2022-08-06 15:22:06
እዉነተኛ ታሪክ
#Part
በእሱ ቁጥጥር ሁኛለሁ የመጀመሪያየ ነበር እሺም እሞቢም የማለቱ ድፍረቱን አጥቻለሁ በስሜት ወድቂያለሁ፡፡ ሀይደር እንደፈለገ ያረገኝ ይዟል ሲፈልግ ይስመኛል ........... በቃ የማላቀዉ አለም ዉስጥ ገባህ እንጃ የዛን ጊዜ የእሁድ ምሽቱን ለመናገር ይቀፈኛል፡......ልብሴን እንኳ እራሴ አላወጣሁም የሚሆነዉ ነገር ማስታወስ አልቻልኩም ስሜት ላይ ነበርኩኝ.......
ፍትጊያዉ ጀምሯል፡፡ የሆነ ሰአት ላይ ካቅሜ በላይ ሁኖ ብቻ ስጮህ አስታዉሳለሁ፡፡
እሱም አይዞሽ ሂኩየ እያለ ወደ ማላቀዉ አለም የትንሽ ሰአታት ደስታ የዘላለም ሂወት ማጨለሚያ የሆነዉን አፀያፊ ስራ እየሰራሁ ነዉ፡፡ ፍትጊያዉ አልቻልኩትም ጮሀኩን የሚሰማኝ የለ....,.,..,,,ከትንሽ ቆይታ ቡሀላ ያ ያማረ ነጭ አንሶላ በቀይ ደም መልኩን ቀየረ፡፡
.....ክብሬን ለሀይደር በሀራም መንገድ አስረከብኩ...ቀይ ደም ሳይ ደነገጥኩኝ.....ወዳዉ እዛዉ መኝታ ክፍል ሻወር ነበር ታጠብኩ ...ከታጠብኩ ቡሀላ ወደ ግድግዳ ዙሬ ተኛሁ እሱም ወደ እኔ ዙሮ ሂኩ ሲለኝ ቆይ ትንሽ ልረፍ ደክሞኛል አልኩት፡፡
...እሱም እሺ ብሎ ተኛ እኔም ተኛሁ፡፡ ግን ተኝቼ መጨነቅ ጀመርኩ ቢተወኝስ እያልኩኝ...እናቴን ለዚና ዋሸሁኝ....,እናቴ ብታየኝ ምን ትለኛለች አምናኝ እናቴን ከደሇት...
ሱብሂ ሶላት ደረሰ ዉዱእ አርጌ ሰገድኩ ግን ዱአየ አላህ ዚና ሰራሁ ማረኝ ሳይሆን....አላህ ሀይደርን የትዳር አጋሬ አርግልኝ ነበር፡፡
...እኔም ሱብሂ ተነስ ስገድ አልኩት እሱም እሺ እሺ እያለ ሳይሰግድ ቀረ፡፡
የማይነጋ የለም ነጋ ቁርስ እዛዉ ኩሪፍቱ ሆቴል
አዘዘ በላን ሂኩየ በጣም ነዉ ያኮራሽኝ ማሻ አላህ ዘልዛላ አይደለሽም ማሻ አላህ ኮራሁብሽ አለኝ፡፡ ቁርስ በልተን ጨረስን ....ከዛ ከደብረ ዘይት ወደ አዲስ አበባ ለመመለስ ጉዟችንን ቀጠልን ከደብረዘይት ተመልሰን ገርጂ ደረስ በመኪና ሸኘኝ ከዛም ተሳስመን፡ተለያየን፡፡ አሁን እኔም ወደ እናቴ ጋር እቤቴ ድረስ ሸኘኝ እኔን እቤቴ ካደረሰኝ ቡሀላ እሱም ወደ ቤቱ ተመለሰ.......
......እቤቴ ሄድኩኝ እናቴ እንኳን ደህና መጣሽ ብላ ግንባሬን ሳመችኝ...የእናት ነገር ብርድ ሳይበርድሽ አደረ ልጄ አለችኝ
...እኔም አዎ እናቴ አልኳት
......በይ አረፍ በይ ስራዉን አጠቃለላችሁ ጓደኛሽን አግዥሻት አለችኝ
....እኔም አዎ እናቴ አልኩኝ፡፡
ቁርስ ብይ አለችኝ
እኔም ጓደኛየ ቤት በልቼ ነዉ የመጣሁት አልኳት፡፡
እናቴም እሺ አለችኝ፡፡ መቼም የዛሬዉ ትምህርት ቀርቷል ነገ ድካሙ ሲለቅሽ ትሄጃለሽ አለችኝ፡፡
ዚና ስሰራ እንዳደርኩ የሴትነት ክብሬን እንደተነጠኩ ብሰማ እናቴ ምን ትለኝ ይሆን......
ብየ ብቻየን አለቀስኩኝ ........እንባዬ ዱብ ዱብ ይላል ግን የማለቅሰዉ እኔም ግራ ገብቶኛል፡፡ ሀይደር ይተወኛል ብየ አስቤ ነዉ ??ወይስ ላተቅረቡ ዚና ጌታየ ብሎኝ እኔም የጌታየን ትእዛዝ መጣሴ ነዉ?? ነገ አላህ ፊት ሲጠይቀኝ መልስ ይኖረኝ ይሁን ብቻ እንባየ በሁለቱ ጥያቄ እየጠየኩ ብቻ መልስ በሌለዉ ጥያቄየ እያለቀስኩ ነዉ፡፡
ውስጤ ብሶት አለ
.
እንደ ጥገኛ ትል ከሆድ የማይጠፋ
ውስጤ ችግር አለ ከሀገር የሚሰፋ
ስኖር በዚች አለም ስርክ የገበርኩለት
በዋይታ በዬዬ....እልፍ ያለቀስኩለት
በእንባዬ ብቻ.....በትግስት ያለፍኩት
አካልን አድምቶ .... ሆድ የበጠበጠ
ከጠጠር ጠጥሮ ውስጥ የተቀመጠ
ብሶት አለ ውስጤ
,
ቃላት ማይገልፀው ከሆድ ማይጠፋ
አካሌ ላይ አፎ.....ሁሌም የሚፋፋ
እንባ እየወለደ ...ሀዘን የሚያረግዝ
ደስታዬን በዝብዞ ልብ የሚጠዘጥዝ
እንደ ጥገኛ ትል ከሆድ የማይጠፋ
ውስጤ ችግር አለ ከሀገር የሚሰፋ
ውስጤ ብሶት አለ ፈፅሞ እማይጠፋ
ምሳ ሰአት ላይ ትናንት ዋሽቼ የለ ያደርኩት እጓደኛየ ቤት አቂቃ አለ ብየ ...እናቴን ሄድኩ ብየ ከቤት ወጣሁ በአዲስ አበባ ጎዳና ከገርጂ ተነስቼ እስከ ጎሮ ድረስ በእግሬ እየሄድኩ ብቻየን እያለቀስኩ እንደ መሳቅም እያልኩ ጅል ይመስል የተለያየ የተዘበራረቀ ስሜት እየተሰማኝ እየሄድኩ ነዉ ግን የት እንደምሄድ አላቀዉም...........ብቻ እግሬ ወደ መራኝ ቦታ እየሄድኩ ነዉ፡፡
ሳላስበዉ ድንገት ስልኬ ጠራ የደወለዉ ሀይደር ነበር ሰላምታ ከተለዋወጥን ቡሀላ የት ነሽ ምሳ ልጋብዝሽ አለኝ፡፡ እኔም ያለሁበትን ቦታ ነገርኩት መኪና ስላለዉ ብዙ ደይቃዎች አልፈጁበትም ቶሎ መጥቶ ወደ ወበሪ ሆቴል ሂደን ምሳ ጋበዘኝ፡፡ ምሳ ከበላን ቡሀላ ከሰአት የት ነሽ አለኝ ፡፡ እኔም የምሄድበት የለም አልኩት
..........ሂኩ ለምን ደብረ ዘይት አንሄድም ዛሬ ግን ለመዝናናት ብቻ ነዉ ፡፡ ደብረዘይት ከተማዋን አይተናት ለመመለስ ነዉ እንጂ ለሌላ አይደለም አለኝ አይን አይኔን እያየ... እኔም እምቢ የማለት ድፍረት አጣሁ አንዴ ልቤን ሀይደር ወስዶታል፡፡ እሺ ስለዉ እዛዉ ተሳሳምን አይ ወንጀሌ ...............
ጉዞ ዳግም ወደ ደብረዘይት ለስለስ ያሉ የሱዳን ነሽዳዎች መኪናዉ ላይ ከፍቶት ጉዟችንን ቀጠልን፡፡
የኔ ነገር ገና አላለቀም ዳግም ትናንት ክብረ ንፅህናየን የተነጠኩበት ደብረዘይት እየሄድኩ ነዉ ፡፡ የወደፊቱ ባሌ ሀይደር ጋር ነኝ፡፡ እሁድም ደብረዘይት ሰኞም ደብረዘይት በሚቀጥለዉ part ጋር የሰኞ ከሰአት ጉዴን አጫዉታችሇለሁ
#Part ይቀጥላል
1.1K views12:22