Get Mystery Box with random crypto!

ሀላል ትዳር👫💍

የቴሌግራም ቻናል አርማ hayu_abdi — ሀላል ትዳር👫💍
የቴሌግራም ቻናል አርማ hayu_abdi — ሀላል ትዳር👫💍
የሰርጥ አድራሻ: @hayu_abdi
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 8.54K

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2022-08-28 22:50:35 ከአላህ ውጭ ሱጁድ የሚደረግለት ነገር የለም እንጅ
ሚስት ለባሏ ሱጁድ እንድታደርግ አዝ ነበር

ሀቢቡና ሙሀመድ ሰ.ዐ.ወ
754 views19:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 10:55:16 ራት ትንሽ ነበር፡፡ኢንቱ ‹‹እኔ በቃኝ!›› አለች፡፡ እኔ መብላቴን ከብዙ ጭቅጭቅ በኋላ በአብዱኬ ምስክርነት አሳምኛቸው መብላት ጀመሩ፡፡ በልቤ ዛሬ ኢንቱዬ እውነቱን እንድትነግረኝ ተመኘሁ፡፡
.
ይቀጥላል …
959 views07:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 10:54:44 ውስጥ?››
ፈገግ አለችና ‹‹አቤላ ከፈቀደልን ካንተ ጋር የሆነ ቦታ ደርሰን እንድንመጣ ፈልጌ ነበር!›› አለች፡፡
አቤል እየሳቀ ‹‹ምን ጣጣ አለው …… ብቻ እንደትናንትናው ብዙ በር ያለበት ቤት አስገብተሽው እንዳይጠፋ!›› አለ፡፡
አቤላን ተሰናብተን መኪናዋ ውስጥ ገባን፡፡ መኪናው ውስጥ ያለው ጠረን ደስ ይላል፡፡
‹‹እሺ …… ወዴት ነን?›› አልኳት ቀበቶዋን የምታስረውን ማህሌትን እየተመለከትኩ!
‹‹you will see it! …… አንድ ቦታ እወስድሀለሁ …… unfortunetly ለዛሬ ጥናት ያልፍሀል፡፡ I hope you won’t get mad! yeah?››
‹‹እሺ ግን ይኼን ያህል ጊዜ የሚወስደው ምን ቢሆን ነው?››
‹‹please be patient!›› ሳቀች፡፡
መኪናዋን በአርባ ሜትሩ በኩል እያካለበች ጦርሀይሎችን አልፋ …. ቶታልን ዞራ …. ሞቢል ጋር የሚገኘው ካልዲስ ኮፊ ግቢ ውስጥ ቆመች፡፡
አስተናጋጁ ሲመጣ ለእኔም ለእሷም አዘዘች፡፡ ምን እንደምፈልግ አልጠየቀችኝም፡፡ የመኪናውን መስታወቶች ዘጋቻቸው፡፡
‹‹አብርሽዬ …… እስኪ just tell me ምን የጎደለኝ ይመስልሀል?››
‹‹እኮ አንቺ?››
‹‹yeah እኔ!››
‹‹አትቀልጂ ባክሽ! ምንም ነዋ! ምንም ነው የጎደለሽ!›› ሳቅ አለች፡፡
‹‹I was የአምስት አመት ህፃን ምናምን ነገር when my mom dies! Dad single parent ሆኖ ነው ያሳደገኝ!››
‹‹እናትሽ ሞታለች እንዴ? ይቅርታ አላወቅኩም ነበር!››
‹‹Its okay! Its okay! Feel free!››
‹‹ወንድምም ሆነ እህት የለኝም፡፡ I am the only one! …… Dad is በጣም busy! ስራውን ቤት ሳይቀር ነው የሚሰራው! Somedays በጣም ብቸኝነት ይሰማኝ ነበር፡፡ ለኔ ብሎ ድጋሚ አላገባም! He is married to his work! የኛን ቤት ስታይ ይህን ገምተሀል?››
‹‹በፍፁም! በፍፁም አልገመትኩም!››
‹‹So እኔም እንዳንተ ፈጣሪ ከኔ ጋር መልካም ግንኙነት የለውም ማለት እችላለሁ አይደል?›› ሳቀች፡፡
‹‹የኛ እኮ በሁሉም ነው! አንቺ እኮ በአንዱ ብትከፊ ሌላ መፅናኛ አለሽ!››
‹‹ሀብታም ነን I know! ሰው ግን የለኝም! Even በእሱም ቢሆን አላማርርም!››
አስተናጋጁ ምግቡን ይዞ መጣ፡፡ ፒዛ ነበር፡፡ እየበላን ማውራት ጀመርን፡፡
‹‹Okay let’s play a game እስኪ አይንህን ጨፍንና ስለእኔ ጥሩ ጥሩ ጎኔን ንገረኝ!››
አይኔን ጨፍኜ ስለማህሌት አሰብኩ፡፡
‹‹ማህሌት …… ቀላ ያለች፣ አይኖቿ ትላልቅ፣ ፀጉሯ ረዥም፣ ሁሌ ቀሚስ የምትለብስ ……››
‹‹No! No! Come on! ግለፀኝ አይደለም ያልኩህ! ፈጣሪ ለእኔ የሰጠኝን መልካም ፀጋ ቁጠርልኝ!››
‹‹እሺ …… ማህሌት ቅን ነች! ደግ ነች! በጣም ቆንጆ ናት! ጎበዝ ተማሪ ናት! አባት አላት! የምግብ ችግር የለባትም ማለቴ የሀብታም ልጅ ናት! ጥሩ ጓደኞች አሏት! በቃ!››
‹‹Okay open your eyes. አንተ ስለኔ ሰባት ጥሩ ነገር ቆጥረሀል፡፡ አሁን የኔ ተራ ነው፡፡›› አይኖቿን ጨፈነች፡፡ አይኗን ስትጨፍን የበለጠ ታምራለች፡፡ ከንፈሮቿ ያሳሳሉ፡፡
‹‹አብርሽ …… በራሱ ይተማመናል! በጣም Genius ነው፡፡ በጣም የምታምር Smart እህት አለችው፡፡ እናቱ በህይወት አሉ፡፡ በጣም ቆንጆ ነው፡፡ amazing friends’ አሉት! በጣም ግልፅ ነው! ጥሩ ስነ-ምግባር አለው! ጤነኛ ነው!›› አይኗን ከፈተች፡፡
‹‹So እኔ ዘጠኝ ቆጠርኩ! አሸነፍኩህ ማለት ነው!››
ዘጠኝ መልካም ነገር አለኝ? አስቤው አላውቅም ነበር፡፡
ክላክስ እያደረገች ‹‹ፈጣሪን ምን አድርግልኝ ብለኸው ታውቃለህ?›› አለችኝ፡፡
‹‹አባቴን አትርፍልኝ ብዬው አውቃለሁ …… ገደለው! እህቴ ላይ መከራ አታብዛባት አልኩት …… ደራረበባት! እማዬን አሽልልኝ አልኩት …… ህመሟን ጨመረው! በጠየቅኩት ቁጥር ተቃራኒው እየሆነ ነው፡፡ ስለዚህ ተውኩት! አትድረስብኝ አልደርስብህም ብዬ ማለት ነው!››
‹‹ጎበዝ አድርገኝ አላልከውም …… ጎበዝ አደረገህ! ጤናዬን አደራ አላልከውም …… ጤነኛ አደረገህ! Why don’t you see መልካም መልካሙን?››
አስተናጋጁ ትኩስ ነገር ይዞልን መጣ፡፡
‹‹የቆምኩበት ቦታ ከባድ ነው ሚቾ!››
‹‹what you just call me? ሚቾ! Wow! ወድጄዋለሁ! ሁሌ እንደሱ ጥራኝ!›› አለችና ማኪያቶዋን እየማገች ስለ ተስፋ፣ ስለ ፈጣሪና ስለህይወት ያላትን አመለካከት ታስረዳኝ ጀመረች፡፡
አብራርታ ስትጨርስ ‹‹እስኪ ያንተን ንገረኝ!›› አለች፡፡
‹‹እኔ ስለ ረሀብ ነው የማስበው! ገና ስለምግብ ነው የምጨነቀው! በባዶ ሆዴ ደግሞ አንቺ ያልሽው አይነት ተስፋም፣ ህይወትም፣ ፈጣሪም …… ሊያፈላስፉኝ አይችሉም፡፡ ፍልስፍናዬ ረሀብ ነው፡፡ ፍልስፍናዬ የእህቴ ስቃይ፣ የእናቴ ህመም ነው፡፡›› አይኔ እንባ ሞላ፡፡
ብርጭቆዋን ዳሽ ቦርዱ ላይ አስቀምጣ ጭምቅ አድርጋ አቀፈችኝ፡፡ አንገቴን ደረቷ ስር ቀብሬ አነባሁ፡፡ ስረጋጋ ሂሳብ ከፈለችና መኪናዋን አስነሳች፡፡ ጨልሞ ነበር፡፡ ወደ ሰፈር እየተመለስን ‹‹ሚቾ …… ሐዋርያት ማለት ግን ምን ማለት ነው?›› አልኳት፡፡
ፈገግ አለች፡፡ ፈገግ አልኩኝ፡፡
‹‹Okay …… ሐዋርያት የእምነቱ ተከታዮች የምንጠራበት ስያሜ ነው፡፡ ቤተክርስትያናችን ደግሞ ሐዋርያዊት ነው የምትባለው!››
‹‹እሺ ሐዋርያዊት ማለት ምን ማለት ነው? ጥያቄዬ እሱ ነበር! ማለቴ ስለእምነቱ!››
‹‹ሐዋርያዊት is a religion በአንድ አምላክ የሚያምን …… በእየሱስ ስም ጥምቀት የሚያምን …… ሐይማኖታዊ ስርዓቱ የሚከበርበት or የሚተገበር እምነት ነው!››
‹‹ምንድነው ለየት የሚያደርገው?››
‹‹ያው እኛ አብ፣ ወልድና መንፈስ ቅዱስ አንድ ናቸው ብለን እናምለን፡፡ like ስላሴ አንድም ሶስትም በሚባለው አናምንም! አብ፣ ወልድ መንፈስ ቅዱስ አንድ አምላክ አንድ አካል ብለን እናምናለን፡፡ ሌላው ደግሞ ቀን መርጠን የምናከብረው በዓልም የለም፡፡ plus ስናገባ ቀለበት አናደርግም! እንደምታየው አንገቴና እጄ ላይም ምንም አይነት ጌጣ ጌጥ የለም፡፡ ጆሮዬም አልተበሳም!››
‹‹ኦው ይገርማል ›› አንገቴን በግርምት እየነቀነቅኩ ጆሮዋንና አንገቷን ተመለከትኩ፡፡ ጆሮዋም አልተበሳም፡፡ እጇም ሆነ አንገቷ ላይ ጌጥ የለም፡፡
ወደ ቤተ-መፅሀፍቱ ስንደርስ ከምሽቱ ሁለት ሰዓት አልፎ ነበር፡፡ በሩ ጋር አውርዳኝ ተሰናብታኝ ሄደች፡፡ ወደ ቤተ-መፅሀፍቱ ስገባ አቤላ እየሳቀ ያየኛል፡፡ አንገቴን ሰብሬ ከፊትለፊቱ ተቀመጥኩ፡፡ ትንሽ ማንበብ ፈልጌያለሁ፡፡ መፅሀፌን ከፍቼ ንባቤ ላይ ሰመጥኩ፡፡ አቤላ በየመሀሉ እየሳቀ ይመለከተኛል፡፡ ሶስት ሰዓት ተኩል ሊሆን ሲል አብዱኬ መጣ፡፡ ከቤተ-መፅሀፍቱ እየወጣን አቤላ የአብዱኬን ትከሻ እየነቀነቀ ‹‹አባቴ ኢቦ ማህሌትን አፈፍ አድርጎልሻል!›› አለው፡፡
‹‹አቤላ ደሞ ምንሼ ነው? ነገር አብርድ እንጂ! ሰላማዊ ግንኙነት ነው ያለን!››
‹‹እሱ ጦርነት ነው አላለ!›› አብዱኬ ጣልቃ ገባ፡፡
‹‹ታውቂያለሽ አብዱኬ ሲዞሩ አምሽተው አሁን ነው ላይብረሪ የገባው! የት እንደነበሩ እንኳን ምንም አልነገረኝም!››
‹‹ላይብረሪ ስለነበርን ነዋ! ካፌ ነበርን በቃ ስናወራ ምናምን! ምንም አዲስ ነገር የለውም!››
‹‹ለምን አቤላን ትታችሁት ሄዳችሁ?››
መመለስ አልቻልኩም፡፡ ዝም ስል ሁለቱም ጮክ ብለው ሳቁ፡፡
ከአቤላ ጋር ተለያይተን ወደ ቤት ሄድን፡፡ ኢንቱዬና እማዬ መምጣታችንን በጉጉት ሲጠብቁ ነበር፡፡ ከሌላ ጊዜው ትንሽ አርፍደናል፡፡
የቀረበው እ
966 views07:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 10:54:28 ከተራራው ላይ
ክፍል ዘጠኝ
(ፉአድ ሙና)
.
‹‹የእኔ የፍራሽ መንገድ፣ ሚስጥር የደስታዬ፣
አፈር ስር ያለኸው፣ እንዴት ነህ አባዬ!
‘ምነግርህ ነበረኝ!››
.
ኢንቱዬ በምግቡ ጥፍጥና በጣም ተገርማለች፡፡ የማህሌትን ደግነት ደግሞ በጣም ወዳዋለች፡፡
‹‹መጠጥ ምናምን አልነበረም?›› አለችኝ ኢንቱ!
‹‹ውሀ እና ለስላሳ ብቻ! መጠጥ ሙዳቸው አይመስለኝም …… አልነበረም፡፡››
‹‹ለማጥናት ብቻ ነው ማለት ነው አላማቸው! ድሮ እኮ እኛ በጥናት ሰበብ እየዞርን ፓሪ ነበር የምናደርገው! …… ብቻ ግን ረጋ ያሉ ልጆች ይመስላሉ!›› ፈገግ አለች፡፡
አብዱኬ ወደ ቤት እንደሄደ መኝታችንን አነጣጠፍኩ፡፡ ኢንቱዬ የማስታወሻ ደብተሯን ማገላበጥ ጀመረች፡፡ አተኩሬ ሳያት አስቀምጣው ልብሷን አወላልቃ ብርድልብሱ ውስጥ ገባች፡፡ እጇን ፀጉሬ ላይ እያንሸራሸረች እንቅልፍ ይዞኝ ጠፋ፡፡
ጠዋት አብዱኬ መጥቶ ቁርስ እየበላን ‹‹ኢንቱዬ ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ እኮ ትምህርት ቤት አንሄድም! ይዘጋል፡፡›› አልኳት፡፡
‹‹ጨርሳችሁ ነው?››
‹‹አዎ! ከዚህ በኋላ የምንሄደው ለፈተና ምናምን ነው!››
‹‹እና ጥናት እየጨረስክ ነው? ፈተናው ደርሷል ማለት ነው አይደል?››
‹‹አዎ …… ትንሽ ነው የቀረኝ ብዙውን ሸፍኛለሁ፡፡››
ቁርስ በልቼ እንደጨረስኩ ቦርሳዬን ላነሳ ስል ኢንቱ የምሳ እቃዬን እያቀበለችኝ ‹‹ዛሬ እኔ ስራ አልወጣም …… እናንተ ሂዱ!›› አለች፡፡
ትኩር ብዬ አየኋትና ‹‹ምሳ …… አቤላ ከትናንት የተረፈውን ይዞ ይመጣል …… አያስፈልገኝም!›› አልኳት፡፡
እንደመኮሳተር እያለች ‹‹የማትችልበትን ውሸት አትሞክር ባክህ! …… አሁን አታድክመኝ ይዘህ ውጣ!›› አለች፡፡
‹‹አያስፈልገኝም ኢንቱ! ለእናንተ ይቀመጥ!››
‹‹እኛ የለንም አልንህ እንዴ!?›› ተቆጣች፡፡
‹‹በቃ ኢንቱ ተይው!›› አብዱኬ ጣልቃ ገባ!
ኢንቱ ማልቀስ ጀመረች፡፡ አቀፍኳት፡፡ እቅፌ ውስጥ ሆና መንሰቅሰቋን ቀጠለች፡፡
‹‹ኢንቱዬ …… እስከመች ድረስ ሁሉንም ነገር ብቻሽን አፍነሽ ትይዥዋለሽ? …… እኔ እኮ ልጅ አይደለሁም! ሁሉም ይገባኛል፡፡ ትምህርቴ ላይ ተፅዕኖ እንዳይፈጥር ሰግተሽ ሊሆን ይችላል፡፡ ግን አሁን ትልቅ ልጅ ነኝ! ማወቄ ብርታት ነው የሚሆነኝ! እልህ እንዲይዘኝ ይረዳኛል!››
እንባዋን እየጠራረገች ‹‹በቃ ሁሉንም ማታ እነግርሀለሁ፡፡ አሁን ግን ምሳውን ይዘህ ሂድ!›› አለችኝ፡፡ አብዱኬ እሺ እንድላት በአይኑ ጠቀሰኝ፡፡ የምሳ ዕቃውን ቦርሳዬ ውስጥ ከትቼ እማዬና ኢንቱን ሳምኩና ከአብዱኬ ጋር ቤቱን ለቅቀን ወጣን፡፡
ሰፈራችንን ለቅቀን ወደ ባጃጅ ተራ እየወጣን ‹‹ስሚማ ……›› አለ አብዱኬ ‹‹ቅድም ለመማር እልህ ያስይዘኛል ምናምን ያልሽው ለማስመጥ ነዋ? እንጂ ሀሳብሽን አልቀየርሽም አይደል?››
‹‹አዎ …… ለጊዜው እንድትረጋጋ ብዬ ነው፡፡››
‹‹የሰጠሁሽን ስልክ ግን እያሳየሽው ነው? እስካሁን ጆካ የጣለባት አልገጠመሽም?››
‹‹ላይብረሪ ለአንዳንድ ልጆች አሳይቻቸው ነበር፡፡ አቤላም ማታ ተቀብሎኝ ለልጆቹ ሲያሳያቸው ነበር! ግን እስካሁን ያመረረበት የለም፡፡››
‹‹ባክሽ ልጆቹ ጨላውን ቶሎ ይፈልጉታል፡፡ ተፍ ተፍ ብትይ አሪፍ ነበር፡፡››
‹‹እስኪ እሞክራለሁ፡፡››
ከአብዱኬ ጋር ተለያይተን ትምህርት ቤት እንደገባሁ ከኢንቱ ማስታወሻ ላይ ያላነነብኳቸውን ጥቂት ገፆች ለመጨረስ ስልኩን ከፍቼ ጠረጴዛ ላይ ተደፍቼ ማንበብ ጀመርኩ፡፡
‹‹ኢቦዬ …… ምግብ የሚባል ነገር ለአይኔ እያስጠላኝ ነው፡፡ አሁን ያለኝ ጥቂት ብር ነው፡፡ ያለው ብር ለተጨማሪ ጊዜ እንዲበረክት ከትናንት ወዲያ ጀምሮ ሰበብ እየፈጠርኩ እራት ከእናንተ ጋር መብላት አቁሜያለሁ፡፡ ቁርስ በበላሁት ቀኑን መዋልና ማደር አያቅተኝም ብዬ አስባለሁ፡፡ ምናልባት ጥቂት ተጨማሪ ቀናትን እንዳትራቡብኝ ማድረግ ብችል ብዬ እመኛለሁ፡፡››
አብዱኬ ምግብ አልበላም ያለችበትን ምክንያት ያለአንዳች ስህተት ነግሮኝ ነበር፡፡ ስክሪኑን ገለጥኩ፡፡
‹‹ኢቦዬ …… አባዬ ናፈቀኝ፡፡ እንዳሻኝ እያበላ፣ የፈለግኩትን እያለበሰ፣ ከጓደኞቼ እኩል አንቀባርሮ …… ምንም ሳያጓድል የሚያስፈልገኝን ሁሉ ያለጭንቀት ያሟላልኝ የነበረው አባቴ ናፈቀኝ፡፡ ኢቦዬ …… ስበሳጭ ደረቱን እየደበደብኩ የምነጫነጭበት አባ ናፈቀኝ፡፡ ለበዓል ልብስ የሚገዛልኝ …… የሚያንሸራሽረኝ መከታዬ ናፈቀኝ፡፡ ሰው ሲያስቸግረኝ ለአባዬ እናገራለሁ እያልኩ የማስፈራራበት አባቴ ንፍቅ አለኝ፡፡ ዛሬ እንደዚህ መራቤን ያውቅ ይሆን? ረሀብን ለአባዬ እናገርልሀለሁ ብለው ይተወኛል? ራበኝ እኮ! ጨጓራዬ ነደደ እኮ ኢቦዬ! አባቴ መቃብሩ ውስጥ ሆኖ ስቃዬን አይቶ እያለቀሰ ይሆናል እንዴ? ኢቦዬ የምበላው እንኳን አጣሁ! ለማን ልናገር? ማንን ድረሱልኝ ልበል? አባት ያላቸው ግን እንዴት ታድለዋል? ቢርባቸው አባዬ ራበን ብለው አባታቸው ላይ ማልቀስ ይችላሉ አይደል? እኔ ማን ላይ ላልቅስ? እኔ ማን ላይ ልነጫነጭ? ላንተ እንዳልነግርህ ትረበሻለህ! ለእማዬ እንዳልነግራት ደግሞ በበሽታዋ ላይ ሌላ በሽታ መደረብ ይሆናል፡፡ ዛሬ መንገድ ላይ የትራንስፖርት ላለማውጣት በእግሬ እየሄድኩ መራመድ አቅቶኝ የእግረኛ መንገዱ ላይ ምሰሶ ተደግፌ ድንዝዝ ብዬ ተቀመጥኩ፡፡ ሰዉ ከብቦ ሲያየኝ …… ውሀ ሊያጠጡኝ ሲሞክሩ ምናለ በሞትኩ ብዬ ተመኘሁ፡፡ እዛ ቢያንስ አባዬ አለ አይደል? ለእሱ ሁሉንም እነግረው ነበር ብዬ አሰብኩ፡፡ ራስ ወዳድ ሆኜ አይደለም እኮ ኢቦዬ …… ግን ከበደኝ! ከአቅሜ በላይ ሆነ!››
እንባዬ ፊቴን አርሶት ንፍጤ እየተዝረበረበ ነበር፡፡ ሳላስበው ድምፅ አውጥቼ መንሰቅሰቅ ጀመርኩ፡፡
‹‹ኢብሮ …… ምን ሆንክ?›› ከጀርባዬ አንዲት ሴት ስትነቀንቀኝ ተሰማኝ፡፡ የክላስ ልጅ ነበረች፡፡ ፊቴን ጠራርጌ እንደምንም ራሴን ካረጋጋሁ በኋላ ‹‹ምንም አልሆንኩም …… ምንም አልሆንኩም!›› ብዬ መለስኩ፡፡ የኢንቱ አፈጣጠር ገረመኝ፡፡ ቀጣዩን ፎቶ ከፍቼ ንባቤን ቀጠልኩ፡፡
‹‹ኢቦዬ …… እጄ ላይ የነበረው ገንዘብ አልቋል፡፡ ስራም ላገኝ አልቻልኩም፡፡ ዛሬ አብዱኬ ትንሽ ገንዘብ ሰጠኝ፡፡ አብዱኬ የልጅ አዋቂ ነው፡፡ ሁሌም ችግሬን ሳልነግረው ይረዳል፡፡ ማታ ሰላጣ ይዞ ባይመጣ ኖሮ በረሀብ የምሞት ይመስለኛል፡፡ አንዳንዴ አብዱኬም ሆኑ ጋሼ እኛን እንዲጠብቁ የተመደቡ መልዓክት ሳይሆኑ አይቀሩም ብዬ አስባለሁ፡፡ ብቻ ግን አሁን ላይ ምንን ተስፋ ማድረግ እንዳለብኝ ግራ ገብቶኛል፡፡ ወዴት መሸሽ እንዳለብኝ አላውቅም! ለእናንተ መኖር አለብኝ! እናንተም መኖር አለባችሁ፡፡››
እኔ ፎቶ ሳነሳው የማስታወሻ ደብተሯ ላይ ተፅፎ የነበረውን የመጨረሻ ጽሁፍ ከፍቼ ማንበብ ጀመርኩ፡፡
‹‹ኢቦዬ …… ረሀብ ከባድ ነው! ማጣት ከባድ ነው! የሰው እጅ ማየት ከባድ ነው! ረሀብ ህሊናህን ያስሸጥሀል፡፡ ለእናቴም ላንተም መትረፍ አለብኝ፡፡ እማዬ በሽተኛ ሆና መራብ የለባትም፡፡ የቻልኩትን ሁሉ ማድረግ አለብኝ! ባልወደውም …… ባልፈቅደውም!››
ከትምህርት መልስ ቀጥታ ወደ ቤት ለመሄድ አሰብኩ፡፡ ያለሰዓቴ ከሄድኩ ደግሞ ለምን አላጠናህም ብላ ትበሳጭና አልነግርህም ትለኛለች ብዬ ስለፈራሁ ሀሳቤን አጠፍኩ፡፡ ከአቤላ ጋር ወደ ቤተል ቤተ-መፅሀፍት ስንደርስ ከኋላችን ማህሌት በመኪናዋ ክላክስ ጠራችን፡፡ ከመኪናዋ ወርዳ ሞቅ ያለ ሰላምታ ተለዋወጥን፡፡ የለበሰችው ሙሉ ብርትኳናማ ቀሚስ ነበር፡፡ በጣም አምሮባታል፡፡
‹‹ሰሞኑን ክላስ የለም እንዴ?›› በጊዜ ቤተ-መፅሀፍቱ አካባቢ መምጣቷ ገርሞኛል፡፡
‹‹ተዘጋልን እኮ! Last week ጨረስን!››
‹‹ቀድማችሁናላ! እና ምን እየሰራሽ ነው መኪና
827 views07:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 04:40:04 ሽ እኮ ያበላሽኝ!››
‹‹እኔና አንተን ማን አስተዋወቀን?››
‹‹አንቺ!››
እየሳቀች መኪናውን አቆመችው፡፡ አለምባንክ ደርሰን ነበር፡፡ እያመሰገንኩ እቅፍ አድርጌ ሳምኳት፡፡ አቤላ ቦርሳዬንና የተቋጠረልኝን ምግብ አቀበለኝ፡፡ ለአቤላም አስቋጥራለታለች፡፡ አብዱኬ መጥቶ ሰላም አላቸው፡፡ ማህሌት አቤላን ይዛ ወደ ቤተል አቅጣጫ ተመለሰች፡፡
አብዱኬ ምግቡ የተቋጠረበትን ፌስታል ከፍቶ እያየ በግርምት ይመለከተኛል፡፡ እየሳቀ ‹‹አባቴ ስራ ጀምሪ ስልሽ ከሚቀልሽ ጀመርሽ ማለት ነው?›› አለ፡፡
‹‹ባክህ እነሱ ቤት አጥንተን ነው!››
‹‹እና ምግቡን ስንተኛ ወጥተሽ ነው የሸለሙሽ?››
ውሎዬን እዘከዝክለት ጀመር፡፡ ስለቤታቸው፣ ስለአባቷ፣ ስለሻወራቸው አንድም ሳላስቀር ተረኩለት፡፡ ባጃጅ ተራ ስንደርስ ኢንቱ ጋር ደወልን፡፡ ቤት ገብታ ነበር፡፡ ወደ ቤት አቀናን፡፡ ከአብዱኬ ጋር ቤት ገብተን ያመጣሁትን ምግብ ከእማዬና ከኢንቱ ጋር በአንድነት በላን፡፡
.
ይቀጥላል …
178 views01:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 04:39:33 ከተራራው ላይ
ክፍል ስምንት
(ፉአድ ሙና)
.
‹‹አንተ …. የሚጮህ ሆዴ የማይሰማህ፣ አውቆ ደንቋሪ፣
ዘንበልታዬ የማያመልጥህ፣ ስህተት ቆጣሪ፤
አክስሞ አዳሪ!››
.
ሰኞ ጠዋቱን አብዱኬ መጥቶ አብረን ቁርስ በላን፡፡ ኢንቱዬ እንጀራውንም ፍራፍሬውንም በደንብ በላች፡፡ አብዱኬም፣ እኔም፣ እማዬም በጣም ደስ ብሎናል፡፡ ከቁርሱ በኋላ ሶስታችን እማዬን ተሰናብተን ተያይዘን ወጣን፡፡ ኢንቱዬን ከአለምባንክ ታክሲ አስይዘናት አብዱኬም ወደ ቤተል እኔም ወደ አየርጤና ሄድን፡፡ ትምህርት ቤት እንደገባሁ የመማሪያ ዴክሳችን ላይ ተቀምጬ ከስልኩ ላይ የኢንቱን ማስታወሻ ማንበብ ጀመርኩ፡፡
‹‹ኢቦዬ …… ደስታ ለምን እንደማይበረክትልኝ አላውቅም! ለምን ሰዎች መጥፎነታቸው እኔ ላይ እንደሚበረታ ግራ ይገባኛል፡፡ ለካ ለአንዳንድ ሰው ደካማ ጎንህን ማሳየት የለብህም፡፡ አሰሪዬ የእማን መታመም ካወቀ በኋላ ያሻውን እንዳደርግለት ውትወታው ላይ በርትቶ ነበር፡፡ ፊት አልሰጥ ስለው ጫና ለማሳደር አስቦ መሰለኝ ዛሬ አስር ቀን የሰራሁበትን አንድ ሺህ ብር ሰጥቶ አባረረኝ፡፡ በጣም ለምኜው ነበር፡፡ ግን ከሴቶቹ ጋር ተስማምተሸ መስራት አልቻልሽም ስራ እያበላሸሽብኝ ነው ምናምን ብሎ ሰበብ አቀረበ፡፡ ምክንያቱ እሱ እንዳልሆነ እኔም እሱም በደንብ እናውቃለን፡፡ ጊዜ ባለስልጣን አድርጎታል …… እኔ ምንም አቅም የለኝም፡፡ ስራ ማግኘት ደግሞ መከራ ነው፡፡ ባለፈው በተቀበልኩት አስር ሺህ ብር እማዬ እንድትታይ የግል ሆስፒታል ወስጃት ነበር፡፡ ካንሰሩ ሙሉ ሰውነቷ ውስጥ ስለተሰራጨ በሌሎች የህክምና መንገዶች መቆጣጠር እንደማይቻል ነግረውኝ ከረዳት በሚል አንዳንድ መድሀኒቶችን አዘውላት ነበር፡፡ ለህክምናውና ለመድሀኒቱ ከአምስት ሺህ ብር በላይ አጥፍቻለሁ፡፡ አሁን እጄ ላይ ያለው ብር ካለፈው ደሞዜ ከተረፈው ጋር ተደምሮ ስምንት ሺህ ብር አይሞላም፡፡ ስራ እስከማገኝ ገንዘቡን ልቆጥበው ወይስ ለእማዬ ጥሩ ጥሩ ምግብ ላቅርብበት የሚለው ግራ ግብት ብሎኛል፡፡ እማዬን አብልቼበት ስራ ሳላገኝ ብሩ ቢያልቅ አንተ ምን ትሆናለህ የሚለውን እያሰብኩ መወሰን ከበደኝ፡፡ በዚያ ላይ ደግሞ የቤት ኪራይም አለ፡፡ አባት ቢኖረን ግን ጥሩ ነበር አይደል?››
አይኔ እንባ አቀረረ፡፡ ኢንቱ ወደ ቤት በጊዜ የምትመለስባቸውን ቀናትና እረፍት ወጣሁ ብላ ከስራ የቀረችበትን ቀን እያስታወስኩ እቆዝማለሁ፡፡ አይኔን አባብሼ ወደ ንባቤ ተመለስኩ፡፡
‹‹ኢቦዬ …… የእማዬ መሞት እንደሆነ የማይቀር ጉዳይ ነው፡፡ አንዳንዴ አንተ ሳትኖር ይዣት እየወጣሁ ደህና ምግብ እንድትበላ ለማድረግ እየሞከርኩ ነበር፡፡ ግን ደግሞ ከቀን ወደ ቀን እጄ ላይ ያለው ገንዘብ እያነሰብኝ ስራ ሳላገኝ ሊያልቅብኝ ነው ብዬ ፈራሁ፡፡ በቻልኩት አቅም ለትራንስፖርትና ለምግብ የማወጣውን ወጪ እየቆጠብኩ ነው፡፡ የቻልኩትን ያህል በእግሬ እሄዳለሁ፡፡ ምግብም ቁርስ ከናንተ ጋር ከቀመስኩ ቀኑን ሙሉ ሳልበላ እውላለሁ፡፡ ወጪ ለመቀነስ ቤት ብቀመጥ ደስ ይለኝ ነበር፡፡ ግን ደግሞ ስራ መፈለግ አለብኝ፡፡ በዚህ በኩል ደግሞ አንተ ካወቅክ ትረበሽብኛለህ ብዬ እሰጋለሁ፡፡ ሰሞኑን አንተ ስራ ማቆሜን እንዳታውቅብኝ ስል ጠዋት እየወጣሁ ያስሚን የምትሰራበት ሱቅ ከእሷ ጋር ጊዜዬን አሳልፋለሁ፡፡ በሰው በሰው ስራ ለመፈለግ እየሞከርኩ ነው ግን ሁሉም ተያዥ ይፈልጋሉ፡፡ የመንግስት ደሞዝተኛ የሆነ ተያዥ! የግል ተቀጣሪም ቢሆን ደህና ደመወዝ ያለው ተያዥ ይፈልጋሉ፡፡ እኔ ደግሞ የለኝም፡፡ አሁን ወዴት እንደምሄድ ግራ ገብቶኛል፡፡››
ቀጣዩን ለማንበብ የስልኩን ስክሪን ዳሰስኩ፡፡ ከሳምንታት በኋላ የፃፈችው ነበር፡፡
‹‹ኢቦዬ …… ስራም ጠፋ! እጄ ላይ ያለውም ብር እያለቀ ነው፡፡ ባለፈው አስር ሺህ ብር የሰጠኝን ቦስ ልጠይቀው አስቤ አፈርኩ፡፡ ሱቁ አልተከፈተለትም፡፡ የባንክ አካውንቱም እንዳይንቀሳቀስ ታግዷል ሲባል ሰምቻለሁ፡፡ ከብላክ ማርኬት ጋር በተያያዘ መሰለኝ …… ብቻ እሱንም በቅርቡ መልሰው ሳያስሩት አይቀሩም፡፡ ያስሚኔ ስጨናነቅ አይታ እሰኪ ካረጋጋን በሚል አመሻሹን እንደተዘጋጀ ወደሰማችው አንድ ኢስላማዊ መድረክ እንድንሄድ ጠየቀችኝ፡፡ እኔ የትራንስፖርት ፒያሳ ድረስ ማውጣት እንደማልችል ነገርኳት፡፡ እሷ እንደምትከፍልልኝ ተነጋግረን ሄድን፡፡ እሷም ገንዘብ ኖሯት ሳይሆን ያለሁበትን ጭንቀት ተረድታ ነበር፡፡ ወደ አዳራሹ ስንጠጋ ገና መግቢያው ጋር ትኬት የያዙ ልጆች ቆመው ይቆርጣሉ፡፡ ለመስጂድ ማሰሪያ እርዳታ እየጠየቁ ነበር የመሰለኝ! ልክ ልንገባ ስንል የመግቢያ ክፍያ መቶ መቶ ብር እንድንከፍል ጠየቁን፡፡ ተያየንና ምንም ሳንናገር ዞረን ተመለስን፡፡ ነገሮች በጣም መቀያየራቸው ገባኝ፡፡ እኔ በገንዘብ የሚገባ ሀይማኖታዊ ዝግጅት ሰምቼም አይቼም አላውቅም፡፡ ሀይማኖትም የሀብታሞች እየሆነ ነው ማለት ነው? በጣም ገረመኝ፡፡ ድሮ እኮ ሰው እንዲገኝ ሰደቃ ተብሎ እንኳን ከፍሎ ሊገባ ቀርቶ በነፃ ሆዱን ሞልቶ ይመለስ ነበር፡፡ ነገሮች እንዴት በፍጥነት እየተቀየሩ እንደሆነ ታዘብኩኝ፡፡››
ወደ ሰልፍ እንድንወጣ የሚጠይቀው ደወል ተደወለ፡፡ ስልኬን ኪሴ ውስጥ አስገብቼ ወደ ሰልፍ ሜዳው ወጣሁ፡፡ በጊዜ የምንገባው ተማሪዎች ብዙም አይደለንም፡፡ ተሰልፈን የትምህርት ቤቱ ዳይሬክተር በማይክ መናገር ጀመረ፡፡
‹‹ … የአስራሁለተኛ ክፍል ተማሪዎች ያላሟላችኋቸው ውጤቶች ካሉ በዚህ ሳምንት ከመምህራኖቻችሁ ጋር በመነጋገር እንድታሟሉ፡፡ ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ ትምህርት ስለማይኖራችሁ ጊዜያችሁን በአግባቡ ተጠቅማችሁ እንድታጠኑ፡፡ … በተረፈ ለሞዴል እንገናኝ!››
የሰልፉ ስነ ስርዓት እንዳለቀ አቤላ ወደ ክላስ መጣ፡፡ አቤል ሰልፍ መሰለፍ በጣም ይጠላል፡፡ ክላስ አብረን ተቀምጠን አስተማሪ ስላልገባ አንዳንድ ጥያቄዎችን መስራት ጀመርን፡፡ አብረውን መስራት የፈለጉ የክላስ ልጆች ከበቡን፡፡ ብዙዎቹ ሴቶች ነበሩ፡፡ ጥያቄውን እየሰራን ማህሌት አጭር የፅሁፍ መልዕክት ላከችልኝ፡፡
‹‹hey አብርሽዬ how you doing? ዛሬ ላይብረሪ ብትመጣ ደስ ይለኛል፡፡ study circle አስበናል እና please come! If not let me know!›› ይላል፡፡
‹‹ደህና ነኝ! አንቺ እንዴት ነሽ? ችግር የለውም እመጣለሁ!›› ብዬ መለስኩላት፡፡
ቀኑ ገፍቶ ወደ ቤት እንድንሄድ የሚፈቅደው ደወል ተደወለ፡፡ እኔና አቤላ ቦርሳችንን ይዘን ግቢውን ለቅቀን መውጣት ጀመርን፡፡ ከፊት ለፊታችን አንድ ሀይማኖተኛ ሀይማኖተኛ የሚሰራራው ልጅ መጣ፡፡ ሰላምታ እንኳን ሳይሰጠን መለፍለፍ ጀመረ፡፡
‹‹አንተ ኢብራሂም ግን አላህን አትፈራም?! በሴቶች ተከበህ ስትተሻሽ ሀራም መሆኑን አታውቅምና ነው! ጠዋት ክፍል ውስጥ ያላየውህ መስሎሀል? ደሞ ሰላት ለምንድነው የማትሰግደው? አላህ ጀሀነም እንደሚከትህ አታውቅም?›› ልጁ እየተከተለን ይጮኻል፡፡ ከትምህርት ቤቱ በር እንደወጣን አንድ የክፍላችንን ልጅ አየሁ፡፡ ሌላ ጊዜ በስርዓቱ ሰላም እንኳን ብያት አላውቅም፡፡ ጠራኋትና ጉንጯን ስሜ ጭምቅ አድርጌ እቅፍ አደረግኳት፡፡ አቤል ይስቃል፡፡ ልጁ ይለፈልፋል፡፡ እሷ ግራ ተጋብታለች፡፡
‹‹አላህን ፍሩ ሲባሉ ኩራታቸው የበለጠ ወደ ወንጀል ይገፋፋቸዋል የተባለው ለእንዳንተ አይነቱ ነው፡፡ ቀብር ውስጥ ስትገባ ሴት ‘ሚመጣልህ መስሎሀል? የትል መጫወቻ ነው የምትሆነው! አትንጠባረር!››
ትዕግስቴ ሙጥጥ ብሎ ሲያልቅ ተሰማኝ፡፡ ከእንደዚህ አይነቱ ሰው ጋር መነጋገር አልወድም ግን ራሴን መቆጣጠር ከበደኝ፡፡
‹‹አንተ ፃድቅ ነህ በቃ!? ስለእኔ ከስሜ በቀር ምን የምታውቀው ነገር
185 views01:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 08:25:38 ነበር አንቺ ግን አልገባሽም! ኢቦ ኢንቱ ያንተ ብቻ ሳትሆን የእኔም እህት ናት፡፡ አብረን ነው ያደግነው፡፡ ሌላ እህት የለኝም፡፡ ሁሌም ስራ እንድትጀምር የምወተውትህ ለዛ ነበር፡፡ ከዚህ በኋላ ጊዜ አታጥፋ! ፈተናውን ተፈተን፡፡ ከዛ በኋላ ግን ቤቱን ተረከብ፡፡ እስከዛ የሚያስፈልግህ ነገር ካለ እኔ አለሁ፡፡››
ከዚህ በፊት የተፈጠሩ ነገሮችን በአዕምሮዬ ለመዳሰስ ሞከርኩ፡፡ ደደብ እንደሆንኩ ተሰማኝ፡፡ የእህቴን ህመም እንኳን በቅጡ መረዳት የተሳነኝ ገልቱ! በራሴ አፈርኩ፡፡ አብዱኬን ጋሼ ከኛ ቤት ሲወጡ ስለጠሩት ከእሳቸው ጋር ሄደ፡፡ ድንጋዩ ላይ እንደተቀመጥኩ በምትሸጠዋ ስልክ ያነሳኋቸውን ገፆች ማንበብ ጀመርኩ፡፡
‹‹ኢቦዬ …… ጨንቆኛል፡፡የእማዬ ነገር ከአቅሜ በላይ ሆኗል፡፡ ቢያንስ የተሻለ ምግብ መብላት አለባት፡፡ መሞቷ ባይቀር እንኳን ጥቂት ቀናት ብናያት ብዬ እመኛለሁ፡፡ ቀኑ የደረሰ የደረሰ እየመሰለኝ እፈራለሁ፡፡ አዎ አሁን አሁን በጣም ፍርሀት ፍርሀት ይለኝ ጀምሯል፡፡ ምናልባት እናት የሌለው ስለሌለ እናቱን አስቦ ያዝንልኛል ብዬ ለአሰሪዬ ስላለንበት ሁኔታ ነገርኩት፡፡ ኩራቴን ከተውኩ እንደሚረዳኝ ነገረኝ፡፡ ኩራትን መተው ማለት ባሻው ሰዓት እንደፈለገው እንዲያደርገኝ መፍቀድ ማለት ነው፡፡ ክብርን መጠበቅ ለእሱ ኩራት ነው፡፡ ከምሰራበት ሱቅ አጠገብ ካሉ ሱቆች ውስጥ ከቦሶቹ ጋር የምግባባቸውን እየሄድኩ ለመንኳቸው፡፡ ቅድመ መስፈርታቸው ግን ይኸው ነበር፡፡ ለገንዘቡ ችግር የለውም ግን እኛ በምላሹ ምን እናገኛለን ይሉኛል፡፡ ታውቃለህ ቆንጆ ባልሆን ኖሮ ይሰጡኝ ነበር ይሆን? እያልኩ አስባለሁ፡፡ እንዲፈልጉኝ ያደረጋቸው ውበቴ ነው? እና ምን ላድርገው? በምላሹ ምንም ሳይፈልግ ደግ የሚሆን ጠፋ! እንደ አባ ደግ የሚሆንልኝ አጣሁ! ›› ይኼ ንግግሯ ትዝ አለኝ፡፡ አንድ ቀን ማታ ደግ ስሆን በምላሹ ምንም እንዳልፈልግ እያለቀሰች መክራኝ ነበር፡፡ ንባቤን ቀጠልኩ፡፡
‹‹ኢቦዬ ዛሬ ደስ ብሎኛል፡፡ አንድ በቅርቡ በዋስ የተፈታ ሱቁ የታሸገበት ቦስ ነበር እና ዝም ብዬ ስለ እማ ነገርኩት፡፡ ገንዘብ ይሰጠኛል ብዬ ሳይሆን ቢያንስ የምለምነው ሳይሆን ጭንቀቴን የማጋራው ሰው ነው ብዬ የውስጤን ዘረገፍኩለት፡፡ከሰማኝ በኋላ ምንም ሳይናገር ትቶኝ ሄደና ተመልሶ መጣ፡፡ አይዞሽ ብሎ የተጠቀለለ አስር ሺህ ብር ሰጠኝ፡፡ ከኔ ምንም አልፈለገም፡፡ በደግነቱ ተገረምኩ፡፡ ሰው ሁሉ እንደሱ ደግ ሲሆን በምላሹ ምንም ባይፈልግ ብዬ ተመኘሁ፡፡ ኢቦዬ አንተም ደግ ስትሆን በምላሹ ምንም አትፈልግ እሺ! ሊያውም ሱቁ ተዘግቶበት እኮ ነው እንዲህ የሰጠኝ አስበኸዋል? ደስታዬን መቆጣጠር አቅቶኛል፡፡››
ፈገግ አልኩ፡፡ ቢያንስ አንድ እንኳን ጥሩ ሰው ስለገጠማት ደስ አለኝ፡፡ የሰፈራችን ልጅ ሚጣ ከኛ ቤት ኢንቱን ጠይቃ እየወጣች ቤት እየተጠራሁ እንደሆነ ነገረችኝ፡፡ ተነስቼ ወደ ቤት ገባሁ፡፡ ሁሉም ጠያቂዎች ሄደው ነበር፡፡
‹‹የት ጠፋህ?›› አለች ኢንቱ ጀርባዬ ላይ እየተጠመጠመች፡፡
‹‹ሰዉ እስኪወጣ በር ላይ ተቀምጬ ነበር!››
‹‹ኢቦዬ አትኮሳተርብኝ እንጂ …… ያላንተ ማን አለኝ?››
ሳላስበው መንሰቅሰቅ ጀመርኩ፡፡
‹‹እኔስ ማን አለኝና ነው ምግብ ሳትበዪ ልትሞቺ የነበረው?! …… ለእኔ እኮ ከምግብ በላይ የሚያስፈልገኝ ያንቺ መኖር ነው፡፡ …… ሞተሸስ ቢሆን ኢንቱዬ? ሞተሸስ ቢሆን?›› ተንዘፈዘፍኩ፡፡ እማዬ እያየችን ታለቅሳለች፡፡
‹‹ኢቦዬ …… ትረበሽብኛለህ ብዬ ፈራሁ! ከምንም እና ከማንም በላይ እንደምወድህ ታውቅ የለ …… ለዛ ነው! በቃ ከዚህ በኋላ ራሴን እጠብቃለሁ፡፡ በደንብ እበላለሁ፡፡ ይቅርታ አድርግልኝ …… ስወድህ!››
ወደሷ ዞሬ እቅፍ አደረግኳት፡፡ ጭምቅ! ከሞት የተመለሰች የተመለሰች አይነት ስሜት ይሰማኛል፡፡
‹‹ኢንቱዬ ምንም ብታደርጊ እረዳሻለሁ፡፡ ራስሽን ከጎዳሽ ግን ዳግመኛ አታገኚኝም!›› ከእቅፌ አውጥቼ እንባዋን ጠረግኩላትና እጇን ሳምኳት፡፡ ፈገግ አለች፡፡ እማዬ ፈገግ እንዳለች እቅፏን ዘረጋችልን፡፡ ሁለታችንም ወደ ፍራሿ ሄደን ተጠመጠምንባት፡፡ ብዙ ጊዜ እንደምናደርገው እማዬን በኃይል በሳመ መፎካከር ጀመርን፡፡
እማዬ እንባ እያነቃት ‹‹ጌታዬን ብዙ ጊዜ ምነው መከራ አበዛህብን ብዬ አማርሬዋለሁ፡፡ ሁሉም ነገር ከአቅሜ በላይ ሆኖ ጭልም ብሎብኝ ያውቃል፡፡ ባለፍናቸው የመከራ ጊዜያት ሁሉ ብርታት የሆነኝ ግን ልጆቼ ላይ የማየው መተሳሰብና መተዛዘን ነው፡፡ እናንተ ስትተሳሰቡ ሳይ የከበበኝን መከራ ሁሉ ረሳዋለሁ፡፡ አደራችሁን! አሁንም ቢሆን ለኢቦ ካንቺ ውጪ የለም ኢንቲሳሬ! ለእሷም ካንተ ውጪ ማንም የለም፡፡ እንደሌላው ዘመድ እንኳን የላችሁም፡፡ ተዋደዱ! ለጎረቤቶቻችንም ጥሩ ሁኑ፡፡ ማንም ባልነበረን ሰዓት ከጎናችን ሆነው እንባችንን ያበሱት እነሱ ናቸው፡፡›› አለች፡፡
ትንሽ ቆይተን የድሮ ትዝታ እያነሳሳን መሳቅ ጀመርን፡፡
ኢንቱዬ እየሳቀች ‹‹ትዝ ይላችኋል?›› አለች፡፡ ‹‹ትዝ ይላችኋል እዚህ ቤት የገባን አካባቢ ኢቦ ማታ ማታ ማስታጠቢያ ላይ ሽና አትውጣ ሲባል እንቢ ይል ነበር፡፡ አንድ ቀን ካልወጣሁ ብሎ ወጥቶ ጅብ ሲያይ ሽንቱን ልብሱ ላይ ለቅቆት የተመለሰው! ›› እያስታወስኩት እስቃለሁ፡፡
‹‹ልክ ቤት ሲገባ ምን ሆንክ ስንለው መናገር አቅቶት እየተወዛገበ ጅቡ ሸናብኝ ያለንን!›› ኢንቱዬ በሳቅ ፍርስ ትላለች፡፡ እኔና እማዬም ድክም እንላለን፡፡
‹‹ያምሻል እንዴ ያኔ እኮ …… ልክ ዚፔን ልከፍት ስል ከፊት ለፊት አራት ምናምን ይሆናሉ እኮ የነበሩት ጅቦች፡፡ አንቺ ደግሞ አይሀለሁ ብለሽኝ ስዞር የለሽም፡፡ መሽናቴን እንኳን ያወቅኩት እናንተ ስትነግሩኝ ነው፡፡ አሸቀጠጥኩት እኮ የሌለ! ከአሁን አሁን አንዱ ያዘኝ እያልኩ …… ብቻ አለፈ ያም ጊዜ!››
‹‹አሁን ግን ብዙ ሰው እዚህ መኖር ሲጀምር ነው መሰለኝ እንደድሮው እኮ ጅብ አይበዛም አይደል?›› አለች ኢንቱ!
‹‹አሁን የለም ማለት ይቻላል፡፡ ያኔ እኮ ጩኸታቸው ራሱ ማታ ማታ እንዴት ነበር የሚያስፈራው! እኔ ሳልተኛ ያደርኩበት ቀን አለ፡፡ አልረሳውም፡፡›› አለች እማዬ!
‹‹ከኢንቱዬ ጋር ውሀ ልታመጡ ቦኖ ሄዳችሁ ……… ወረፋ አልደርስ ብሏችሁ ቀኑን ሙሉ ውላችሁ፤ ከዛ ውሀውን ይዛችሁ ስትመጡ የኢንቱ ማዘያ ተቀዶ ጀሪካኑ እየተከረባበተ ወደታች ወርዶ ውሀው እንዳለ ፈሶባችሁ የኢቦን አስር ሊትር ጀሪካን ብቻ ይዛችሁ የተመለሳችሁበትስ?!›› ሳቀች፡፡
‹‹ውይ እማ እሱን ቀንማ አታስታውሺኝ! እንዴት እንደተቃጠልኩ እኮ በአላህ! ማዘያዬ ተርርር ይላል ጀሪካኑ እየተገለባበጠ በቃ ቦኖው ጋ ደረሰ በይው እኮ! ኢቦም እንዳይሮጥ የእሱም ሊደፋ ሆነበት፡፡ ጀሪካኖቹን ደግሞ በፌስታል ነበር የምንከድናቸው ክዳን አልነበራቸውም፡፡››
ትዝታችንን እየተጨዋወትን የእራት ሰዓት ስለደረሰ ያለውን አቀራረብኩ፡፡ ኢንቱዬ የመጡላትን ፍራፍሬ እና ጁሶች አቀረበች፡፡ እየተጨዋወትን በልተን መኝታችንን አነጣጥፈን ተኛን፡፡ ኢንቱዬ እንቅልፍ እንደወሰዳት እርግጠኛ ስሆን የማስታወሻ ደብተሯን መፀሀፌ ውስጥ አስገብቼ ያላነበብኳቸውን ገፆች በሙሉ ፎቶ አነሳኋቸው፡፡
.
ይቀጥላል …
32 views05:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 08:25:11 ከተራራው ላይ
ክፍል ሰባት
(ፉአድ ሙና)
.
‹‹ቢርበው ሆዴን ነው፣ ደግሞም ብርቄ አይደለ፣
ተጎድተሽ ሳይሽ ነው፣ ውስጤ የቆሰለ፡፡
አይዞኝ የኔ ሚስኪን!››
.
ፍራሹ ላይ የተጋደመችውን ውዷ እህቴን በስስት እያየሁ ቀጣዩን ክፍል ማንበብ ጀመርኩ፡፡
‹‹ኢቦዬ የእማዬ ሁኔታ ከቀን ወደ ቀን እየከፋ እየመጣ ነው፡፡ እኔ ደግሞ የስራ ቦታውን ጫና መቋቋም እየታከተኝ ነው፡፡ የሴቶቹ ተንኮል …… የአለቃዬ ጉንተላ ብቻ ምን ልበልህ ጭንቀት ሆኖብኛል፡፡ ሴቶቹ ለአለቃዬ ደንበኛ ወደእሷ አንልክም እያሉት እንዲያባረኝ እየወተወቱት ነው፡፡ በዚህ በኩል ደግሞ እሱ አብሬው እንድተኛ የማያቀርብልኝ መደለያ የለም፡፡ አሁን ከስራ ማባረሩን እንደማስፈራሪያ መጠቀም ጀምሯል፡፡ እኔ ደካማ ነኝ …… አቅም የለኝም፡፡ ዛሬ እሱ ቢያባረኝ ያለ ተያዥ ሌላ ቦታ ስራ ለማግኘት መከራ ነው፡፡ መቻል አለብኝ ብዬ አስባለሁ ግን ደግሞ ከበደኝ፡፡ ከዚህ በኋላ የቀድሞዋን ኢንቲሳር ሆኜ መቀጠል የምችል አይመስለኝም፡፡ አዎን ኢቦዬ …… ያቺ ኢንቲሳር እየሞተች ነው፡፡››
የእንባ ዘለላዎች ከአይኔ ቅጥር እየተሸቀዳደሙ ይወጣሉ፡፡ እንባዬን እያበስኩ ኢንቱዬን በስስት ተመለከትኳት፡፡ አሁን የእኔ ተራ እንደሆነ ተሰማኝ፡፡ ከዚህ በኋላ በኢንቱ የማሳብብበት ምክንያት ያለኝ አይመስለኝም፡፡ ህልሟን ላሳካ ካልኩ ያሰበችው ቦታ ብደርስ እንኳን ሳታየኝ መሞቷ ነው፡፡ ከዚህ በኋላ ኢንቱ በእኔም ሆነ በእርሷ ህይወት ላይ መወሰን ማቆም ይኖርባታል፡፡ ሀሳቧ መልካም ነበር ግን ደግሞ በእኛ ሁኔታ የሚሳካ አይመስለኝም፡፡ አብዱኬ ልክ ነበር፡፡ ልረዳት ይገባል! ባትፈልግም እንኳን ግድ ይለኛል፡፡
አቀርቅሬ ከራሴ ጋር ስከራከር ረዘም ያለ ጊዜ ካሳለፍኩ በኋላ አብዱኬ መጣ፡፡ ቀስ ብሎ ከጎኔ ተቀመጠ፡፡
‹‹ስራ መውጣቱን ተውከው እንዴ?››
‹‹ባክህ አንደኛውን ነገ እወጣለሁ! እንዴት ሆነች ኢንቱ ቅድም ከተኛች እስካሁን አልተነሳችም እንዴ?››
‹‹አዎ የብዙ ቀን እንቅልፍ ሳይኖርባት አይቀርም!››
እጄን ይዞ እንድንወጣ እየጠቆመ ጎተተኝ፡፡ ተከታትለን ወጣን፡፡ ከቤታችን ትንሽ ሸሸት ብለን ቀጭኑ መተላለፊያ ላይ ያለች ድንጋይ ላይ ተቀመጥን፡፡
አብዱኬ ፊቴን በአይኑ እየሰለለ ‹‹ምን አሰብክ?›› አለኝ፡፡
‹‹ስለምኑ?››
‹‹ስለሆነው ነገር ምናምን!››
ጥያቄው ግልፅ አልሆነልኝም፡፡ ዝም ብዬ እመለከተው ጀመር፡፡
በረዥሙ ተነፈሰና መሬቱን በእንጨት እየጫረ መናገር ጀመረ፡፡
‹‹ታውቂያለሽ ኢቦ …… ብዙ ጊዜ በዚህ መልኩ ላወራሽ እፈልግና የኢንቱንም የአንቺንም ሙድ ላለመከነት እያልኩ እተወዋለሁ፡፡ አሁን ግን ልነግርሽ ይገባል፡፡ ህይወት ትምሮ ቤት ተምሮ እንደመመለስ ቀላል አይደለችም፡፡ የህይወትን እውነተኛ ገፅታ የምትረዳው ኑሮን ለማሸነፍ ግብግብ መግጠም ስትጀምር ነው፡፡ አየህ አሁን እኔ ተፍ ተፍ ብዬ ቤት ስለምደግፋቸው ያሉበትን እፎይታ እኔ ነኝ የማውቀው! እንዳንተ ጎበዝ ባልሆንም መማር ግን እችል ነበር፡፡ ከቤተሰቤ የኑሮ ደረጃ አንፃር ግን ገና ከመሰረቱ ተፍ ተፍ ባልል ኖሮ ዛሬ ጋሼ እንዲህ ሲያረጅ የምንበላው እንኳን እንቸገር ነበር፡፡ ግን እኔ ከጎን ገባሁላቸው …… ቤታችንም አልፈረሰም፡፡ ጋሼም አባዬም ደስ ብሏቸው ይኖራሉ፡፡ ቢያንስ ምን እንበላለን ብለው አይጨነቁም፡፡ ገባሻ! ኢንቱን አንተ ከምትረዳት በላይ እረዳታለሁ፡፡ እኔም እሷም የውጪውን አለም ተጋፍጠነዋል፡፡ እኔ ወንድ ነኝ፡፡ ከማንም ጋር ታግዬ የሆነ ነገር ይዤ መግባት እችላለሁ፡፡ ለእሷ ግን ይከብዳል፡፡ ሴት ናት! ብዙ መከራ አለ፡፡ የኢንቱ ደሞዝ ስንት እንደሆነ ታውቃለህ? ሶስት ሺህ ምናምን ነው፡፡ እሱንም አሁን በጣም አደገ ተብሎ ማለት ነው፡፡ ከዚህ ሀያሁለት ለትራንስፖርት ስንት እንደምታወጣ ታውቃለህ? ብዙ ነው! አንተንና አባይዬን መመገብ ስላለባት እሷ ምግብ አትበላም፡፡ እናንተ ወሩን ሙሉ እንድትበሉ ስትል እሷ ምሳ አትበላም፡፡ ዶክተር እንድትሆንላት ትፈልጋለች፡፡ የተቸገረ ሰው ገንዘብ በማጣቱ መታከም እንዳያቅተው ማድረግ የምትችል ይመስላታል፡፡ ግን እንደዚያ አይደለም፡፡ ዶክተር ልትሆን ትችላለህ፡፡ ኢንቱ እንዴትም ብላ እዛ ደረጃ ልታደርስህ ትችል ይሆናል፡፡ ግን ዶክተር ስለሆንክ የፈለግከውን አታክምም፡፡ አንተም የቅባት ተቀጣሪ ትሆናለህ፡፡ አቅም ያላቸውን ታገለግላለህ፡፡ ስራው በግለሰብ ደረጃ የሚሰራ አይደለም፡፡ መርዳት የምትችለው ዶክተር ስትሆን ሳይሆን ሀብታም ከሆንክ ነው፡፡ ዶክተር ባትሆንም ገንዘብ ካለህ ሆስፒታል መገንባት ትችላለህ፡፡ ከዚህ በላይ በዚህ ቅዠት ውስጥ ከቀጠልክ ግን ኢንቱን እንደዛሬው ልናተርፋት አንችል ይሆናል፡፡ ንቃ ኢቦ ንቃ!›› ትከሻዬን በእጁ ተመተመኝ፡፡
መንታ መንገድ መሀል ቆሞ ለምርጫ እንደተቸገረ ሰው …… ሁለቱም መንገድ የት እንደሚያደርሰው እንደማያውቅ …. ልክ እንደሱ …. ውዝግብ እንዳልኩ በዝምታ ተዋጥኩ፡፡ አብዱኬ ቀጠለ፡፡
‹‹በዚህ ጉዳይ ላይ ከኢንቱ ጋር ብዙ ጊዜ ተጨቃጭቀንበታል፡፡ አንተን በዚህ መልኩ እንዳልጫንህ ታስጠነቅቀኝ ስለነበር ምንም ማድረግ አልቻልኩም፡፡ ኢቦ ከዚህ በኋላ ህፃን አይደለህም አስብበት!›› ትቶኝ ወደ ቤት ገባ፡፡ ትንሽ ቆይቼ ተከተልኩት፡፡
ኢንቱ ተነስታ ነበር፡፡ ከአብዱኬ ጋር ሲያወሩ ደረስኩ፡፡ ፊቷ ወደ ቀደመው ፍካቱ ተመልሷል፡፡ ከአጠገቧ ስቀመጥ አይኔ ላይ አፈጠጠች፡፡
‹‹አልቅሰሀል እንዴ?›› በእጇ ራሴን እየዳበሰች ጠየቀችኝ፡፡
ዝም አልኳት፡፡ ‹‹ደህና ነኝ እኮ …… ምንም አልሆንኩም እኮ ……›› እያለች ከጀርባዬ ተጠመጠመችብኝ፡፡ ምንም መናገር አልፈለግኩም፡፡ የሰፈር ሰዎች ኢንቱን ለመጠየቅ ወደ ቤት መምጣት ስለጀመሩ እኔና አብዱኬ ቦታውን ለእነሱ ለቅቀን ወጣንና የቅድሙ ድንጋይ ላይ ተቀመጥን፡፡
‹‹ታውቃለህ አብዱኬ …… ለእኔ ትክክለኛው ነገር የኢንቱን ህልም ማሳካት …… ሀኪም መሆን ይመስለኝ ነበር፡፡ እኔ ፈልጌው ሳይሆን እሷ ስለምትፈልገው ማለት ነው፡፡ ግን ልክ ነህ …… ኢንቱዬ እኛን ለማኖር ምን ያህል መስዋዕትነት እየከፈለች እንደነበር እስከቅርብ ጊዜ ድረስ አላውቅም ነበር፡፡ እንዳንተ እውነተኛውን አለም ከመጋፈጥ ይልቅ በመፅሀፍት ተሸሽጌ በእሷ ህመም ምቾቴን ስገነባ ነበር፡፡›› ሳግ ተበተበኝ፡፡ አብዱኬ ትከሻዬን እየነቀነቀ ሊያባብለኝ ይሞክራል፡፡
‹‹ግን አሁን ወስኛለሁ፡፡ ምናልባት የአስራሁለተኛ ክፍል ፈተና ስለደረሰ ልፈተን እችል ይሆናል፡፡ ከዚህ በላይ ግን ኢንቱዬ ላይ ሸክም አልሆንም፡፡ አሁን ኢንቱን የመንከባከብያ ጊዜዬ ነው፡፡እስከዛሬ ለእኛ ኖራለች፡፡ ከዛሬ ጀምሮ ለእሷ መኖር መጀመር አለብኝ፡፡ ማንኛውንም አይነት ስራ መስራት ካለብኝ እሰራለሁ፡፡ ማንኛውንም!›› እንባዬን እየጠራረግኩ ጉልበቴን መደብደብ ጀመርኩ፡፡
‹‹ትዝ ይልሀል ……›› አለ አብዱኬ መሬቱን በእጁ እየዳሰሰ፡፡ ‹‹አንድ ቀን ማታ እንደውም ኢንቱ እራት ከኛ ጋር ከበላች ቆይታለች …… አቅርባልን በልቻለሁ ብሉ ትላለች ምናምን ብለኸኝ ሰላጣ ምናምን ገዝተን አልገባንም? ያኔ ለምን ምግብ የገዛሁ ይመስልሀል? በልቻለሁ ብሉ ምናምን የምትላችሁ የእውነት በልታ ሳይሆን ገንዘብ አጥሯት ወሩ እስኪደርስ እናንተ የምትበሉት እንዳታጡ ብላ እንደሆነ ስለባተትኩ ነው፡፡ ሰላጣውን ይዘን ስንገባ ግን የሌለ ደስ ብሏት በላች፡፡ ከዛም ብዙም አልቆየም አስመለሳት፡፡ አይደል? ምክንያቱም ምግብ ካገኘች ቆይታ ነበር፡፡ ኢንቱ እየበላች አልነበረም፡፡ ይገባሻል ብዬ አስቤ
36 views05:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 19:19:03 አጃ አለብኝ ትላችዋለች አንዲት እህታችን


በዱሀ
501 views16:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-23 18:56:50 ክኬ አቀፍኳት፡፡ እማዬ ከመኝታዋ መነሳት አቅቷት እያለቀሰች ታያታለች፡፡ ውሀ ላጠጣት ሞከርኩ፡፡ አስመለሳት፡፡ ከውስጧ የወጣው ውሀ ብቻ ነበር፡፡ ምን ማድረግ እንዳለብኝ ግራ ተጋባሁ፡፡ ኢንቱን ባለችበት አስተካክዬ አስተኝቼ አብዱኬን ለመጥራት ሮጥኩ፡፡ ከአብዱኬ ጋር ስንመለስ ኢንቱ ራሷን ስታለች፡፡ አብዱኬ አቅፌያት እንድወጣ ነግሮኝ ብር ሊያመጣ ወደ ቤት ሮጠ፡፡ ኢንቱዬን ተሸክሜ ወደ ዋናው መንገድ ከወጣሁ በኋላ ቁልቁል መንደርደር ጀመርኩ፡፡ የሰፈር ሰዎች ከበው ይከተሉኛል፡፡ አብዱኬ ደርሶብን አልፎን መሮጥ ጀመረ፡፡ ወደ ሰፈራችን የሚመጣ መኪና ስለሌለ ባጃጅ ተራ ድረስ በዚህ መልኩ መጓዝ ሊጠበቅብን ሆነ፡፡ ትንሽ እንደተጓዝን አብዱኬ ባጃጅ ይዞ መጣ፡፡ ኢንቱዬን ከባጃጁ የኋላ ወንበር ላይ አንገቷን ጭኔ ላይ አስቀምጬ አስተኝቻት፤ አብዱኬ ከፊት ከሹፌሩ ጋር ተቀምጦ ወደ አለምባንክ ጤና ጣቢያ መሄድ ጀመርን፡፡ ሰውነቴ ይንዘፈዘፋል፡፡ ወደ ጤና ጣቢያው ገብተን ኢንቱዬን ለነርሶቹ አስረከብናቸው፡፡ እሁድ ስለነበር የጤና ጣቢያው ግቢ ጭር ብሏል፡፡ እኔ እየሆነ ያለውን ነገር ማመን አልቻልኩም፡፡ ድንዝዝ ብያለሁ፡፡ አብዱኬ እዚህ እዚያ ይሯሯጣል፡፡ የሚያስፈልገውን ነገር አሟልቶ ሲጨርስ መጥቶ ከጎኔ ተቀመጠ፡፡
‹‹አብዱኬ …… አሁን እኮ እየሳቀች ነበር! እነማህሌትን እኮ ስታስተናግዳቸው ነበር ……›› እያለቀስኩ እለፈልፋለሁ፡፡ አብዱኬ ትከሻዬን እየተመተመ እንባ ባራሰው ድምፅ ‹‹ምንም አትሆንም ……›› እያለ ሊያፅናናኝ ይሞክራል፡፡
ከአንድ ሰዓት ጥበቃ በኋላ ነርሷ አብዱኬን ጠራችው፡፡ አናግሯት እየተመለሰ ‹‹ነቅታለች ማየት እንችላለን!›› አለኝ፡፡ እየተቻኮልኩ ወደተኛችበት የድንገተኛ ህክምና ክፍል ገባሁ፡፡ ኢንቱዬ እጅ ላይ መርፌ ተሰክቶ ውሀ የመሰለ ፈሳሽ ከጎኗ በብረት መስቀያ ተሰቅሏል፡፡ ስታየኝ የደከመ ፊቷ ላይ ፈገግታ ለመርጨት ሞከረች፡፡ አብዱኬ እንደሚመጣ ነግሮኝ ወጣ፡፡ የኢንቱዬን እጆች እየሳምኩ በስስት አያታለሁ፡፡ ላብ የወረሰው …… የደከመ ፊቷን ፈገግታ ለማልበስ ትሞክራለች፡፡ ነርሷ ገባችና ‹‹ይኼ እንደውም ራስን የማጥፋት ሙከራ ተብሎ ሪፖርት መደረግ የነበረበት ኬዝ ነው! …… እንዴት ሰው እስኪሞት ድረስ ምግብ ይተዋል?›› እያለች ጮኸች፡፡ ግራ ግብት ብሎኝ ነርሷንና ኢንቱን እያፈራረቅኩ እመለከታለሁ፡፡
ነርሷ እኔ ላይ እያፈጠጠች ‹‹ምግብ በአግባቡ መውሰዷን ተከታተሉ! …… ድጋሚ እንደዚህ ትተርፋለች ብላችሁ እንዳታስቡ!›› አለችኝ፡፡ እያቀረቀርኩ ‹‹እሺ ……›› አልኳት፡፡ ነርሷ ኢንቱ እጅ ላይ የተሰካውን መርፌ ነቅላ ወጣች፡፡
ከጥቂት ቆይታ በኋላ አብዱኬ ጁስ፣ አትክልት እና ውሀ በፌስታል ሞልቶ መጣ፡፡ ኢንቱዬ ቀስ እያለች ጁሱን መማግ ጀመረች፡፡ ጤና ጣቢያው ውስጥ ትንሽ ከቆየን በኋላ ወደ ቤት ለመሄድ ግቢውን ለቅቀን ወጣን፡፡ የጤና ጣቢያው በር ላይ በርካታ የሰፈራችን ሰዎች ቆመው ሲጠብቁን አገኘናቸው፡፡ ጥበቃው አላስገባም ብሏቸው ነበር፡፡ የኛ ሰፈር ሰው በየሄደበት አትገባም መባል ብርቁ አይደለም፡፡ ለምዶታል! ደሀ ድህነቱን ይለምድ ዘንድ …… መዋረዱንም ለምዶታል፡፡
ቤት ገብተን ኢንቱዬ አረፍ አለች፡፡ እንቅልፍ ይዟት ጠፋ፡፡ ተነፋፍቀው የነበሩ ይመስላሉ፡፡ እኔ ከራሴ ጋር እከራከራለሁ፡፡ ‹‹ኢንቱዬ ምግብ አትበላም ነበር? ለምን?›› ራሴን እወቅሳለሁ፡፡ እማዬ ኢንቱዬ በሰላም መመለሷን ስታይ በደስታ አንብታለች፡፡ አሁን እሷም እንቅልፍ ወስዷታል፡፡ ቀስ ብዬ የኢንቱን ማስታወሻ ደብተር አነሳሁ፡፡ ከከፈትኩት በኋላ ድንገት ከነቃች በሚል ፍርሀት ባለፈው ካቆምኩበት ቀጥሎ ያሉትን ተከታታይ ገፆች አብዱኬ ባመጣት ስልክ ፎቶ አነሳኋቸው፡፡ ስልኩ እንዳይታይብኝ በመማርያ መፅሐፌ ሸፍኜ ማንበብ ጀመርኩ፡፡
‹‹ኢቦዬ …… ሰኞ እለት የእማዬን የምርመራ ውጤት ተቀበልኩ፡፡ መከራ ሲደራረብብህ ይቀላል እንዴ? …… ሀኪሙ ቀለል አድርጎ እማዬ ካንሰር አለባት አለኝ! ሰውነቷ ውስጥ ስለተዛመተ መቆጣጠር አንችልም ግን አቅሙ ካላችሁ እድሜዋን ለማርዘም የተሻለ እንክብካቤ እንዲደረግላት የግል ሆስፒታል አስተኟት አለ፡፡ አቅም ካለህ የእናትህን እድሜ መጨመር ትችላለህ …… ከሌለህ ደግሞ ወላጅ አልባ ትሆናለህ ነው ነገሩ! ታውቃለህ ምንም አልመሰለኝም! ውጤቱን ተቀብዬው ወጣሁ፡፡ አላለቀስኩም! ደሞ ለምን አለቅሳለሁ? ለእማዬስ ቢሆን በህይወት ከመሞት የእውነቷን ሞታ ከአባዬ ጋር መሆን አይሻላትም? ግድየለሽ እየሆንኩ እንደሆነ እየተሰማኝ ነው፡፡ እማዬ ጥሩ ምግብ ማግኘት አለባት፡፡ እኛ ደግሞ የለንም! አሁን አሁን ድሮ ተማሪ እያለሁ ከጓደኞቼ ጋር እንደቀልድ ለበርገርና ለፒዛ እናወጣው የነበረው ገንዘብ ትዝ እያለኝ ……… ምነው ጊዜን መመለስ በተቻለና ገንዘቡን ለተቸገረ ሰው ሰጥተን በነበረ እላለሁ፡፡ ግን ደግሞ ያኔ የችግርን ህመም አናውቀውም ነበር፡፡ መብላት እየፈለጉ ጦም የማደርን ስቃይ አልቀመስነውም ነበር፡፡ ችግረኛን ለመርዳት ችግሩን መረዳት ነበረብን፡፡ ችግሩ ደግሞ ሶፋ ላይ ተቀምጠህ ወይም መጅሊስ ላይ ተጋድመህ የሚገባህ አይነት አይደለም፡፡ በተቸገረው ሰው ጫማ ውስጥ ቆመህ …… ውሎውን ውለህ …… አዳሩን አድረህ የምትረዳው ነው፡፡ እና እኔ ደግሞ ስረዳው ሰጪ ሳይሆን ለማኝ ነበርኩ፡፡ ራሴንና ቤተሰቤን ለማኖር የምፍጨረጨር ምስኪን!
የእማዬ ህመም ካንሰር መባሉን ለያስሚን ነገርኳት፡፡ ላንተ አልነግርህ ነገር ትረበሽብኛለህ ብዬ ፈራሁ፡፡ ምን በወጣህ ትጨነቃለህ …… እኔ ከተጨነቅኩ አይበቃም? …… ያስሚን ሲጨንቃት ለአንድ ጎረቤቷ ነገረችው፡፡ ቢያንስ የሚረዳን ካገኘን ደህና ምግብ ብትበላ እናታችንን ለተጨማሪ ቀናቶች በህይወት እናያታለን ብዬ አስቤ ነበር፡፡ ጎረቤቷ ጀሞ አካባቢ ያለ አንድ ሙስሊም ወጣት ልጆች ያቋቋሙት እድር ነገር ስላለና ዘመዱ አባል ስለሆነ ለእሱ ጉዳዩን አስረዳው! እነሱ መጥተው ለመመልከት እንደሚፈልጉ ነገረን፡፡ አንተ ትምህርት ቤት በነበርክበት የእረፍቴ ቀን ሊመጡ ተቀጣጠርን፡፡ ወጣቶች ናቸው፡፡ ገና ህይወትን በቅጡ እንዳልተረዷት ያስታውቃሉ፡፡ ገንዘብ ማሰባሰብ ስለቻሉ ብቻ እድር የከፈቱ! እንደዛ ናቸው፡፡ ገና የቤታችንን ቁልቁለት መውረድ ሲጀምሩ ጀምሮ ካሜራቸውን አጥምደዋል፡፡ ስድስቱም ነው የምልህ ስድስቱም እየቀረፁ ነው፡፡ አንዱ አበጥበጥ ያለ ወጣት ወደ እኔ ተጠግቶ አብሮኝ ሰልፊ ተነሳ፡፡ ትዕግስቴ ሙጥጥ ብሎ ሲያልቅ ተሰማኝ! ሴቶቹ ከቤታችን ጋር ፎቶ ይነሳሉ፡፡ ቤት ካስገባኋቸው እማዬንም እንዲህ ሊያስቸግሩ መሆኑ ስለገባኝ መቅረፅ ካላቆሙ እንደማላስገባቸው ነገርኳቸው፡፡ ጎረምሳው ምን እንዳለኝ ታውቃለህ …… ‹‹ድሀ ሆነሽ ምን ያወጣጥርሻል?›› አዎ ጆሮዬን ማመን አቃተኝ፡፡ ሆዴን ስለራበው ክብሬን ለመርገጥ ሞከረ፡፡ በጥፊ አጮልኩት! ጋሽ አብራር ልጁ ሲጮህ ሰምተው መጡና አባረሯቸው፡፡ ከሄዱ በኋላ አምርሬ አለቀስኩ፡፡ ምናለ ወይ ለእነሱ ህሊና በሰጣቸው …… ወይ እኛን ህሊና በነሳን ብዬ ተመኘሁ፡፡ ሰዉ የተሸከመው የማይገባውን ሀላፊነት ነው፡፡ ፍፁም የማይገባውን!››
ሳለቅስ እማዬ ሰማችኝ መሰለኝ ከእንቅልፏ ባነነች፡፡ ‹‹ምነው?›› አለችኝ በደከመ ድምጽ!
‹‹ምንም!›› አልኩ እንባዬን እየጠረግኩ!
.
ይቀጥላል …
902 views15:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ