅንም ባይሆን ለኔ ቁርአን መቀራቱ ትንሽ ለዉጥ አመጣሁ ማዉራት ትንሽ እየከፈተልኝ ነዉ፡፡

አባቴ አላስቻለዉም እኛ ሰፈር ያለዉ ኢብኑ አባስ መስጊድ ዉስጥ ታዋቂ የጂን የሚቀሩት ልጆች አሉ ተብሎ ተነገረዉ፡፡ ማታ ላይ ከመቅሪብ ቡሀላ እቤት ይዟቸዉ መጣ ፡፡ እኔ ሁሉን በሆዴ ይዠዋለሁ ፡፡ መናገር የማልችለዉ ነገር ነዉ፡፡ ከኢብኑ አባስ መስጊድ የመጡ ጀመአዎች ማታ ላይ ሲቀሩብኝ አመሹ ለዉጥ የለም ያዉ ነዉ፡፡

ግን ቁርአን በተቀራብኝ ቁጥር ልቤ በጭንቀት በሀሳብ አልተረጋጋም ብቻ ግን የተያያዘዉ አፌ እየተፍታታ ነዉ፡፡
እናቴ ደግሞ ሰፈሩ አሉ የሚባሉት ትላልቅ ሴቶችን ጠርታ ቅዳሜ ቀን በግ ታርዶ ምሳቸዉን አብልታ ከምሳ ሰአት የጀመሩ እስከ መቅሪብ ድረስ ዱአ ሲደረግልኝ ዋለ፡፡ ከእኔ በላይ ቤተሰቦቼን አስቸገሪኩ፡፡

ቤተሰቦችን አስጨነኳቸዉ ለነገሩ አንድ ፍሬ ልጅ ነኝ ምን ያርጉ አባቴም የመንግስት ስራዉን ከሸዋሮቢት አስፈቅዶ መጥቷል፡፡ እናቴም ጭንቀቷ እኔ ሁኛለሁ ስታየኝ በስስት ሳለቅስ የምታለቅሰዉ ከእኔ በላይ ነዉ፡፡ እኔ ተረብሼ ቤተሰቦቼን እረበሽኩኝ በእኔ መቀያር እነሱ ተረበሹ በጣም አዘንኩ፡፡

አላህ የዉመል ቂያማ ሲጠይቀኝ መልሴ ምን ይሆን የወላጆቻችሁ ሀቅ አደራ
እያለ በቁርአን ነግሮኝ ነብዩ ሙሀመድ ሰ ዐ ወ ጀነት ከእናት እግር ስር ናት ብለዉን ....እኔ ግን ገና ሀይደር ያገባኛል ብየ አምኘዉ እሱ ጋር ወንጀል ሰርቼ ለዛዉም ባለትዳር ሆኖ በራሴ ባለመጠንቀቅ በተጎዳሁ በራሴዉ ጥፋት ቤተሰቦቼን አሰቃይ ይዣለሁ፡፡ አላህ በስንቱ ነዉ የሚቀጣኝ አንድ ዚና በመስራቴ ሁለት ወላጆቼን እነሱ በማያቁት ነገር ማስጨነቄ ማስቸገሬ.... ኡፍ እንኳን እንዳትሉ የተባልኩትን ወላጆች በእኔ መረበሽ ማልቀስ ከጀመሩ አንድ ወር ሆናቸዉ ፡፡ ብቻየን እያሰብኩ መኝታ ክፍሌ ገብቼ አለቅሳለሁ፡፡
አንድ የእናቴ ወንድም አለ ደሴ ከተማ የሚኖር ደሴ ትምጣ እዚህ ጥሩ የጂን የሚቀሩ ቁርአን ቀሪዎች አሉ ብሎ ይደዉልላታል፡፡ እናቴም ምንም ይሁን ምንም እኔ አንድ ፍሬ ልጇ ሳለቅስ ስጨነቅ ማየት አልፈለገችም ፡፡ እኔም ሁሉን በሆዴ ደብቄ እነሱ የሚሉኝን እሺ ከማለት ዉጭ ምንም አማራጭ የለኝም፡፡ እናቴ ጋር አብረን ከ አዲስ አበባ 401 ኪሎ ሜትር ወደ ምትገኘዉ የወሎእምብርት ደሴ ከተማ ጉዟችንን ቀጠልን፡፡ ጠዋት ተነስተን 8:30 ደሴ ከተማ ገባን፡፡ አጎቴ ተቀብሎን አረፍ አለን፡፡ ጠዋት ላይ ደሴ ከተማ የሚገኘዉ ተቋም አካባቢ የሚገኘዉ ጦለሀ መስጊድ በብዙ ጀመአ በተሰበሰበበት ቁርአን ቀሩልኝ ከአዲስ አበባ ለየት ያለ አቀራር ነበር፡፡ ግን አብረዉ የሚቀራባቸዉ ጅን የያዛቸዉ ነበሩ የእነሱ ብዙም ሳይቆይ ለቀቀ እኔ ግን ሁሌን በሄዴ ይዤ ቤተሰቦቼን ዘመዶቼን እያስቸጠረኩ እያሴጨነከ ነዉ፡፡ በመነገታዉ ማታ ላይ ደግሞ ደሴ ከተማ የሚገኘዉ አሬራ አካባቢ አሬራ መስጊድ ከመቅሪብ ቡሀላ ቁርአን ተቀራልኝ ፡፡ ሁለት ቀን ከተቀራብኝ ቡሀላ አጎቴ ደሴን አሶገበኝኝ አዝናናኝ ፡፡ ደሴ ከተማን አንድ ሳምንት ቆይቼ ወደ አዲስ አበባ ተመለስኩኝ፡፡

አዲስ አበባም እንደተመለስኩኝ ጓደኛቼ የክፍል ተማሪዎችም እየመጡ ይጠይቁኝ አጫዉተዉኝ ይሄዱ ነበር፡፡
ትምህርት ካቆምኩ አንድ ወር ሆነኝ
......አዲስ አበባ የሚኖረዉ አጎቴ አልፎ አልፎ እየመጣ ይጠይቀኝ ነበር ፡፡
ዛሬ ግን እቤት መጥቶ አንድ መፍትሄ አለኝ ሲል ሰማሁት ለምን አታገባም እኔ እኮ ዳረኝ ብለዉ የጠየቁኝ አሉ ሲል መኝታ ክፍል ሁኜ ሰማሁት...እኔም ደነገጥኩኝ....

#part ይቀጥላል
147 views09:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-17 12:57:19 እዉነተኛ ታሪክ
#Part

እንደምንም ብሎ የሰኞ የሀሳብ ለሊት አልቆ ማክሰኞን ተካ ወደ የምማርበት ቦሌ Priparatoty ጓደኜቼ ጋር ትምህርት ቤት ተገናኘን ደብረዘይት የሰራሁት ወንጀል ያዩኝ ያዩኝ ይመስል ፈራሆቸዉ እንደዚህ ወንጀል መስራት ያሳፍራል ማለት ነዉ፡፡ ሂክማ ትናንት የቀረሽዉ በሰላም ነዉ እያሉ በጥያቄ አፋጠጡኝ ..ጓደኞቼም አይፈረድባቸዉም ከትምህርት ቀርቼ አላቅም ስቀር ተደናግጠዉ ነዉ፡፡
........እኔም አዎ እቤት ስራ ይዤ ነዉ ብየ ሌላ ዉሸት ዋሸሁ፡፡ ዉሸትን ለመደበቅ ግድ ሌላ ዉሸት አይደል የምንሰጠዉ ከጓደኞቼን ሰላም ተባብለን ወደ ክላሳችን ገባን፡፡ መምሆሮቹም እንደ ጓደኞቼ ጠየቁኝ በሰላም እደቀረሁ ነገርኳቸዉ፡፡ ክላስ ሁኜ በሰራሁት ስራ በቃ እየገረመኝ የሆነ የማላቀዉ ነገር የወረረኝ ይመስለኛል፡፡ በጓደኝቼ በመምህሮቼ ተወዳጅ እንደ ሂክማ ሁኑ የምባለዉ ልጅ ከአሁን ቡሀላ አይደለሁም እፍረትም ተሰማኝ፡፡ ከትምህርት ስወጣ ደወልኩለት አንስቶ ትንሽ አዉርተን ወደ ቤቴ ተመለስኩኝ፡፡
ግን እቤቴ ከገባብ ቡሃላ ማታ ተኝቼ ከየት መጣ የማይባል ፍርሀት ወረረኝ ምን ሆኘ ነው ምን ነካኝ ብየ ራሴን ጠየኩ መልስ ባላገኝም
.........ከዚህ በኃላ የኔ ህይወት በሀይደር እጅ እደሆነ ገባኝ አሁንስ ቢተወኝ አልፈልግሽም ቢለኝ ብየ ሳስብ የምሆነውን አጣሁ ይህ ሀሣብ ውስጤ ላይ የፈጠረው ፍርሀት ይሁን ቁጭት ባላውቅም ጩሂ ጩሂ አለን ግን ደግሞ ለመጮህም ምክንያት ያሥፈልጋል ፡፡
ጠዋት ወደ ትምህርት እየሄድኩ ስደዉልለት ስልክ አያነሳም ነበር፡፡ ምን ሆነ እያልኩ አሰብኩኝ እሱም ከትምህርት ስንለቀቅ ደወለልኝ ሂኩ አሁን ለማዉራት የማይመች ቦታ ነኝ መልሼ እደዉላለሁ አለኝ ፡፡ እኔም እሺ ብየ የደስደስ ነገር ተሰማኝ፡፡ ግን አልደወለም፡፡ በመነገታዉም ትምህርት ቤትም ቢሆን ስልኬን ደብቄ ይዤ ነዉ የዋልኩት ግን ሙሉቀን አልደወለልኝም ለምን ይሆን ???

የውስጥ ህመም ሆነብኝ በፊት በእረፍት ሰአት እና ከትምህርት ስንለቀቅ አስቦ የሚደዉልልኝ ሀይደር ይህን ሁለት ሶስት ቀን ግን አልደወለም፡፡ እቤቴ ገባሁ telegram ላይ ስገባ on line ነበረ፡፡ አላህ ይወቅ telegram on line መግባቴን አይቶ እንደሆነ አላቅም ወዳዉ ደወለ ፡፡
......እኔም አነሳሁት ሂኩ በጣም ይቅርታ ስራ ላይ ቢዚ ሁኜ ነበር ያልደወልኩት አሁንም ለማዉራት አይመችም ታቂያለሽ እቤት ቤተሰቦቼ ሶላሉ ማታ ማታ ስልክ እንደማላወራ አለኝ፡፡ እራት በላሽ ብዙ ነገሮችን አዉርቶኝ..... ደግሞ እንዳትረሽ አወድሻለሁ አለኝ እኔም እወድሀለሁ ብየ ሥልኩን ዘጋሁ
.....እወድሻለሁ ስላለኝ ደስ አለኝ

ግን ቀናቶች በሂዱ ቁጥር እንደበፊቱ ሁሌ መደወል ቀዘቀዘብኝ telegram ስገባ አላገኘዉም ፡፡ አንድ ቀን በሂወታችን በጀመርን ቁጥር ይህ ቀን ለመሞታችን እየቀረብን ነዉ፡፡ እኔ ከዛሬ ነገ ይስተካከላል ሁሉም ነገር ቦታ ይይዛል ስል ሀይደር እየራቀኝ ስልክም መደወል እያቆመ መጣ በጣም ግራ ተጋባሁ፡፡ደግሞ ለኔ መርዶ የሆነ profile pictur አየሁት ለጊዜዉ በዚህ acount ስለማልጠቀም በዚህኛዉ ነዉ የምታገኙን ብሎ profie አርጎታል፡፡ በጣም ግራ ገባኝ ሌላወን ቁጥሩን አላቀዉም፡፡ ...

በጣም ከምነግራችሁ በላይ ተጨነኩኝ ተወዛገብኩኝ፡፡
......በመጥፋቱ ብናደድም ቢያንገበግበኝም ግን ስራ ስላልተመቻቸለት ነው ይደውላል እወድሻለሁ ብሎኛል እያልኩ ራሴን ለማሳመን ከራሴጋር ሙግት ገጠምኩ ያለፈውን የፍቅር ወሬ በህሊናየ እያዎጠነጠንኩ እፅናናለሁ በtelegram ያወራናቸዉን message እያየሁ እገረማለሁ መልሼ እንደ መፅሀፍ ከላይ ጀምሬ ማታ ማታ አነባቸዋለሁ፡፡በዚህ መልኩ ቀን ቀንን እየተካ 20 ቀን ሆነን በዚህ ቀናት ውሥጥ ሶስት ቀን ብቻ ደውሎልኛል በፊት በቀን ሁለቴ ሶስት ጊዜ ይደውል ነበር እኔ ስጋት ውስጥ ነኝልቤ ለሁለት ተከፍሏል፡፡
...... በአንድ በኩል ቢተወኝ ምንድነው ምሆነው እላለሁ መልሽ ደግሞ ቃል ገብቶልኛል ሙስሊም ነው ለዛዉም አላህን ፈሪ ነዉ ፡፡እንደዚህ አያደርግም እላለሁ ሀሳቤ ተበታትኗል፡፡
አሁን መደወል አቆመ ግራ ገባኝ አላስችለኝ አለ፡፡ ስደዉልለት ስልክ አያነሳም .......
........በሌላ ሰዉ ስደዉልበት ያነሳዉና...የእኔ ድምፅ መሆኑን ሲያዉቅ ይዘገዋል፡፡ በጣም ተጨነኩ ግን ይተወኛል ብየየየየየየየየየየ አስቤ አላቅም ፡፡ ሀይደር ምን ሆነብኝ ሀይደር ምን ሆነብኝ ሀይደር ምንሆነብኝ ሁኗል አሳቤ ፡፡ ስልክ እየቀያየርኩ መደወል አልተዉኩም፡፡ የእኔ ድምፅ መሆኑን ካወቀ አንስቶ ይዘገዋል፡፡ telegram የሚጠቀምበትንም ቁጥር ቀይሯል በምን ላግኘዉ ፡፡ ተጨነኩኝ ወይኔ
ሂክማ የምሆነውን አጣሁ በሀሣብ ታመምኩ

ክላስ ቁጭ ብየ የሂሳብ መምህራችን ታሞ አልመጣም ነበር ...እስኪ ሀይደርን facebook ላይ ልፈልገዉ ብየ... በስሙ ፈለኩት ላገኘው አልቻልኩም ፡፡ ግን እሱ ለራሱ ያወጣም ስም አለ ነግሮኝ ነበር በስሜ ከምጠሪኝ ሱደይስ ብለሽ ጥሪኝ የመጀመሪያ ልጄ ስም ሱደይስ ነዉ የምንለዉ ይለኝ ነበር ስሙንም እወደዋለሁ በእሱ ጥሪኝ ይለኝ ነበር ፡፡ ትዝ አለኝ.. ከዛ fb ላይ ሱደይስ እና የአባቱን ስም አንድ ላይ ፅፌ search አረኩት ፡፡ ብዙ ሱደይስ ቢኖሩም የአላህ ነገር የfb....profile pictur ፎቶ ነበር ይገርማል ፎቶ profile ማረግ ወንጀሉ ለሴቱ ብቻ ነዉ እያልኩ ተገራረምኩ እኔን ፎቶ አታርጊ ብሎ የመከረኝ ሀይደር እሱ ፎቶ አርጎ አገኘሁት ..አሁን ይሄን የማስብበት ጊዜ አይደለም ብቻ እሱን fb ላይ ማግኘቴ በጣም ደስ አለኝ በface book እናወራለን አልኩኝ ብቻየን አወራለሁ የዋህ ነኝ እኮ፡፡

face book ላይ time line እና profile pictur ማየት ጀመርኩ፡፡ profile pictur ሳይ ያየሁትን ማየት አቃተኝ ድርቅ ብየ ቀረሁ፡፡ ልቤ ምቱን ያቆመ መሰለኝ እንባየ ይፈሳል አፌ ቃል ማውጣት ተሳነኝ ከጎኔ ያሉት የክፍሌ ልጆች ሂክማ ማን ሆንሽ ሂክማ ምን ሆንሽ ሲሉኝ እሰማለሁ፡፡ ዉሀ እምጡ እያሉ ተማሪዉ ሲጮህም እሰማለሁ ትንሽ ትንሽ ..ከዛ ቡሀላ ግን ምንም የማስታዉሰዉ ነገር የለም..... ወደ ሀኪም ቤት ሄድኩኝ.....ሲወስዱኝ ለራሱ አላስታዉስም ....ብቻ ማታ 4 ሰአት ነዉ የነቃሁት ስባንን እኔን ያገኘሁት ኮሪያ ሆስፒታል ነበር እራሴን ስቼ ተኝቼ ከጎኔ እናቴ እና የክፍል ጓደኛቼ ሶስት ልጆች አሉ፡፡

ሂክማ ምን ሁና ነዉ እራሷን የሳተችዉ ...ምን አይታ ነዉ በfb time line ላይ የሀይደር profile pic ሀኪም ቤት እስከምትገባ ድረስ የሚለዉን ?????
በቀጣዩ ክፍል እናየዋለን፡፡
145 views09:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-17 12:57:19 እዉነተኛ ታሪክ

#Part

ደብረ ዘይት ደረስን በመኪና እየዞርን አየናት ከዛ ሰአቱም አሱር ደረሰ ሶላታችንን ሰገድን .... ደብረዘይት የሚገኘዉ ባቡጋያ ሪዞርት ወደ እዛ ሄድን፡፡
ባቡጋያ ሪዞርት ደረስን አንድ ላይ ሁነን ሰልፊ ፎቶ ተነሳን በቃ ሁለታችንም ተቅበጠበጥን እየሄድን መሳሳም ፎቶ መነሳት ሆነ .....ከዛም ሂኩ ይህን ሁለት ቀን በጣም ደስተኛ ነኝ አንቺስ አለኝ እኔም አዎ ብየ መለስኩለት...........
........ተቃቀፍን ሳመኝ.....ነይ የማሳይሽ ነገር አለኝ ብሎ ወደ ባቡጋያ ሪዞርት የሚገኘዉ መኝታ ክፍል ይዞኝ ገባ፡፡
ሀይደር ነገሮቹን አመቻችቶ ጨርሷል ፡፡ እመኝታ ክፍል ኬክ አዘጋጅቶ በሁለታችንም ስም የተፃፈበት ኬክ አብረን ቆረስን ......በኬኩ እየተጎራረስን በቃ መደባደብ ጀመርን ኬኩን ሲቀባኝ እኔም ስቀባዉ የሌለ መነካካት ...ምን ልበላችሁ ሰዉ ከሚሰራዉ ነገር ወጣ ያለ ነገር እየሰራን ነዉ...እሱም ልብሱን አወለቀ ...በመቀጠልም የእኔን ልብስ አወለቀዉ፡፡ እምቢ የምልበት ድፍረቱ የለኝም.......
፡.......ሁለተኛዉ የሀራም የስሜቴን እርካታ ሰኞ ከአሱር ቡሀላ እስከ መቅሪብ ድረስ ለወደፊቱ ባሌ ይሆነኛል ብየ የአሰብኩት ሀይደር ጋር በ ባቡጋያ ሪዞርት መኝታ ክፍል.....በሚያስጠላ እንስሳዊ በሆነ ስሜት ትንቅንቅ አደረግን ፡፡ መቅሪብ ላይ ይበቃናል ....እናቴ ምንም የማስፈቅድበት ምክንያት የለኝም ጊዜዉ መሸ ትናንት ስላደረኩ ዛሬ ማደር አልችልም እንዳትቆጣ ወደ አዲስ አበባ እንመለስ አልኩት.......
......እሱም እሺ አለኝ...እቅፉ ዉስጥ እንዳለሁ ..
ሂኩ ምን እንደናፈቀኝ እንደ ቸኮልኩ ታቂያለሽ አለኝ
.......እኔም አረ አላቅም አልኩት
..........እሱም እናትሽ ጋር እስከ መተዋወቅ በጣም ቸኩያለሁ አለኝ
....እኔም ወላሂ በል አልኩት
.........እሱም ወላሂ አለኝ፡፡ አመንኩት በጣም ከስከዛሬዉ በበለጠ መልኩ ወደድኩት......ግን እሱ ጋር ሀራም መስራቴ የአላህን ትእዛዝ መጣሴ ምንም አልመሰለኝም.......
ከመኝታችን ተነስተን ባቡጋያ ሪዞርት ወጥተን
ወደ አዲስ አበባ እየተመለስን ነዉ.....
አዲስ አበባ ደረሰን እቤቴ ገርጂ ድረስ ሸኘኝ ከንፈር ለከንፈር ተሳስመን ተለያየን....እቤቴ እናቴን እንዴት ዋልሽ ብየ ገብቼ የደስታ ስሜት እየተሰማኝ አልጋየ ጋር ጋደም ብየ ስለ ሀይደር ማሰብ ጀመርኩ፡፡ በጣም ወድጀዋለሁ ለእሱ የሴትነት ክብሬን ማስረከቤ እንደ ክብር እንጂ ወንጀል መስሎ አልታየኝም......የሰጠኝን የጣት ቀለበት እያየሁ ደስተኛ ሁኛለሁ፡፡

በቃ እወድሀለሁ
——————
ለምን አትበለኝ ምክኒያት የለኝም፣
ፍቅር ስሜት እንጂ ሰበብ አይመስለኝም፣
ብቻ እወድሀለሁ መዉደዴም ጥልቅ ነዉ፣
ፍቅርህ ለእኔነቴ የልቤ ዙፋን ነዉ፣
ህያዉ የምሆነዉ አንተን በማፍቀር ነዉ፣
ሀቁ ቃል ይሄ ነዉ ሰርክ አዲስ የማምነዉ፣
ቂልነት አይደለም ሁሌ አንተን ማለቴ፣
ሞኝነት አይሆንም ለፍቅርህ መክሳቴ፣
ጅልነት አይደለም እራሴን መስጠቴ፣
በቃ አንተን መዉደድ ነዉ ደስታ መደሰቴ፣
ዉለታን ፈልጌ ዉደደኝ አላልኩም፣
ፍቅር ሰጠሁ እንጂ ምላሽ አልፈለኩም፣
እንዴት ለምን ካልከኝ እኔም አላወኩም፣
በቃ እወድሀለሁ ማለቴን አልተዉኩም፣
አዎ እወድሀለሁ፣
አዎ አፈቅርሀለሁ፣
ፍቅርቅር አድርጌህ በፌሽታ እኖራለሁ፣
ዉድድ አድርጌህ አንተን እፎይታ አገኛለሁ፣
ዉዴን እየወደድኩ ሀሴት አደርጋለሁ፣
በፍቅርህ ዉቅያኖስ ስዋኝ እኖራለሁ፣
አንተ ካለህልኝ ለምን እፈራለሁ
ባላገኝህ እንኳ በተስፋላይ ሁኘ ሌላይቱን አለም
እቀላቀላለሁ ሁሌም እወደሀለሁ ።

ሰኞ ማታ ስገላበጥ እሱ ጋር አብረን ያሳለፍነዉን ትዝ እያለኝ እንደ መፀፀት በደስታ ስገላበጥ አደርኩኝ፡፡ ግን በጣም ግራ ተጋብቻለሁ እኔ ነኝ ማለት ነዉ ሂክማ ያ ቆራጥ አመራሬ በትምህርት ቤት ጓደኞቼ መምህሮቼ እንደ ሂክማ ሁኑ ተብሎ በጥሩ ባህሪየ ስነምግባር የምታወቀዉ በሀይደር እንደዚህ እሆናለሁ ብየ መቼም አስቤዉ አላቅም፡፡ ብቻ ሰዉ የሚሸወደዉ በመወሰኑ አይደለም ለምን ኸይር ስራም ቢዝነስም ማንኛዉም ህይወት በዉሳኔ የፀናች ሲሆን ግን ሳናጣራ ግንዛቤዉ ሳይኖረን የምንወስነዉ ዉሳኔ የወደፊት ሂወት ሊያጨልምብን ይበራል ይደምቃል ብለን ያሰብነዉ በተዘዋዋሪ ሊጨለም እና ከጭልመቱም በላይ ብርሀን ቢያገኝ እንኳ አስፈሪ ቁጭት ያለዉ ጨለማ ሊሆን ይችላል፡፡

ጠንቃቃ ነጋዴዌች የሚሉት አሉ ሶስት ጊዜ ለካ አንድ ጊዜ ቁረጥ ይላሉ አዉነት ነዉ፡፡ ሀሳብም ቢሆን አንድ ሀሳብ በሶስት መልኩ ማየት መቻል አለብን ፡፡ አንደኛዉ የመጀመሪያዉ መጥፎ ጎኑን ..መጥፎ ጎን ይዞ ቢመጣ በምን ወደነበረበት መመለስ እችላለሁ ወይ ሲሆን....ሁለተኛዉ ጥሩ ጎኑን መሳብ አለብን ...ጥሩ ጎኑ ለኔ ምን ያህል ጠቃሚ ነዉ ብለን ማሰብ መቻል አለብን፡፡ ሶስተኛዉ ዱንያ ስለሚሆን ጥሩ ተስፋ በአእምራችን ላይ ሙሉ በሙሉ መስጠት አያስፈልግም፡፡ የሰዉ ልጅ በጣም የሂወቴ መርህ መለወጫየ ነዉ ብሎ ተስፋ ካረገ ይህ ተስፋ ያረገዉ ነገር ካልተሳካ በጣም የሞራል ዉድቀት እና መልሶ ተስፋ እንዳያደርግ እና በጌታ ላይ ተወኩል ማረግ ሊዘናጋ ይችላል፡፡ ተስፋዎች ማሰብ ባይከፋም ...ግን ኔጌቲቭ ሀሳቦች አብሮ ማሰብ ያሰፈልጋል ዱንያ ነዉ አላህ ከፃፈልን ዉጭ የማይሆን ነገር ነዉ ይህ የአሰብኩት ተስፋ ግብ ካልመታ ወደ በፊቱ ያለበት እስቴፕ ቶሎ መመለስ መቻል አለበት፡፡ ወደ በፊቱ ማንነት ለመመለስ ደግሞ ካሳለፍነዉ የጨለማ ሂወት ያለፉ ታሪኮች ሊከብድ ስለሚችል ያንን በብቃት መወጣት መቻል አለብን፡፡

እኔ ለራሴ የወደፊት ባሌ ሀይደር ነዉ ብየ 100% .እርግጠኛ ነኝ፡፡ ማንም የሚወስድብኝ እሱን የሚያፈቅርብኝ ያለ አይመስለኝም፡፡ እሱም እንደነገረኝ ከእኔ ዉጭ እንደማያገባ የቃልኪዳን ቀለበት እና ሀብል ሰጥቶኛል፡፡ ግን ልቤን ጭንቅ ይለኛል ቢተወኝስ እላለሁ እንደገና አይ ሀይደር በጭራሽ አያረገዉም እላለሁ እንደማያረገዉም እርግጠኛ ነኝ.........

#part 9 ይቀጥላል
147 views09:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-17 12:57:19 እዉነተኛ ታሪክ

#Part

በእሱ ቁጥጥር ሁኛለሁ የመጀመሪያየ ነበር እሺም እሞቢም የማለቱ ድፍረቱን አጥቻለሁ በስሜት ወድቂያለሁ፡፡ ሀይደር እንደፈለገ ያረገኝ ይዟል ሲፈልግ ይስመኛል ........... በቃ የማላቀዉ አለም ዉስጥ ገባህ እንጃ የዛን ጊዜ የእሁድ ምሽቱን ለመናገር ይቀፈኛል፡......ልብሴን እንኳ እራሴ አላወጣሁም የሚሆነዉ ነገር ማስታወስ አልቻልኩም ስሜት ላይ ነበርኩኝ.......

ፍትጊያዉ ጀምሯል፡፡ የሆነ ሰአት ላይ ካቅሜ በላይ ሁኖ ብቻ ስጮህ አስታዉሳለሁ፡፡
እሱም አይዞሽ ሂኩየ እያለ ወደ ማላቀዉ አለም የትንሽ ሰአታት ደስታ የዘላለም ሂወት ማጨለሚያ የሆነዉን አፀያፊ ስራ እየሰራሁ ነዉ፡፡ ፍትጊያዉ አልቻልኩትም ጮሀኩን የሚሰማኝ የለ....,.,..,,,ከትንሽ ቆይታ ቡሀላ ያ ያማረ ነጭ አንሶላ በቀይ ደም መልኩን ቀየረ፡፡
.....ክብሬን ለሀይደር በሀራም መንገድ አስረከብኩ...ቀይ ደም ሳይ ደነገጥኩኝ.....ወዳዉ እዛዉ መኝታ ክፍል ሻወር ነበር ታጠብኩ ...ከታጠብኩ ቡሀላ ወደ ግድግዳ ዙሬ ተኛሁ እሱም ወደ እኔ ዙሮ ሂኩ ሲለኝ ቆይ ትንሽ ልረፍ ደክሞኛል አልኩት፡፡

...እሱም እሺ ብሎ ተኛ እኔም ተኛሁ፡፡ ግን ተኝቼ መጨነቅ ጀመርኩ ቢተወኝስ እያልኩኝ...እናቴን ለዚና ዋሸሁኝ....,እናቴ ብታየኝ ምን ትለኛለች አምናኝ እናቴን ከደሇት...

ሱብሂ ሶላት ደረሰ ዉዱእ አርጌ ሰገድኩ ግን ዱአየ አላህ ዚና ሰራሁ ማረኝ ሳይሆን....አላህ ሀይደርን የትዳር አጋሬ አርግልኝ ነበር፡፡
...እኔም ሱብሂ ተነስ ስገድ አልኩት እሱም እሺ እሺ እያለ ሳይሰግድ ቀረ፡፡

የማይነጋ የለም ነጋ ቁርስ እዛዉ ኩሪፍቱ ሆቴል
አዘዘ በላን ሂኩየ በጣም ነዉ ያኮራሽኝ ማሻ አላህ ዘልዛላ አይደለሽም ማሻ አላህ ኮራሁብሽ አለኝ፡፡ ቁርስ በልተን ጨረስን ....ከዛ ከደብረ ዘይት ወደ አዲስ አበባ ለመመለስ ጉዟችንን ቀጠልን ከደብረዘይት ተመልሰን ገርጂ ደረስ በመኪና ሸኘኝ ከዛም ተሳስመን፡ተለያየን፡፡ አሁን እኔም ወደ እናቴ ጋር እቤቴ ድረስ ሸኘኝ እኔን እቤቴ ካደረሰኝ ቡሀላ እሱም ወደ ቤቱ ተመለሰ.......
......እቤቴ ሄድኩኝ እናቴ እንኳን ደህና መጣሽ ብላ ግንባሬን ሳመችኝ...የእናት ነገር ብርድ ሳይበርድሽ አደረ ልጄ አለችኝ
...እኔም አዎ እናቴ አልኳት
......በይ አረፍ በይ ስራዉን አጠቃለላችሁ ጓደኛሽን አግዥሻት አለችኝ
....እኔም አዎ እናቴ አልኩኝ፡፡
ቁርስ ብይ አለችኝ
እኔም ጓደኛየ ቤት በልቼ ነዉ የመጣሁት አልኳት፡፡
እናቴም እሺ አለችኝ፡፡ መቼም የዛሬዉ ትምህርት ቀርቷል ነገ ድካሙ ሲለቅሽ ትሄጃለሽ አለችኝ፡፡

ዚና ስሰራ እንዳደርኩ የሴትነት ክብሬን እንደተነጠኩ ብሰማ እናቴ ምን ትለኝ ይሆን......
ብየ ብቻየን አለቀስኩኝ ........እንባዬ ዱብ ዱብ ይላል ግን የማለቅሰዉ እኔም ግራ ገብቶኛል፡፡ ሀይደር ይተወኛል ብየ አስቤ ነዉ ??ወይስ ላተቅረቡ ዚና ጌታየ ብሎኝ እኔም የጌታየን ትእዛዝ መጣሴ ነዉ?? ነገ አላህ ፊት ሲጠይቀኝ መልስ ይኖረኝ ይሁን ብቻ እንባየ በሁለቱ ጥያቄ እየጠየኩ ብቻ መልስ በሌለዉ ጥያቄየ እያለቀስኩ ነዉ፡፡

ውስጤ ብሶት አለ
.
እንደ ጥገኛ ትል ከሆድ የማይጠፋ
ውስጤ ችግር አለ ከሀገር የሚሰፋ
ስኖር በዚች አለም ስርክ የገበርኩለት
በዋይታ በዬዬ....እልፍ ያለቀስኩለት
በእንባዬ ብቻ.....በትግስት ያለፍኩት
አካልን አድምቶ .... ሆድ የበጠበጠ
ከጠጠር ጠጥሮ ውስጥ የተቀመጠ
ብሶት አለ ውስጤ
,
ቃላት ማይገልፀው ከሆድ ማይጠፋ
አካሌ ላይ አፎ.....ሁሌም የሚፋፋ
እንባ እየወለደ ...ሀዘን የሚያረግዝ
ደስታዬን በዝብዞ ልብ የሚጠዘጥዝ
እንደ ጥገኛ ትል ከሆድ የማይጠፋ
ውስጤ ችግር አለ ከሀገር የሚሰፋ
ውስጤ ብሶት አለ ፈፅሞ እማይጠፋ

ምሳ ሰአት ላይ ትናንት ዋሽቼ የለ ያደርኩት እጓደኛየ ቤት አቂቃ አለ ብየ ...እናቴን ሄድኩ ብየ ከቤት ወጣሁ በአዲስ አበባ ጎዳና ከገርጂ ተነስቼ እስከ ጎሮ ድረስ በእግሬ እየሄድኩ ብቻየን እያለቀስኩ እንደ መሳቅም እያልኩ ጅል ይመስል የተለያየ የተዘበራረቀ ስሜት እየተሰማኝ እየሄድኩ ነዉ ግን የት እንደምሄድ አላቀዉም...........ብቻ እግሬ ወደ መራኝ ቦታ እየሄድኩ ነዉ፡፡

ሳላስበዉ ድንገት ስልኬ ጠራ የደወለዉ ሀይደር ነበር ሰላምታ ከተለዋወጥን ቡሀላ የት ነሽ ምሳ ልጋብዝሽ አለኝ፡፡ እኔም ያለሁበትን ቦታ ነገርኩት መኪና ስላለዉ ብዙ ደይቃዎች አልፈጁበትም ቶሎ መጥቶ ወደ ወበሪ ሆቴል ሂደን ምሳ ጋበዘኝ፡፡ ምሳ ከበላን ቡሀላ ከሰአት የት ነሽ አለኝ ፡፡ እኔም የምሄድበት የለም አልኩት
..........ሂኩ ለምን ደብረ ዘይት አንሄድም ዛሬ ግን ለመዝናናት ብቻ ነዉ ፡፡ ደብረዘይት ከተማዋን አይተናት ለመመለስ ነዉ እንጂ ለሌላ አይደለም አለኝ አይን አይኔን እያየ... እኔም እምቢ የማለት ድፍረት አጣሁ አንዴ ልቤን ሀይደር ወስዶታል፡፡ እሺ ስለዉ እዛዉ ተሳሳምን አይ ወንጀሌ ...............
ጉዞ ዳግም ወደ ደብረዘይት ለስለስ ያሉ የሱዳን ነሽዳዎች መኪናዉ ላይ ከፍቶት ጉዟችንን ቀጠልን፡፡

የኔ ነገር ገና አላለቀም ዳግም ትናንት ክብረ ንፅህናየን የተነጠኩበት ደብረዘይት እየሄድኩ ነዉ ፡፡ የወደፊቱ ባሌ ሀይደር ጋር ነኝ፡፡ እሁድም ደብረዘይት ሰኞም ደብረዘይት በሚቀጥለዉ part ጋር የሰኞ ከሰአት ጉዴን አጫዉታችሇለሁ

#Part ይቀጥላል
151 views09:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-17 12:57:19 እዉነተኛ ታሪክ

#Part

ሂኩ ዝም አልሽ እሳ አለኝ ....እቤት እናቴ ትቆጣለች ከእናቴ ተነጥየ አድሮ አላቅም የት አደርሽ ብትለኝ ምን እላለሁ አልኩት
...እሱም ምክንያት ፍጠሪ አለኝ፡፡
ነገም ሰኞ ነዉ ትምህርት አለኝ እንዴት ብየ እቀራለሁ ብየ የማምለጫ ሀሳብ ባቀርብ የኔ ሀሳብ አንድሱ በሚሰጠኝ መልስ ላስምነዉ አልቻልኩም እምቢ የምልበት ምክንያት አጣሁ፡፡ በዛ በዚህ ብሎ አሳመነኝ ..እምቢ የምልበት ቃል የለኝም......

በመጨረሻም እሺ አልኩኝ....እሱም በደስታ ከንፈር ለከንፈር ጨዋታችንን አጧጧፍነዉ...በቃ የተለየ ስሜት ገባን እኔም ሁኔታዉ ስላላማረኝ ተረጋጋ ሁሌም ፧በሰአቱ ይደርሳል አልኩት፡፡
...እቤት ደዉለሽ አስፈቅጂ አለኝ
......እኔም ለእናቴ ደወልኩኝ
..እናቴም ስልኩን አነሳችዉ
ሀሎ ልጄ ልደዉልልሽ ስል ደወልሽልኝ እንዴት ዋልሽ አለችኝ ጊዜዉ ወደ መቅሪብ ሶላት ደርሷል፡፡
እኔም ደህና ነኝ እናቴ ያዉ እንደነገርኩሽ የጓደኛየ ቤት አቂቃዉ በስራ ዉጥርጥር ብየ ነዉ አልኳት
እናቴም አይዞሽ ጓደኛሽ አይደለች የእሷን ደስታም ሀዘንም አብረሽ መወጣት አለብሽ አለችኝ
....እናቴ .አሁንም እዛ ላድር ነዉ ስራዉ አላለቀም ፡፡ እናዳትሰጊ ልደዉልልሽ ብየ ነዉ አልኳት
.....እናቴም ቅር እያላት ሙሉቀን ሳላይሽ ዋልኩ አሁንም ቀረሽብኝ እሺ ምን አረጋለሁ ልጄ አደራሽን ተጠንቀቂ አለችኝ፡፡ ጭራሽ እኔን ወንድ ጋር ትሄዳለች ብላ አስባዉም አታቅ እናቴ በኔ የምትተማመንብኝ ነኝ ወይኔ ሂክማ ምን አረጋለሁ በሀራም መንገድ ፍቅር ዋሽቼ የማላቀዉን ለወደፊት ተስፋ እና በስጦታ አንበሽብሾ ይሄዉ ለሀይደር ብየ እየዋሸሁ ነዉ፡፡
...እኔም እሺ አልኩኝ
.......እናቴም ግን ሙሉቀን ምግብ ቀምሰሻል አለችኝ
...እኔም አዎ እናቴ አልኩኝ የእናት አንጀት የምታስበዉ አሁንም ለኔ ነዉ፡፡
....እናቴም እሺ ንፋስ እንዳይመታሽ ከምታድሪበት የጓደኛሽ ቤት ሹራብ ደረብ አርገሽ ስሪ ልጄ ...አይዞሽ ደህና እደሪ..ነገ ግን በጠዋት ነይ ዛሬ ሙሉቀን አላየሁሽም ...አንቺዉ ነሽ ያለሽኝ ትናፍቂኛለሽ ነገ አይንሽን እንዳይሽ አለችኝ
...እኔም እሺ እናቴ ደህና እደሪ ብየ ስልኩን ዘጋሁት ፡፡

ሀራም ለመስራት እናቴን ስንቱን ዉሸት ዋሸሁ..እናቴ አምናኝ አልጠረጠረችም ምን ይደረጋል...ሀይደርም ማሻ አላህ በዉሸት ማሳመን ትችያለሽ ማለት ነዉ አለኝ፡፡

እኔም ምን ላርግ ብለህ ነዉ ምንም አማራጭ የለኝ ፡፡
ለአንተ ብየ ነዉ እንጂ እንደዚህ የምዋሸዉ እናቴን ዋሽቼ አላቅም ነበር ምን ይደረጋል አልኩት፡፡
እሱም ነገ እናትሽ የጓደኛሽን ቤት አሳይኝ ብትልሽ እሳ አለኝ
....እኔም እናቴ ታምነኛለች አትለኝም አልኩት፡፡

አንተስ አታስፈቅድም እንዴ አልኩት
..እሱም አስፈቅጃለሁ አለኝ፡፡ አሁን ሰአቱ ከምሽቱ 1:30 አካባቢ ሁኗል የጨረቀዋ ዉበት ሙሉ ለሙሉ ባይሆንም ደስ የሚል ድባብ ነበረዉ፡፡ ግን የሚገርማችሁ አሱር እና መቅሪብ ሶላት አልሰገድንም ነበር፡፡ እሱም እንስገድ አላለኝም....
እዛዉ ባቡጋያ ሪዞርት እራት አዘዝን እሱም ማደሪያ መኝታ ክፍል ያዘ፡፡
እኔም ሀይደር ዛሬ እኮ አሱር እና መቅሪብ አልሰገድንም እኮ አልኩት
...እሱም ሂኩ የሚገርም ነዉ እየቀለደ ሙሳፊር ነን እኮ በዛም ላይ የአንቺ ፍቅር ሶላት አስረሳኝ በይ ዉዱእ እናርግ እና እንስገድ አለኝ፡
ባቡጋያ ሪዞርት በሚገኘዉ እዛዉ መዝናኛዉ ዉስጥ አነስ ባለች ቤት መስገጃ ቦታ በተዘጋጀች ቤት እኔ መጀመሪያ አሱር መቅሪብ ቀዷዉን ኢሻን በወቅቱ ሰገድኩ

እኔ ሰግጄ ስጨርስ እኔ ወጣሁ እሱ ገብቶ ሶላቱን ጀመረ አሱር መቅሪብ ኢሻ ለመስገድ ገባ፡፡....ግን ቶሎ ብሎ ሶስቱን ሶላት ጨርሶ ከመስገጃ ቤቱ ወጣ ፡፡ ...... ሀይደር ሶላት የሰገደ ሳይሆን የህሊና ፃለት አርጎ የመጣ ነዉ የሚመስለዉ፡፡ በጣም ፈጠነብኝ ..እኔም ፈጠንክ ልለዉ አልኩና ዝም አልኩት፡፡
የአዘዝነዉ እራት ደረሰ እየተጎራረስን በላን በቃ የሚምር እራት ግብዣ ነበር፡፡ አንቺ ጋር እራት ስበላ የመጀመሪያየ በጣም ደስተኛ ነኝ ሀዩ አንቺስ አለኝ...
እኔም ደስተኛ ነኝ አልኩት
እሱም ኢንሻ አላህ ዛሬ ሆቴል ብላን ለወደፊት አንድ ላይ ልጆቻችንን ይዘን እቤታችን ነዉ የምንበላዉ ብሎ ጉንጬን ሳመኝ፡፡

በልተን ጨረስን አሁን ሰአቱ ከምሽቱ 2:30 ሁኗል ፡፡ ሂኩ ወደ መኝታ ክፍል እንሂድ አለኝ ፡፡ እኔም ቅር እያለኝ ደስም እያለኝ ተያይዘን መኝታ ክፍል ገባን ......በሩን ሲከፍተዉ የሚያምር ክላስ ነዉ ሻማ የበራበት ነበር፡፡ ሂጄ አልጋዉ ጋር ቁጭ አልኩኝ እሱም በሩን ዘግቶ ከጎኔ መጥቶ ቁጭ አለ፡፡ ጨዋታዉ ጀመረ ...ሀይደር ወደ እኔ ተጠጋ እና ሂኩ አለኝ .....እኔ በእሱ ፍቅር ተሸንፊያለሁ የሚያረገኝን ለመቀበል ዝግጁ ነኝ...........ወደ እኔ ተጠግቶ ሂኩ እወድሻለሁ ብሎ ..........,

#part 8 ይቀጥል
155 views09:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ