Get Mystery Box with random crypto!

ሀላል ትዳር👫💍

የቴሌግራም ቻናል አርማ hayu_abdi — ሀላል ትዳር👫💍
የቴሌግራም ቻናል አርማ hayu_abdi — ሀላል ትዳር👫💍
የሰርጥ አድራሻ: @hayu_abdi
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 8.54K

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-09-02 12:28:17 ኪ ሁሌ ስታዪኝ የሚመጣልሽን አንድ ጥያቄ ጠይቂኝ!››
‹‹ለምንድን ከፈረ?››
‹‹አዎ! አየሽ ስሜ ኢብራሂም ነው ግን ደግሞ ሙስሊም አይደለሁም፡፡ ግን ስሜ ኢብራሂም በመሆኑ ሰዉ እንዴት ኢብራሂም ሰሚር ተብዬ ሙስሊም ላልሆን እንደምችል ሊሞግተኝ ይፈልጋል፡፡ አጭሩ መልስ ሀይማኖቴን ቀይሬ የሚለው ነው፡፡ ግን ደግሞ ጥያቄው በዚሁ አያቆምም! ለምን ይሉኛል፡፡ የዚህም መልስ ሌላ ጥያቄ ይወልዳል፡፡ ይኼን ደግሞ ህይወቴን ሙሉ ለሁሉም ማብራራት አልፈልግም! ስለዚህ ገና ከሩቁ መሸሽን እመርጣለሁ፡፡››
ከመኪናዋ ወርደን ወደ አንድ ሆቴል ካፌ ገባን፡፡ ትኩስ ነገር አዝዘን ጨዋታችንን ቀጠልን፡፡
‹‹የቅድሙን ቁጣ የማትደግመው ከሆነ አንድ ጥያቄ ልጠይቅህ?›› ፈገግ ብላ ጠየቀችኝ፡፡
‹‹ምን?››
‹‹ብዙ ለምን ያለውን አሰልቺውን ጥያቄ ለእኔ ብቻ ንገረኝ!››
ለጥቂት ደቂቃዎች ዝም ብዬ ተመለከትኳትና ፈገግ አልኩ፡፡
.
ይቀጥላል …
742 views09:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 12:27:50 ሉ ይርቃታል፡፡››
‹‹hey come on አብርሽ! እና ሁሌ እንደታመመች ትኑር እንዴ? ሰዉ ከፈለገ የፈለገውን ይበል! ከፈለገ ‹‹በቃ ለቀቀች›› ይበል! No አልበቃም ታክማ ትድናለች ማለት ያለብህ አንተ ነህ! በተግባር ማለት ነው! Use your brain men!›› ተቆጣች፡፡
‹‹ታውቂያለሽ …… እሱ ሁሉ ጠፍቶኝ አይደለም! ግን ኢንቱዬ ታማለች ብዬ ማመን አልፈልግም! …… እኔንጃ ሚቾ …… አይሻላትም ቢሉኝስ ብዬ እፈራለሁ፡፡ አይሻላትም ያሉኝ ቀን ሰው የምሆን አይመስለኝም፡፡ ህልምን ፈርቶ ሳይተኙ እንደማደር ነው የሆነብኝ! አይቻልም አይደል?›› እንባዬ አይኔን ሞላው! መነፋረቅ ጀመርኩ፡፡ ቀራኒዮ ደርሰን ስለነበር መኪናውን አቁማ አቅፋ ታባብለኝ ጀመረች፡፡ አቤላ የመኪናውን በር ቀስ ብሎ ከፍቶ ወረደ፡፡ እጇን ፊቴ ላይ ስታርመሰምሰው ነዘረኝ፡፡ ከዚህ በፊት እንደዚህ ተሰምቶኝ አያውቅም፡፡ ‹‹ምጷ›› የሚል ድምፅ ተሰማ፡፡ በሀፍረት አቀረቀረች፡፡ አንገቴን ሰበርኩ፡፡ መኪናዋን አስነስታ ወደኛ ቤት ነዳችው፡፡ እጇ ሲንቀጠቀጥ ይታየኛል፡፡
አንገቴን በስሱ ወደሷ አዙሬ እየተመለከትኩ ‹‹ይቅርታ ……›› አልኩ፡፡
‹‹it’s okay …… it’s fine›› ፊቷ በድንጋጤ ቀልቷል፡፡
መኪናዋን ጥበቃ ያለበት ቦታ አቁመን ወደ ቤት ማዝገም ጀመርን፡፡ ዳገቱ ሲከብዳት እንደቀድሞው ልትይዘኝ ትልና ትተወዋለች፡፡ ባልሳምኳት ብዬ ተፀፀትኩ፡፡ ውለታዋን ያረከስኩ መሰለኝ፡፡ ሀሳቧን ለማስቀየር ጥያቄ ሰነዘርኩ፡፡
‹‹ሚቾዬ …… ብዙ የሀብታም ልጆች ቤት ቁጥጥር ይበዛባቸዋል፡፡ አንቺ እኛ ጋ ስታድሪ አባትሽ ምንም አይልሽም?››
‹‹ልመለስ? መምጣቴ ደበረህ?›› አኮረፈች፡፡
‹‹እኔ እንደዛ አላልኩም እኮ …… እኔ የሚደብረኝ አንቺ ሳትኖሪ ነው፡፡››
ሳቀችና ‹‹ሚስትነትን ልለማመድ ብዬ እኮ ነው!›› አለችኝ፡፡ በደስታ አቀፍኳት፡፡
‹‹አሁን መልሱን ልመልስልህ ወይስ እንደዚሁ እንደጨመቅከኝ ልንቆም ነው?›› እጄን ትከሻዋ ላይ ጥዬ መሄድ ጀመርን፡፡
‹‹ታውቃለህ …. ቤት ስሆን ብቸኝነት ይሰማኛል፡፡ dad በጣም ስለሚያምንብኝና ስሜቴን ስለሚረዳ የት እንደሆንኩ ይወቅ እንጂ ምንም አይለኝም፡፡ So ምንም አይለኝም ነው መልሱ!››
ተቃቅፈን ወደ ቤት ስንገባ አብዱኬ ኢንቱን እያባበለ ምግብ እያጎረሳት ነበር፡፡ ቤት ውስጥ ተቃቅፈን ስንቆም ግራ በመጋባት አፍጥጦ ተመለከተንና ‹‹አዲስ level unlock አስደረጋችሁ እንዴ?›› አለ፡፡
አነጋገሩ አስቆን መሳቅ ስንጀምር ኢንቱም ሳቀች፡፡ ገብቷት ይሁን አይሁን ግን አላውቅም፡፡
‹‹level unlock ምናምን …… ደግሞ ከመች ጀምሮ ነው ጌም ተጫዋች የሆንከው?››
‹‹እና አራቱን ቀን ከኢንቱ ጋር ምን ስንሰራ የምንውል ይመስልሀል?›› እያለ ያሳሰረችውን ስልክ አሳየኝ፡፡
ኢንቱዬን ስመን እንደተቀመጥን አብዱኬ ማህሌትን እያየ ‹‹የምር የምር ግን ምንም ለውጥ የለም?›› አለ፡፡ ሚቾ አቀረቀረች፡፡ አብዱኬ እየሳቀ ‹‹እንግዲህ ያጣፍጥላችሁ!›› አለ፡፡ እራት ለወጉ እየቀማመስን ማህሌት ህክምናውን በተመለከተ አብዱኬን አማከረችው፡፡ እሱም እያሰበበት እንደነበረ ነግሯት በነጋታው ሀኪም ቤት ለመሄድ ተስማማን፡፡
‹‹ከአምስት አመታት በኋላ››
ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ግቢ ከመኪናዬ ወርጄ መራመድ ስጀምር የክላክስ ድምፅ ሰማሁ፡፡ ዞር ብዬ ስመለከት አንዲት ቆንጅዬ ልጅ ሂጃቧን እያስተካከለች ከመኪናዋ ወረደች፡፡ ቀጠሮዬ ከእርሷ ጋር ነበር፡፡ ከብዙ ቀናት ጭቅጭቅ በኋላ ዛሬ የምትለውን ልሰማት ፈቅጃለሁ፡፡ አጠገቤ ደርሳ ‹‹ኢብሮዬ በጣም አመሰግናለሁ፡፡ ትመጣለህ ብዬ አላሰብኩም፡፡›› አለችኝ፡፡ ረዘም ብላ ቀላ ያለች ቆንጅዬ ልጅ ናት፡፡ ሙስሊሞች የሚለብሱትን ጥቁር አባያ ለብሳለች፡፡
ኮስተር እንዳልኩ ‹‹ለምን ተጠራጠርሽ?›› አልኳት፡፡
‹‹ብዙ ሰው እሺ አይልሽም ብሎኝ ስለነበር ነው፡፡ እና መኪና ውስጥ እናውራ ወይስ ሻይ ቡና እያልን እናውራ?››
‹‹ደስ እንዳለሽ …››
መኪናዋ ውስጥ ገብተን በመኪናዬ አጠገብ ስናልፍ ‹‹ይኼ መኪና አንድ ነጥብ ምናምን ነዋ የሚሸጠው?›› አለች፡፡
አንገቴን በአዎንታ እየነቀነቅኩ ‹‹መኪናሽ በጣም ታምራለች! ለምን Cheat ታደርጊባታለሽ?›› አልኩ፡፡ በግርምት አየችኝ፡፡
‹‹ምነው?››
‹‹ቀልድ የምታውቅ አይመስለኝም ነበር፡፡››
‹‹ገምቻለሁ፡፡››
‹‹ለምንድነው ሰው እንዲቀርብህ የማትፈልገው?››
‹‹ብዙ የሚቀርቡኝ ሰዎች አሉ፡፡››
‹‹ማለቴ እኔ የማውቃቸው ብዙ ልጆች በስራ ካልሆነ አሊያም ስንቸገር ካላየ በቀር ዞር ብሎ እንኳን አያየንም ነው የሚሉኝ!››
‹‹ሙስሊሞችን ማለትሽ ነው?››
‹‹አዎ ብዙዎቹ ሙስሊሞች …… ግን ሌሎችም አሉ፡፡››
‹‹ሙስሊሞች ላይ ነው እንጂ ሌሎቹ ላይ እንኳን ብዙም አልኮሳተርም፡፡››
‹‹እኮ ምንድነው ምክንያትህ?››
‹‹ለዚህ ነው የፈለግሽኝ?!›› ተቀያየርኩባት፡፡
‹‹ይቅርታ …… ተረጋጋ በቃ›› ደንግጣለች፡፡ በመካከላችን ለረዥም ደቂቃዎች ዝምታ ነገሰ፡፡ ከሚገባው በላይ የተንጠባረርኩባት መሰለኝ፡፡ በምን መልኩ ንግግራችንን ማስቀጠል እንዳለብኝ ማውጠንጠን ጀመርኩ፡፡ አይኖቼ መኪናው ውስጥ ሲቃብዙ መስታወቱ ላይ የተለጠፈ ጥቅስ ተመለከትኩ፡፡ ‹‹ከመርዳት መረዳት ይቅደም!›› ይላል፡፡ ከጥቅሱ ስር ‹‹ኡሚ የየቲሞች ልማትና መረዳጃ እድር›› የምትል ፅሁፍ አለች፡፡ ጥቅሱ ቀልቤን ስቦታል፡፡
ወደ ጥቅሱ እየጠቆምኩ ‹‹ይኼን …… ገዝተሽው ነው ወይስ?›› አልኳት፡፡
‹‹አይ እኛ ነን ያሰራነው!››
‹‹አባባሏን ወድጃታለሁ ማነው የፃፋት?››
‹‹ፕሬዝዳንታችን ነው፡፡ ሁሌም ችግርን ከመቅረፍ በፊት የችግሩን ምንነት መረዳት አስፈላጊ እንደሆነ ይነግረናል፡፡ የምናግዛቸውን ቤተሰቦች ህመም ስንረዳ እነሱን ለማገዝ የምናደርገው ሁለንተናዊ ጥረት የመስመር እድሉ ሰፊ ነው ይላል፡፡››
‹‹ምንድነው የምትሰሩት?››
‹‹ገንዘብ ከአባላቶቻችን እያሰባሰብን በቋሚነት በአቅም የደከሙ ቤተሰቦችን እናግዛለን፡፡ በገንዘብ ብቻ ሳይሆን ፍቅር በመስጠትም ማለት ነው፡፡ ቤተሰብ እንከፋፈልና የልጆቹን የጥናት ሁኔታ እንከታተላለን …… ኢስላማዊ ትምህርቶችንም እየከፈልንላቸው እንዲማሩ እናደርጋለን፡፡ ሁሌ የሰው እጅ እንዳይጠብቁ ደግሞ ስራ የመስራት አቅም ያላቸውን በተወሰነ ካፒታል ስራ እናስጀምራቸዋለን፡፡ ቤታቸውን እናድሳለን፡፡ በቃ በአጭሩ ቤተሰብ እንሆናቸዋለን፡፡››
‹‹ይገርማል …… ቢሮ ምናምን አላችሁ ወይስ?››
‹‹አለን ቤተል ነው፡፡ ቤተልን ታውቀዋለህ?››
‹‹እየቀለድሽ ነው?››
‹‹ኧረ አልቀለድኩም!›› በጥያቄ አይን ተመለከተችኝ፡፡
‹‹ሰፈሬ እኮ ነው፡፡››
‹‹አትቀልድ!?››
‹‹የምሬን ነው …… ቆይ የት ሰፈር ያሉ ናቸው የምታግዟቸው? ማለቴ ቤተል ብዙ እንደዚህ አይነት ችግር ያለ ስላልመሰለኝ ነው፡፡››
‹‹አንፎ፣ ቀራንዮ፣ ገመቹ፣ ካራ፣ ምናምን ከብዙ ቦታ ነው ሰዉ የሚመጣው! ደግሞ ቤተልም አይጠፋም!››
አንፎ ስትል ደነገጥኩ፡፡ ፈጠን ብዬ አንፎ ሄዳ ታውቅ እንደሆነ ጠየቅኳት፡፡ በብዛት እንደምትሄድ ነገረችኝ፡፡ አንፎ ላይ እሷ እየሄደች የምትከታተላቸውን ቤተሰቦች ስም ጠየቅኳት፡፡ የማውቃቸውን ሰዎች ጠራችልኝ፡፡ ለልጅቷ የነበረኝ እይታ ተቀየረ፡፡ ነፃ ሆኜ ማውራት ጀመርኩ፡፡
‹‹ቅድም ምንድን ነበር የጠየቅሽኝ?››
‹‹ለምንድነው ሰው የማትቀርበው ነበር ያልኩህ!››
‹‹ስለራሴ ማብራራት ስለሚደክመኝ ነው፡፡ በተለይ ሙስሊሞችን መቅረብ የሚደብረኝ ለዚያ ነው፡፡ ለምሳሌ አሁን አንቺ ስለኔ ጭንቅላትሽ ውስጥ ብዙ ጥያቄዎች አሉ፡፡ እስ
629 views09:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 12:27:32 ከተራራው ላይ
ክፍል አስራሶስት
(ፉአድ ሙና)
.
‹‹ከመራራው ስር፣ የማር ጠብታ፣
መፆም አልቻልኩም፣ ልቤ ተረታ፡፡
ይቅርታ!››
.
ግርግሩ ቀስ በቀስ መስከን ጀመረ፡፡ ሆኖም ኢንቱዬ ወደ ቀድሞ ማንነቷ መመለስ አልቻለችም፡፡ አንዳንዴ ወደ እኔ ትመጣና ‹‹ለአንድ ቀን እማዬን መጠበቅ አቃተህ!?›› እያለች ትጮህብኛለች፡፡ አንዳንዴ ‹‹ጋሽ አብዱረዛቅ ለምን እማዬን አይመልሱልንም? ለምንድነው የሰው እናት የሚወስዱት?›› ትላለች፡፡ ሲላት ብቻዋን ትስቃለች፡፡ ሲያሻት ማስታወሻ ደብተሯን አቅፋ ታለቅሳለች፡፡ የሆነ ሰዓት ላይ ደግሞ ወደ ራሷ ትመለስና ‹‹ኢቦዬ …… ራበህ እንዴ? ብር እኮ አለን! እየውማ እየውማ!›› እያለች ፖስታውን ታሳየኛለች፡፡ አሁን አሁን ከእማዬ ሞት ህመም በላይ እየጎዳኝ ያለው የኢንቱ ሁኔታ ነው፡፡ የሚመጣው ለቀስተኛ ሁሉ ‹‹ውይ ለቀቀች!›› እያለ ከንፈሩን ይመጣል፡፡
አብዱኬ በቀጠሮው መሰረት ፍርድ ቤት ቀርቦ በድጋሚ የሰባት ቀን ቀነ-ቀጠሮ ተጠይቆበታል፡፡ ሳምንቱ ሲያልፍ ቤታችን ወደ ቀድሞው ድባቡ ተመለሰ፡፡ ከቤታችን የማይጠፉት አቤላ፣ ማህሌትና ጥቂት የሰፈራችን ልጆች ናቸው፡፡ የፌሎው ልጆች እስካሁን ሶስት ጊዜ ያህል መጥተው ጠይቀውኛል፡፡ ኢንቱዬ ማህሌትን ስታይ ደስ ይላታል፡፡ ማህሌት የምታድር ጊዜ አቅፋት ትተኛለች፡፡ እሷ ከሌለች ከኔ ጋር ካልሆነ በፍፁም አትተኛም፡፡ የአብዱኬ ቀጠሮ ሲደርስ ማህሌት በዚህኛው መቅረት የለብንም ብላ ወተወተችን፡፡ በእርግጥ ሀሳቧ ከቀጠሮው በላይ እኛን ማናፈስ ነበር፡፡ እኔ፣ ማህሌት፣ ኢንቱ፣ አቤላና ጋሼ ሆነን በማህሌት መኪና ወደ ኮልፌ ሄድን፡፡ አብዱኬ የእማዬን መሞት አውቋል፡፡ ሲገባ ቆመን ሲያየን ፈገግ ለማለት እየሞከረ እጁን አውለበለበልን፡፡ ጉስቁልቁል ብሏል፡፡ በጣም ከስቷል፡፡ ጋሼ ሲያዩት አይናቸው እንባ ሞላ፡፡ ኢንቱ ግቢው ውስጥ እየለፈለፈች ስታስቸግረን ከማህሌት ጋር መኪና ውስጥ እንድትቆይ አደረግን፡፡
ትንሿ የችሎት አዳራሽ ውስጥ ተሰይመን የፍርድ ሂደቱን መከታተል ጀመርን፡፡ የአብዱኬ ተራ ደርሶ ፖሊስ መከራከሪያውን አቅርቦ ውሳኔ እንዲሰጥበት ጠየቀ፡፡አብዱኬም ወንጀሉን አለመፈፀሙንና ከዚህ በፊትም ምንም አይነት የወንጀል ታሪክ እንደሌለው በመጥቀስ ተከራከረ፡፡ በስተመጨረሻ ዳኛዋ አብዱኬ በአምስት ሺህ ብር ዋስ እንዲለቀቅ ወሰነች፡፡ በደስታ ሰጠምን፡፡ አብዱኬ ከችሎቱ በረዥሙ እየተነፈሰ ወጣ፡፡ ቀስ እያልን ችሎቱን ለቀን ወጣን፡፡ መዝገብ ቤት ሄደን መዝገቡ እስኪመጣ ከጠበቅንና ወረቀት ከተቀበልን በኋላ ክፍያውን ሞቢል አካባቢ ከፍለን እንድንመለስ አዘዙን፡፡ ከማህሌት ጋር ሄደን ከፈልን፡፡ ከከሰዓት በኋላ አብዱኬ ተለቀቀ፡፡ በደስታ ተቃቀፍን፡፡ ማህሌት የደስ ደስ ካልጋበዝኳችሁ ብላ ወደ አንድ ሬስቶራንት ወሰደችን፡፡ ኢንቱዬ አብዱኬን እየደጋገመች አቅፋ ትስመዋለች፡፡ ሁኔታዋ ግራ አጋብቶት በአይኑ ምን ሆና እንደሆነ ሊጠይቀን ይሞክራል፡፡ አዕምሮዋ መነካቱን ሲያውቅ ራሱን መቆጣጠር አልቻለም፡፡ እየተንሰቀሰቀ ማልቀስ ጀመረ፡፡
አብዱኬ ተፈትቶ ስራ ከጀመረ በኋላ ማህሌት ትኩረቴን ወደ ንባብ እንዳደርግ ለማድረግ የቻለችውን ያህል ጥራለች፡፡ ኢንቱ እንዲህ ታምማ ባለችበት ሁኔታ ወደ ቤተ-መፅሀፍት ሄጄ ማንበብ ባልችልም የቻልኩትን ያህል ቤት ውስጥ ለማንበብ እሞክራለሁ፡፡ ኢንቱዬ ብቻዬን ሆኜም ሆነ ከማህሌት ጋር ቤት ውስጥ ስናነብ ስታይ ደስ ይላታል፡፡ ማስታወሻ ደብተሯን አቅፋ እየሳቀች ታየናለች፡፡ ኢንቱና ማህሌት ንፋስ ለመቀበል ወጣ ሲሉ በዚህ ወር የተፈጠሩትን ነገራቶች ማሰላሰል ጀመርኩ፡፡ ኢንቱ ያመጣችውን ፖስታ ከፍቼ ተመለከትኩት፡፡ ውስጡ ሰላሳ ሺህ ብር ነበረው፡፡ አሁን እኛ ሰላሳ ሺህ ብር ምን ያደርግልናል? ምናልባትም ማህሌት ያለችው ልክ ሳይሆን አይቀርም፡፡ ሰው ይርባል፡፡ እማዬ ትናፍቃለች፡፡ ያቺ ኢንቲሳር ትናፍቃለች፡፡ አሁን ይኼ ገንዘብ ምን ይጠቅማል? ድሮ ልጅ ሆኜ የአማርኛ መፅሀፋችን ላይ ያነበብኩት የከበደ ሚካኤል ግጥም ትዝ አለኝ፡፡ ፅጌረዳና ደመና የሚል አርዕስት ያለው ግጥም ነበር፡፡
‹‹የፀሐዩ ንዳድ ያጠቃት በብዙ፣
ጠውልጎ የሚታይ የቅጠልዋ ወዙ።
አንዲት ጽጌረዳ ቃልዋን አስተዛዝና፣
እንዲህ ተናገረች ለሰማይ ደመና።

"ድርቀት በጣም ጎድቶኝ እየኝ ስንገላታ፣
እባክህ ጣልልኝ የዝናብ ጠብታ።
ቶሎ ካላራስኸኝ ጉልበቴ እንዲጥናና፣
ምንም ተስፋ የለኝ መሞቴ ነውና።"

"አሁን መሄዴ ነው ለትልቅ ጉዳይ፣
ስመለስ መጥቼ ሳልፍ ባንቺ ላይ።
አዘንምልሻለሁ ጠብቂኝ" እያለ፣
ምንም ሳይጥልላት መንገዱን ቀጠለ።

ጉዳዩን ጨርሶ ቆይቶ ሲመጣ፣
ያቺ ጽጌረዳ ስሯ ውሃ ያጣ፣
እንደዚያ አስተዛዝና ጭንቋን ያዋየችው፣
የፀሐዩ ንዳድ አድርቋት ቆየችው።
እስኪጎርፍ ድረስ የወንዝ ውሃ ሙላት፣
ወዲያው እንደመጣ ዝናቡን ጣለላት፣
ግን ደርቃለችና አልቻለም ሊያድናት።
"ሳልደርስላት ቀረሁ አዬ ጉድ" እያለ፣
ደመናም ወደፊት ጉዞውን ቀጠለ።

ሰውም እንደዚሁ ጭንቁን እያዋየ፣
በችግሩ ብዛት እየተሠቀየ።
ብዙ ጊዜ ኖሮ ቆይቶ ሲጉላላ፣
የሚረዳው አጥቶ ከሞተ በኋላ።
ዘመድ ወዳጆቹ እንባ እያፈሰሱ፣
ተዝካር ቢያወጡለት አርባ ቢደግሱ፣
ይህ ሁሉ ከንቱ ነው አይጠቅመውም ለሱ።
እውነት ከወደደው ሲቸገር ሲጎዳ፣
በሕይወቱ ሳለ ሰው ወዳጁን ይርዳ።››
ገንዘቡን ያገኘነው በፈለግነው ሰዓት ሳይሆን ከረፈደ ነው፡፡ ይኼ ገንዘብ እማዬን አይመልስም፡፡ ሰው ከምንም በላይ ዋጋ እንዳለው ተሰማኝ፡፡ በዙሪያዬ ያሉ እኔ ዘንድ ትልቅ ዋጋ ያላቸውን ሰዎች አሰብኩ፡፡ የኢንቱን ስልክ አንስቼ ተመለከትኩት፡፡ ከመቶ በላይ ያልተመለሱ ጥሪዎች ነበሩት፡፡ ስልኩን ከፍቼ የፅሁፍ መልዕክቶችን ካነበብኩ በኋላ የአሰሪ ተብዬውን ስልክ ወሰድኩ፡፡
የእኔና የማህሌት ግንኙነት ስሙ ምን እንደሚባል አላውቅም፡፡ ሰላም የሚሰማኝ እሷ ስትኖር ነው፡፡ ሁሌም ከጎኔ አለች፡፡ ይኼን የመከራ ጊዜ ያለሷ በፍፁም የማልፈው አይመስለኝም፡፡ ሞዴል ተፈትነን የዋናው ፈተና ቀን ደረሰ፡፡ ኢንቲሳር ከእኔ፣ ከማህሌት አሊያም ከአብዱኬ ጋር ካልሆነ ተረጋግታ መቀመጥ አትችልም፡፡ ትረበሻለች፡፡ ሞዴል ስፈተን አብዱኬ ለተከታታይ ቀናት ስራ አቋርጦ ሲጠብቃት ነበር፡፡ ለዋናው ፈተናም አብዱኬን ስራ ከማስፈታት ውጪ አማራጭ አልነበረንም፡፡ ፈተናው ተጠናቅቆ በመጨረሻው ቀን የፌሎው ልጆች የምህረት ቤተሰቦች ቤት ልዩ ግብዣ አዘጋጁ፡፡ ግብዣው ላይ ከአቤላና ከማህሌት ጋር ተካፍለን ወጣን፡፡ ማህሌት መኪናዋን አቤላን ለመሸኘት ወደ ቀራኒዮ እያሽከረከረች ‹‹አብርሽዬ ኢንቱዬ medical care ማግኘት ያለባት አይመስልህም?›› አለችኝ፡፡
‹‹ማለት?››
‹‹I mean የአዕምሮ ህክምና ምናምን ……››
‹‹የእብድ ሀኪም ቤት?›› ፊቴ ተቀያየረ፡፡
‹‹calm down አብርሽዬ …… የአዕምሮ ህመም እኮ just እንደሌላው ህመም ሁሉ በህክምና የሚድን ነው፡፡››
‹‹እና አማኑኤል ትግባ ማለትሽ ነው?›› ከዚህ ቀደም ስለ እብድ ሀኪም ቤት የሰማሁትም ሆነ በፊልም ያየሁት ነገር የሚደብር ነው፡፡ ኢንቱዬን ደግሞ ደፍሬ እንደዚህ ያሉ ቦታዎች ላስገባት አልችልም፡፡
‹‹ኢንቱዬን Where ever it is የአእምሮ ሀኪም ያለበት ቦታ እንውሰዳት፡፡ በአንድ ኪኒን እኮ በቀላሉ control ሊደረግ የሚችል ሊሆን ይችላል፡፡ ደግሞ በግድ ቀምተው ሆስፒታል ትቆይ አይሉህም፡፡››
‹‹እብድ ናት ተብሎ ሰው ያገላታል፡፡ አሁን እንኳን በቃ ለቀቀች እያሉ ያልሆነ አስተያየት ነው የሚያዩዋት …… አስበሽዋል እዛ ከወሰድናት ደግሞ እብድ ናት ብሎ ሰው ሁ
589 views09:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 11:39:30 ች፡፡ ልክ እንደአባቴ ስስት የማያውቃት …… ቤቷ የገባን ሁሉ አጥግባ የምትሸኝ ቸር ነበረች፡፡ የዚህችን እናት ጡት ጠብቼ አድጌያለሁ፡፡ በድሎቱም በችግሩም ጊዜ ከህመሟም ጋር እየታገለች በፈገግታዋ ልታክመን ሞክራለች፡፡ ይህቺ ሴት የማጠቢያ አልጋው ላይ አስተኝተው የሚያገላብጧት …… ለእኔና ለኢንቱ የአባታችን ማስታወሻ ብቸኛ ዋርካችን ነበረች፡፡ አንዳንዴ ወደ ሰማይ ቀና ብዬ ‹‹ግን የምታደርገው ነገር ልክ ነው? …… ድሀ ላይ መበርታትህ ፍትህ ነው?›› እያልኩ ፈጣሪን መሞገት ያሰኘኛል፡፡ መከራን ሁሉ እኛ ላይ …… ድሎትን ሁሉ ሌላ ላይ ያደረገበት ምክንያት አይገባኝም፡፡ አሁን እናትም አባትም የለኝም፡፡ እናቴን መከፈን ሲጀምሩ ሳይ አምርሬ አለቀስኩ፡፡ ይኼ ከፈን የስንብት ልብስ ነው፡፡ ከዚህ ቀደም አባቴ ለብሶት አይቻለሁ፡፡ እሱን ልብስ ከለበሰ በኋላ ተመልሶ አልመጣም፡፡ እማዬ ተከፍና ቃሬዛው ላይ ተደረገች፡፡ ጋሽ አብዱረዛቅ ‹‹በሉ በሉ ሬሳ ማቆየት አይወደድም! ቶሎ ቤተሰቦቿ ይሰናበቷትና እንሸኛት፡፡›› አሉ፡፡ ጋሽ አብራር ግራ እየተጋቡ ‹‹ኢቦዬ ኢንቲሳሬ የታለች?›› አሉኝ፡፡ ራሴን ለማረጋጋት ሞክሬ ልደውልላት ስልኬን መነካካት ስጀምር ለቀስተኛው ድምፁን ከፍ አድርጎ ሲያለቅስ መሰማት ጀመረ፡፡ ሁላችንም ምን ተፈጥሮ ነው በሚል ወደ ቅያሱ አፈጠጥን፡፡ የአይኔ ማረፊያ በእጇ የተጠቀለለ ፖስታ ይዛ ብቅ አለች፡፡ ከጀርባዋ የሰፈራችን ልጆች ሰሚራና ሙሀባ ይከተሏታል፡፡ እያለቀሰች አልነበረም፡፡ እየሆነ ያለውን በቅጡ የተረዳች አትመስልም፡፡ ቃሬዛው ላይ በአቡጀዴ የተጠቀለለ ሰው ስታይ ፊቷ ወደ ፍምነት እየተለወጠ ተጠጋች፡፡ የእማዬ ፊት ክፍት ነበር፡፡ እሷ መሆኗን እንዳረጋገጠች ተዝለፍልፋ ወደቀች፡፡ ሙሀባ አፈፍ አድርጎ ከጎኔ አስቀመጣት፡፡ ጋሽ አብዱረዛቅም ማንባት ጀመሩ፡፡ ሰሚራ ሰውነቷ ላይ ውሀ አድርጋላት ስትነቃ መለፍለፍ ጀመረች፡፡
‹‹ኢቦዬ …… እየው እየው ብር እኮ አግኝቻለሁ፡፡ ሀኪም ቤት ውሰዷት እሺ!?›› ፖስታውን ከፍታ አሳየችኝ፡፡ እየተንሰቀሰቅኩ ማልቀስ ጀመርኩ፡፡
‹‹ደሞ ለምንድነው ነጭ የምታለብሷት? ቆንጆ ልብስ አልብሷት እንጂ! ግን ለምንድነው እናንተ ያለበሳችኋት? የእኔ እናት አይደለች እንዴ? ምን አገባችሁ? ……››
አቅፌያት መንሰቅሰቅ ጀመርኩ፡፡ ኢንቱ ጮክ ብላ ትስቃለች፡፡
‹‹ሸወድኳችሁ …… ሸወድኳችሁ፡፡›› አለችና ወደ እማዬ ተጠግታ ‹‹እማ ተነሽ በቃ ቤት እንግባ እዚህ ይበርድሻል፡፡ ይበርደኛል ትይኝ አልነበር እንዴ?!›› አለች፡፡ አቅፌ ወደ ድንጋዩ ይዣት ተመለስኩ፡፡
‹‹ለምን የሚበላ ገዝተህላት አትመጣም?›› ትዘባርቃለች፡፡
ጋሽ አብራር እናቴን እንድሰናበት ጠሩኝ፡፡ ወደ ሬሳዋ ሄጄ ግንባሯን ሳምኳት፡፡ ኢንቱዬም ተከትላኝ ግንባሯን ሳመቻትና ‹‹ካንተ በላይ ነው የሳምኳት!›› አለችኝ፡፡ አንዳንዴ እማዬን በደንብ በሳመ እንፎካከር ነበር፡፡ አሁንም እየተጫወትን ሳይመስላት አይቀርም፡፡ ሀሚዱ፣ ፈረጃ፣ ከድርና ሚስባህ በአራቱ የቃሬዛው መሸከሚያ ጎኖች በኩል ቆመው፤ ቃሬዛውን በጋሽ አብዱረዛቅ ትዕዛዝ ሰጪነት ተሸከሙ፡፡ ጋሽ አብዱረዛቅ ከፊት እየመሩ እማዬን ይዘዋት መውጣት ሲጀምሩ ኢንቱ መንገድ ዘጋችባቸው፡፡
‹‹እናቴን ወዴት ልትወስዷት ነው?›› ጮኸች፡፡
ጋሽ አብድረዛቅ ከፊት ለፊታቸው ቆማ የምታንባርቅባቸውን ኢንቲሳርን እየተመለከቱ አለቀሱ፡፡
‹‹እርሶ ጋሽ አብዱረዛቅ የሚባሉ ሰውዬ ግን አላበዙትም እንዴ? አሁን ባለፈው የሸረፋን እናት እንደዚህ ወስደው መች መለሷትና ነው የኛን እናት የሚወስዱት? …… እናቴን አስቀምጡ! አስቀምጡ! አንተ ኢቦ አስቀምጧት በላቸው እንጂ!›› እየተንሰቀሰቀች ማልቀስ ጀመረች፡፡
አማራጭ ስላልነበራቸው በጉልበት ወደ ቤት እንድትገባ አደረጉ፡፡ ጋሽ አብዱረዛቅና ጋሽ አብራር ሴቶቹ ኢንቲሳርን እንዲጠብቁ አደራ ብለው ወንዶቹ በሙሉ ሬሳውን ተከትለን ወጣን፡፡ ከሰፈራችን ስንወጣ ያቺ ከኋላ ክፍት የጃጀች ፒክአፕ መኪና ቆማ እየጠበቀችን አገኘናት፡፡ ሸምገል ሸምገል ያሉት መኪናዋ ውስጥ ገቡ፡፡ እነሀሚዶ እማዬን ከኋላ ጭነው ጠርዙ ላይ ዙሪያውን የቻለውን ያህል ሰው ጭነን ወደ አለምባንክ መስጂድ ሄድን፡፡ የቻሉ በባጃጅ እንዲከተሉን …… ያልቻሉ ደግሞ ቀብር ቦታ እንዲጠብቁን ጋሽ አብዱረዛቅ አሳሰቡ፡፡ አለምባንክ መስጂድ ስንገባ አስር ሰዓት ደርሶ ስለነበር ሰጋጁ ወደ መስጂዱ ብቅ ማለት ጀመረ፡፡ እኔ ከነፈረጃ ጋር ተጣጥቤ ወደ ውስጥ ገባሁ፡፡ የአስር ሰላት እንደተሰገደ ኢማሙ የሞተ ሰው መኖሩን በመናገር ሰጋጁ እንዳይወጣ አሳሰቡ፡፡ እነሀሚዱ እማዬን ተሸክመው ከኢማሙ ፊት አስቀመጧት፡፡ ኢማሙ ወገቧ ጋር ቆመው በሟች ላይ የሚሰገደውን ስግደት ምዕመኑን አስከትለው ፈፀሙ፡፡
ወደ አንፎ መቃብር ስንመለስ አብዛኛው ሰው ቀድሞን ደርሶ እየጠበቀን ነበር፡፡ አባዬም የተቀበረው እዚህ ነው፡፡ መስጂድ መምጣት ያልቻሉት እዚያው ከሰገዱባት በኋላ ወደተቆፈረላት ጉድጓድ ተወሰደች፡፡ ልክ እንደዚሁ አባቴም ተመሳሳይ ጥልቀትና ስፋት ባለው ጉድጓድ ውስጥ ተቀብሯል፡፡ ከዚያ በኋላ ወደ ቤት አልተመለሰም፡፡ ለቀስተኛው በአንድ ድምጽ ቁርዓን ያነበንባል፡፡ ሀሚዱና የቀብር ቆፋሪው ጉድጓዱ ውስጥ ገቡ፡፡ ሌሎቹ እማዬን ከቃሬዛው ላይ አንስተው አቀበሏቸው፡፡ ከውስጥ ያሉት እማዬን መሬቱ ላይ አደላድለው ካስተኟት በኋላ እርሷን ያስገቡበት የቀብሩ የጎን ኪስ በብሎኬትና በጭቃ ተመረገ፡፡ እኔ እየተንሰቀሰቅኩ አለቅሳለሁ፡፡ ሌላው በአንድ ድምፅ ቁርዓኑን እያነበነበ ወደ ጉድጓዱ አፈር ይመልሳል፡፡ መንሰቅሰቄ በረታ! እውነታውን አውቀዋለሁ፡፡ እናቴን ከዚህ በኋላ ማየት አልችልም፡፡ አባቴም እናቴም ባዶ ቤት ትተውን ሄዱ፡፡ ልፋቷ ሁሉ መና ከቀረባት አንድ እህቴ ጋር ብቻችንን መቅረታችን ነው፡፡
ጉድጓዱ በአፈር ተሞልቶ ቀብርተኛው ቦታውን ለቅቆ መሄድ ጀመረ፡፡ እኔ ቆሜ አያታለሁ፡፡ ‹‹ከዚህና ከኛ ቤት የቱ ይመቻል?›› ብዬ ልጠይቃት እከጅላለሁ፡፡ ጋሽ አብራር እጄን ይዘውኝ መመለስ ጀመርን፡፡ ቤት ስንደርስ በጣም ብዙ ለቀስተኛ ተሰብስቦ ጠበቀን፡፡ በራችን ላይ ሸራ ተወጥሮ አግዳሚ ወንበር ተደርድሯል፡፡ ሰዉ በሀዘን ድባብ ተውጦ ሰፈራችን ፀልማለች፡፡ ሴቶቹ ያዘጋጁትን ምግብ ለለቀስተኛው ያቀርባሉ፡፡ ሁሉም በየተራ ከአጠገቤ እየተቀመጠ ሊያፅናናኝ ይሞክራል፡፡ አመሻሹን አቤላ መጣ፡፡ እንዴት እንደሰማ አላውቅም፡፡ እሱን ሳይ እንባዬ አገረሸ፡፡ አቅፌው መንሰቅሰቅ ጀመርኩ፡፡
ከቀብር ከተመለስኩበት ሰዓት ጀምሮ ኢንቱዬን አንዴ እንኳን አላየኋትም፡፡ እሷም በሴቶቹ ተከብባ ቤት ውስጥ ተቀምጣ እንደሚሆን ገምቻለሁ፡፡ ግርግሩ ጥሩ ነው፡፡ ለጊዜውም ቢሆን የመከራውን ህመም ከመጋፈጥ ያዘገያል፡፡ እናቴ የሌለችበትን ቤት የማየትን ህመም …… ዘወትር የምትተኛበትን ቦታ ባዶ ሆኖ የመመልክትን ህመም …… የአባዬን ማስታወሻ የማጣትን ህመም …… ‹‹አባቴ ቢሞትም እናቴ በህይወት አለች፡፡›› ብሎ የአባትን ሞት መሸንገያ የማጣትን ህመም …… ለጊዜውም ቢሆን በግርግሩ ተውጠን እናመልጠዋለን፡፡ ሰው ያለን ሰው ያለን ይመስለናል፡፡ ግን እንሸሸው ይሆናል እንጂ አናመልጠውም፡፡ ምክንያቱም ቀናት መቁጠራቸውን አያቆሙም!
.
ይቀጥላል ……
534 views08:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 11:39:29 ከተራራው ላይ
ክፍል አስራሁለት
(ፉአድ ሙና)
.
‹‹ጥርሴን አልስቅበት፣ መች አርፌ ከእንባ፣
እጠቀመው መስሎት፣ ይኸው ጥርሴ አነባ!
የጥርስ እንባ እንዴት ነው?››
***
የመጀመሪያውን ገፅ ከፍቼ ማንበብ ጀመርኩ፡፡
‹‹ኢቦዬ …… ለእኔ ከሁሉም በላይ ሽንፈት አንተ ገንዘብ እንደሌለኝ ማወቅህ ነው፡፡ ግን ንገሪኝ ካልከኝ ምን አደርጋለሁ? እነግርሀለሁ፡፡ የነገርኩህ ግን በአንድ ሳምንት ሁሉም ስለሚስተካከል ነው፡፡ ዳግም ሆዳችንን የሚርበው አይመስለኝም፡፡ ሁለት ወዶ አይሆንም አይደል የሚባለው?›› ፅሁፉ ቅኔ ሆነብኝ፡፡ ባለፈው ገንዘብ እንደሌላት ስለነገረችኝ በጣም ከፍቷታል ማለት ነው? ወደ ቀጣዩ ገፅ ተሻገርኩ፡፡
‹‹ኢቦዬ …… አብዱኬ እንደታሰረ ስሰማ በጣም አለቀስኩ፡፡ ለምን የተሰረቀ ሞባይል ማሻሻጥ እንደፈለገ አልገባሽ ብሎኛል? ገንዘብ ቸግሮት ነው እንዳልል ቢቸግረው ይነግረኝ ነበር፡፡ ተጨማሪ ፍራንክ አመጣለሁ ብሎ የባሰ የጋሼና የአባይዬን ጉሮሮ ዘጋ፡፡ እስከ ሰኞ ድረስ የምንበላውን አብዱኬ መሸፈኑ አይቀርም ብዬ አስቤ ነበር፡፡ በእርግጥ ባይታሰር አይርበንም፡፡ እሱንስ እየደበደቡት ይሆን ወይ ብዬ ሳስብ ሆድ ይብሰኛል፡፡ ምን ማድረግ እንዳለብኝ አላውቅም፡፡ እማዬን ግን ከዚህ በላይ እንዲርባት አልፈቅድም፡፡ ቢያንስ ደህና ምግብ በልታ መሞት አለባት፡፡ …… ቀኑ አልፈጥን ብሎኛል፡፡››
ኢንቱ አብዱኬ ሞባይሉን ያመጣው በእኔ ምክንያት እንደሆነ ብታውቅ ምን ትለኝ ይሆን? ፀፀት ተሰማኝ፡፡ አብዱኬ በእኔ ሰበብ ለዚህ ሁሉ በመብቃቱ ራሴን ወቀስኩ፡፡ ደብተሩን ገልጬ የመጨረሻውን ፅሁፍ አየሁት፡፡ ትንሽ ረዘም ይላል፡፡ ማንበብ ጀመርኩ፡፡
‹‹ኢቦዬ …… በህይወቴ እንደዚህ እየቀፈፈኝ የፃፍኩበት ቀን ያለ አይመስለኝም፡፡ አዎ የለም! ከልጅነቴ አዕምሮዬ ላይ የተቀረፀ ነገር አለ፡፡ ክብርን መጠበቅ! ማንም ሰው ያለ ፍላጎቴ ምንም እንዲያደርገኝ አለመፍቀድ! …… ጥቅምን ፍለጋ ራሴን የምሸጥ አይነት ሴትም አይደለሁም፡፡ ብሆን ኖሮ ድሮ ድሮ የሀብታም ቅምጥ ሆኜ ነበር፡፡ ግን ስለማልፈልግ ጫናውን ሁሉ ተቋቁሜ እዚህ ደርሻለሁ፡፡ ይኼ መድረሻ ይሁን መነሻ አላውቅም፡፡ ግን የአንዱ ምዕራፍ መደምደሚያ የሌላኛው መጀመሪያ ይመስለኛል፡፡ ጥሩ አይደለም አውቃለሁ፡፡ እንደዚያም እያልኩ አመታትን በአቋሜ ፀንቻለሁ፡፡ አሁን ግን አንተና እማዬ ተራባችሁብኝ፡፡ ከሁሉም በላይ እማዬን ከዚያ ህመሟ ጋር በረሀብ ስትቆላ መመልከት አልቻልኩም፡፡ ለእናቴ ብዬ ክብሬን ብረግጠው ፀፀቱ ብዙ አይመስለኝም፡፡
ኢቦዬ …… ባለፈው ሳምንት ያለኝ ገንዘብ እያለቀ ሲመጣና ከስራውም ተስፋ ስቆርጥ የቀድሞው አሰሪዬ ጋር ደወልኩለት፡፡ ፀባዬን እንደማስተካክልና መልሶ እንዲቀጥረኝ ለመንኩት፡፡ ግን ለቅሶዬ ግድ አልሰጠውም፡፡ በአጭሩ ‹‹የምፈልገውን ታውቂያለሽ ……… እሱን እሺ ካልሽ እንደሰራተኛ ሳይሆን እንደአሰሪ ትኖሪያለሽ!›› አለኝ፡፡ ከዚህ በላይ የቀድሞዋን ኢንቲሳር መሆን አልቻልኩም፡፡ ተስማማሁ፡፡ ቅዳሜ ይዞኝ ወደ አዳማ እንደሚሄድና አድረን እንደምንመለስ ነገረኝ፡፡ ቀድሞ ትንሽ ብር ሊሰጠኝ ይችል እንደሆነ ጠየቅኩት፡፡ ‹‹ሳልነካሽ አላምንሽም …… በኋላ ሀሳብሽን ብትቀይሪስ?›› አለኝ፡፡ ያለሁበትን ሁኔታ ላስረዳው ሞከርኩ፡፡ ግን ‹‹ፀባይሽ አይያዝም ከሰጠሁሽ በኋላ እምቢ ትይኛለሽ!›› አለኝ፡፡ ያለኝ አማራጭ ቅዳሜ ከእሱ ጋር ሄጄ ድንግልናዬን ማስረከብ ነው፡፡ እንደዚያ ካደረግኩ በፈለግኩት ሰዓት የምፈልገውን ያህል ገንዘብ ይሰጠኛል፡፡ እንደተስማማሁ ነገርኩት፡፡ ሰፈር ድረስ መጥቶ እንደሚያነሳኝ ነገረኝ፡፡ ከዚህ በኋላ ሆዳችንን አይርበውም፡፡ በረሀብ እንቅልፍ አጥተን አናድርም! ኢቦዬ ይኼ ማንም በእኔ ቦታ የቆመ ሰው የሚያደርገው ነገር ነው፡፡ የቻልኩትን ያህል ታግሻለሁ፡፡ ከዚህ በኋላ ግን በቃ! ሴትነቴን ለአሰሪዬ ማስረከብና እሱን ማስደሰት አለብኝ፡፡ እሱን ሳስደስት እናንተ ሳይርባችሁ የተሻለ ኑሮ ትኖራላችሁ፡፡ ከመሞት …… መሰንበት ይሻላል!››
በደመነብስ ማስታወሻ ደብተሩን ወደ ቦታው ወርውሬ ከቤት ወጣሁ፡፡ እየሮጥኩ ከሰፈራችን ወጥቼ ባጃጅ ተራ ደረስኩ፡፡ ለምን እንደወጣሁ …… ለምን እንደምሮጥ …… ወዴት እንደምሄድ አላውቅም፡፡ ባጃጅ ተራ ስደርስ ከብዥታዬ መንቃት ጀመርኩ፡፡ ከአይኔ የእንባ ዘለላዎች መንታ መንታ እየሆኑ ይፈሳሉ፡፡ ከዚህ በኋላ ምንም ፈጥሬ እንደማላተርፋት ገባኝ፡፡ እየተመለስኩ ያገኘኋት ድንጋይ ላይ ተቀምጬ ለረዥም ሰዓት አለቀስኩ፡፡ እማዬ ቁርስ አለመብላቷ ትዝ ሲለኝ እንባዬን ጠራርጌ ወደ ቤት መመለስ ጀመርኩ፡፡
የቤታችን ቅያስ ጋር ስደርስ የጩኸት ድምፅ ተሰማኝ፡፡ ቁልቁለቷን ወርጄ ቤታችን ጋር ስደርስ የሰፈራችን ሰዎች እየጮኹ እያለቀሱ ተመለከትኩ፡፡ ምን እንደተፈጠረ ለማየት በመሀል እየሰነጠቅኩ በር ጋር ደረስኩ፡፡ ጋሼ በር ላይ ቆሞ ያለቅሳል፡፡ መምጣቴን ሲመለከት አቅፎኝ ማልቀስ ጀመረ፡፡
‹‹ጋሼ ምንድነው? ምንድነው?›› እያልኩ ከእቅፉ ወጥቼ ወደ ቤት ገባሁ፡፡ ወንዶቹ እማዬን ከበው እየተነሱና እየፈረጡ የሚያለቅሱትን ሴቶች ለመያዝ ይሞክራሉ፡፡ የሆነ ሰው መስኮቱን ሲከፍተው ብርሀኑ እማዬ ላይ አረፈ፡፡ አይኖቿ ፈጠዋል፡፡ ግራ ተጋባሁ፡፡ ቅድም ስቀሰቅሳት እንዲህ ሆና ነበር? ከራሴ ጋር ተወዛገብኩ፡፡ ሰውነቴ ከድቶኝ ተዝለፍልፌ ልወድቅ ስል ጠንካራ እጆች ደግፈው አስቀመጡኝ፡፡ በሰላም የወጣሁበት ቤት በሰዓታት ውስጥ ለቅሶ ቤት ሆኖ ሲጠብቀኝ በእውነት ይሁን በቅዠት አለም ያለሁት ማወቅ ተሳነኝ፡፡
ትንሽ ቆይቼ ‹‹ትናንት እኮ ከእነምህረት ጋር ስታወራ …… ስትመርቃቸው ነበር!›› አልኩ፡፡ ጋሼ አቅፈው ሊያረጋጉኝ ሞከሩ፡፡
‹‹አንተ ወንድ ነህ! ጠንከር በል! አንተ ካልጠነከርክ እህትህን ማጠንከር አትችልም!›› ጋሼ ትከሻዬን እየወዘወዙ ሊያበረቱኝ ይሞክራሉ፡፡ ትንሽ ካለቀስኩ በኋላ ወደ እማዬ ተጠግቼ ግንባሯን …… እጆቿን …… እግሯን ሳምኩኝ፡፡ ጋሽ አብዱረዛቅ ትከሻቸው ላይ አቡጀዴ አጣፍተው ሲመጡ ሳይ የእናቴ መሞት እውነት መሆኑ ገባኝ፡፡ አባቴ ሲሞትም ያጠቡት እርሳቸው ነበሩ፡፡ አሁን በጣም አርጅተዋል፡፡ ሆኖም ከሰፈሩ ሙስሊም ቤት ውስጥ የሞተ ሲኖር ለማጠብ የሚጠሩት እሳቸው ናቸው፡፡ ወደ ቤት እየገቡ ‹‹በሉ ግርግር አያስፈልግም! አልቅሳችሁ ልትመልሷት ነው?!›› አሉ፡፡ የለቀስተኛው ድምፅ ረገበ፡፡ የሰፈራችን ሰዉ ሁሌ ሞት ሲኖር ስለሚመጡ የሞት መልዓክ አድርጎ ያስባቸዋል መሰል ይፈራቸዋል፡፡ ሰዉ ራቅ እንዲል ተደርጎ ትንሽዬዋ የሬሳ ማጠቢያ የብረት አልጋ በራችን ፊት ለፊት ተዘረጋች፡፡ ጋሽ አብዱረዛቅ አጥበው እስኪጨርሱ ከቤተሰብ በቀር ሁሉም እንዲርቅ ተናገሩ፡፡ ሁሉም ሰው ደጃፋችንን ለቅቆ ትጥበቱን በማይመለከትበትና ጋሽ አብዱረዛቅ በማይመለከቱት ቦታ ሰፈረ፡፡ ከጋሽ አብዱረዛቅ ጋር የቀረነው እኔ፣ ጋሼና ሀሚዱ ብቻ ነበርን፡፡ ሀሚዱ ሰውነቱ ግዙፍ ስለሆነ ጋሽ አብዱረዛቅ ለቅሶ ባለ ቁጥር ሬሳውን በመሸከም እንዲያስተካክልላቸው ይዘውት ይዞራሉ፡፡ አሁን ከእሳቸው እኩል ስርዓቱን በደንብ ያውቃል ይባላል፡፡
ሀሚዱ እማዬን ከአንድ ቀን በላይ ልትተኛበት ካልታደለችበት አዲሱ ፍራሿ ላይ እንደህፃን ታቅፎ ወደ ቃሬዛ ካሻገራት በኋላ ከጋሼ ጋር ተሸክመው ይዘዋት ወጡ፡፡ ከኋላቸው እየተከተልኩ የሚያደርጉትን አያለሁ፡፡ ማጠቢያው ላይ አስተኝተዋት ማጠብ ሲጀምሩ ደጃፋችን ላይ ያለችዋ ድንጋይ ላይ ተቀምጬ እያለቀስኩ መመልከት ጀመርኩ፡፡ አሁን በድን ሆና የማጠቢያ አልጋው ላይ የተኛችው ሴት ከአመታት በፊት ዘመደ-ብዙ ነበረ
475 views08:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 15:43:07 @hayu0913 asteyayet
220 viewsedited  12:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 15:42:43 ላ ……›› ብዬ ቀና አልኩ፡፡ ከአቤል ኋላ ማህሌት …… ምህረት …… ቤተልሔም ……… ሁሉም የፌሎው ልጆች በእጆቻቸው ለመያዝ የከበዳቸውን ያህል በኩርቱ ፌስታል ተሸክመዋል፡፡ ሁለት ትልልቅ ፍራሾች መሬቱ ላይ ተቀምጠዋል፡፡ የተጠቀለለ ወለልም የቤታችንን ግርግዳ ተደግፎ ቆሟል፡፡
‹‹Surprise!›› አሉ በአንድነት! እንባዬ አይኔን ሞላው፡፡
‹‹አቤላ ምንድነው?›› አልኩት፡፡ የማየውን ማመን ከብዶኛል፡፡ እንባዬ ከአይኔ አመለጠ፡፡ ማህሌት ተጠመጠመችብኝ፡፡ አቅፋኝ ‹‹ስልክህን ያላነሳነው Surprise ልናደርግህ ፈልገን ነው፡፡›› አለችኝ፡፡ ‹‹ሰው ናቸው መልዓክ?›› ማመን አቃተኝ፡፡
‹‹ተቃቅፋችሁ ትቆማላችሁ ወይስ ታስገቡናላችሁ?›› አቤላ እየሳቀ ያየናል፡፡ በሩን በደንብ ከፍትኩትና ከማህሌት ጋር ወደ ውስጥ ገባን፡፡ ሁሉም በተራ በተራ ገቡ፡፡ ብርድ ልብሱን አጣጥፌ አነሳሳሁት፡፡ መስኮቱን ስከፍተው ቤቱ በብርሀን ተሞላ፡፡ ሁሉም ደረታቸው ላይ በትንሹ የቤተ-ክርስቲያናቸው አርማ ያለበት ነጭ ቲሸርት ለብሰዋል፡፡ ሆዳቸው አካባቢ በትልቁ ‹‹Together …… we can!›› እና ‹‹በአንድነት እንችላለን!›› የሚሉ ፅሁፎች ከላይና ከታች ተፅፈዋል፡፡ ከስር ደግሞ ሴቶቹ ጥቁር ሰማያዊ ቀሚስ …… ወንዶቹ ጥቁር ሰማያዊ ጂንስ ሱሪ ለብሰዋል፡፡ እማዬን ሰላም ብለዋት ተቀመጡ፡፡
ማህሌት ፍራሹ ላይ እየተቀመጠች ‹‹አብርሽዬ …… ለመገዛዛት ስንዞር ምሳ አልበላንም! I am hungry! Please እንብላ!›› አለች፡፡ አቤላ ያመጡትን ምግብ በሁለት ምድብ ከፍሎ ማቀራረብ ጀመረ፡፡ ምህረት ከእናቴ ጋር ታወራለች፡፡ የምግቡ ሽታ ሆዴን አላወሰው፡፡ እኔ፣ እማዬ፣ ማህሌት፣ አቤላ፣ ምህረትና ሁለቱ ወንዶች በአንድ ቡድን …… የተቀሩት ደግሞ በሌላ ሆነው መብላት ጀመርን፡፡ ሚቾዬና ምህረት እማዬን በላይ በላዩ ያጎርሷታል፡፡ በጣም ርቦኝ ስለነበር አንድ እንኳን ሳላወራ ለእነሱ ንግግር አንገቴን ብቻ እየወዘወዝኩ ወጠቅኩ፡፡ የምግቡ አይነት ምን እንደሆነ መለየት የጀመርኩት ስጠግብ አካባቢ ነው፡፡
በልተን እንደጨረስን ማህሌት ኮዳዋን አንስታ ውሀ እየተጎነጨች ‹‹Guys! Let us change this house! ኢንቲሳር ስትመጣ totally ሌላ ቤት የገባች እንዲመስላት ነው የምናደርገው!›› አለች፡፡
እማዬን አዝዬ እነአብዱኬ ቤት አስገብቻት ተመለስኩ፡፡ ሙሉ የቤታችንን ኮተት ከቤት ውጪ አወጣነው፡፡ የውስጡን የተሰነጣጠቀ ግድግዳ ክሬም ቀለም ቀባነው፡፡ አቤላ ልምድ ስለነበረው ብዙ ጊዜ አልወሰደብንም፡፡ አዲሱ ሰማያዊ ወለል ተዘረጋ፡፡ በጣም ያምር ነበር፡፡ አዳዲሶቹ ፍራሾች ቀለም እንዳይነካቸው ከግድግዳው ፈቀቅ እየተደረጉ ተዘረጉ፡፡ በጣም ከፍታ አላቸው፡፡ ብርድ ልብሶቻችንን ፍራሾቹ ላይ አነጠፍን፡፡ ቤቱ ቀለል አለ፡፡ ትራሶቹን በስርዓቱ ደረደርን፡፡ አዲስ ቤት ይመስል ነበር፡፡ ማህሌት አንድ ፍሬም ከተጠቀለለበት ማሸጊያ አውጥታ ከፊት ለፊት ግድግዳው ላይ ሰቀለችው፡፡
ፍሬሙ ውስጥ ያለው ፅሁፍ ‹‹ሁሉም ቀን የራሱ መልካም ስጦታ አለው!›› ይላል፡፡
‹‹ቢያንስ ሁሌ ከእንቅልፍህ ስትነሳ ይኼን ስታይ positive positive side እያሰብክ እንድትውል ይረዳሀል!›› አለች፡፡ ፈገግ አልኩላት፡፡
ያመጡትን አስቤዛ በአይነት በአይነቱ ጥግ ላይ ደረደሩት፡፡ ቢያንስ ለአንድ ወር ምግብ የሚያሳስበን አይመስለኝም፡፡ ከጨረስን በኋላ ሴቶቹ እራት ሳንሰራላችሁ አንሄድም ብለው ግግም አሉ፡፡ ከሰሉን አቀጣጥዬ መክተፊያና ድስቱን ሰጠኋቸው፡፡ እየመሸ ነበር፡፡ እማዬን ይዣት ወደ ቤት ስገባ ያየችውን ማመን ከበዳት፡፡ እያለቀሰች መረቀቻቸው፡፡ ወጡን ሰራርተው ሲጨርሱ፤ እማዬ እንዲሻላት ፀልየውላት ለመሄድ ተነሱ፡፡
አብረን እየተጫወትን እስከመኪናቸው ድረስ ሸኘኋቸው፡፡ ልንለያይ ስንል ሁሉንም ከልብ አመሰገንኳቸው፡፡ ማህሌት ከቦርሳዋ ውስጥ የተጠቀለለ አስር ሺህ ብር አውጥታ እየሰጠችኝ ‹‹ይኼ ደግሞ ለአስፈላጊ ነገር ይጠቅማችኋል!›› አለችኝ፡፡
‹‹ሚቾ ……››
‹‹Come on አብርሽ! ይኼን እኮ ነው Social responsibility የምንለው! አንተ ደግሞ አሮጌውን ፍራሾች ካንተ በላይ ለሚያስፈልገው ሰው ስጥ! አንተ ስታስረዳን እንቢ ብለናል እንዴ? አላልንም! አንተ እውቀት አለህ ባለህ እውቀት አገዝከን! እኛ ደግሞ just ለእንደዚህ አይነት purpose ባጠራቀምነው ብር Surprise አደረግንህ! Just take it! It is normal! We are friends!››
‹‹ባለፈው ፈጣሪ ላንተ የሰጠህ ጥሩ ነገር ብለሽ ስትቆጥሪ ግን እኔን ማለት ረስተሻል!›› ሳቀች፡፡
ገንዘቡን ተቀብዬ አቀፍኳት፡፡ ሁሉንም አቅፌ አመሰገንኳቸው፡፡
ማህሌት ‹‹ሁሌም ከጎንህ ነን! ደግሞ አብዱኬን next days ሄደን እንጠይቀዋለን፡፡ እሺ?›› ብላ ጉንጬን ስማ ወደ መኪናዋ ገባች፡፡ ስለአብዱኬ አቤላ እንደነገራት ገባኝ፡፡ መኪናዎቻቸው ከአይኔ እይታ እስኪሰወሩ ድረስ ቆሜ ተመለከትኳቸው፡፡
ለኢንቱዬ ደውዬ ልነግራት ፈለግኩና ስትመጣ አይታው ብትደመም ይሻላል ብዬ ተውኩት፡፡ ወደ ቤት ስገባ እማዬ ተኝታለች፡፡ አስተካክዬ አለበስኳት፡፡ ሰዓቱ ከምሽቱ ሁለት ሰዓት ተኩል ይላል፡፡ ኢንቱዬን ማደር አለማደሯን ልጠይቃት አሰብኩና ወጥቼ ካርድ ገዝቼ ተመለስኩ፡፡ ስደውል ስልኳ ዝግ ነው፡፡ ሶስት ሰዓት ተኩል ሲሆን እንደምታድር ገምቼ ራት አቀራረብኩና እማዬን ቀስቅሻት በላን፡፡
አራት ሰዓት አካባቢ ተመቻችቼ ተኛሁ፡፡ እንቅልፍ የበላ ሰው ይወዳል መሰለኝ ይዞኝ ነጎደ፡፡ ጠዋት ከእንቅልፌ ተነስቼ ውጪ ላይ ስፖርት ሰራሁና ቤት ገብቼ ለቁርሳችን ሻይ ማፍላት ጀመርኩ፡፡ ሻይ እያፈላሁ የኢንቱን ስልክ ደጋሜ ሞከርኩ፡፡ አይሰራም፡፡ ጭንቅ ጭንቅ አለኝ፡፡ የያስሚን ስልክ ስለነበረኝ እሷ ጋር ደወልኩኝ፡፡ የሷ ስልክ ይሰራል፡፡
ያስሚን ስልኩን አንስታ ‹‹ወዬ ኢንቱ ……›› አለች፡፡ ኢንቱ ካርድ ሲያልቃት ብዙ ጊዜ በእኔ ስልክ ትደውልላት ነበር፡፡ ትንሽ ግራ ገባኝ፡፡
‹‹ያስሚን …… ኢንቱ አይደለሁም …… ወንድሟ ኢብራሂም ነኝ፡፡››
‹‹ኢቦ እንዴት ነህ? እሷ መስላኝ እኮ ነው፡፡››
‹‹ኢንቱ አንቺ ጋር አልመጣችም እንዴ?›› የልቤ አመታት ሲፈጥን ተሰማኝ፡፡
‹‹አዎ ኢቦዬ እኔ ጋር አይደለችም፡፡ ስልኳ እንቢ ብሎህ ነው?››
‹‹ሰርግ የለም እናንተ ጋር?›› ግራ ተጋባሁ፡፡
‹‹ኢቦ ደግሞ የምን ሰርግ ነው? ምንድነው ኢንቱ ደህና አይደለችም እንዴ?››
‹‹ደህና ናት!›› በአጭሩ ተሰናብቼ ስልኩን ዘጋሁት፡፡ አዎ ደህና ናት ከሚለው ውጪ ምንም መስማትም መናገርም አልፈልግም፡፡
ስልኳን ያለእረፍት ደጋግሜ ሞከርኩት አይሰራም፡፡ እማዬን ቁርስ እንድትበላ ልቀሰቅሳት ብሞክር አትነሳም፡፡ ማታ እንቅልፍ አጥታ ይሆናል ብዬ ቁርሱን አቀራርቤ እስክትነሳ መጠበቅ ጀመርኩ፡፡ ሰዓቱ ከረፋዱ አራት ሰዓት ገደማ ይሆናል፡፡ የኢንቱን ስልክ ደጋግሜ እየሞከርኩ ቀና ስል የኢንቱን ማስታወሻ ደብተር ተመለከትኩ፡፡ ምናልባት የፃፈችው ነገር ካለ ብዬ ደብተሩን ለመክፈት መርፌ ቁልፌን መፈለግ ጀመርኩ፡፡ መርፌ ቁልፌ ጠፍታ ነበር፡፡ መርፌ ቁልፍ ገዝቼ ተመለስኩና ደብተሯን ከፈትኳት፡፡ ከባለፈው በኋላ የፃፈችው ካለ እየገለጥኩ መፈለግ ጀመርኩ፡፡ መጨረሻ ላይ ያላነበብኳቸውን ሶስት ገፆች አገኘሁ፡፡
.
ይቀጥላል …
219 views12:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 15:42:17 ከተራራው ላይ
ክፍል አስራአንድ
(ፉአድ ሙና)
.
‹‹መሸ ብዬ ሙሾ ሳወርድ፣ ደሞ ይነጋል፣
ነጋ ብዬ ስፈነጥዝ፣ ፈክቶ ሳይጠግብ ይጨልማል፡፡
ምን ይሻላል?!››
***
ቀኑን በረሀብ እየተቆላን አሳለፍነው፡፡ ሁለታችንንም ያሳሰበን የእማዬ ጉዳይ ነበር፡፡ በበሽታዋ ላይ ረሀቡ ሲጨመር በጣም ይጎዳታል ብለን ፈርተናል፡፡ ማታ ጋደም እንዳልን ኢንቱዬ አቅፋኝ መንሰቅሰቅ ጀመረች፡፡
‹‹ምነው ኢንቱዬ ራበሽ እንዴ?›› ፀጉሯን በእጄ እየዳበስኩ ላባብላት ሞከርኩ፡፡
‹‹ኢቦዬ …… እማዬ ፆሟን ውላ ማደሯ …… ምንም ማድረግ አለመቻሌ ……… ያማል ኢቦዬ …… ያማል …… የእሷ እኮ ከባድ ነው፡፡››
‹‹አይዞን ኢንቱዬ …… አንቺ የምትችይውን አድርገሻል፡፡››
‹‹አይዞን እሺ ኢቦዬ …… ለሁለትና ሶስት ቀን ብንራብ ነው፡፡ ደሞ ለእሱም ቢሆን ከጎረቤትም የሆነ ነገር ፈላልጌ መበደሬ አይቀርም፡፡ ከዛ ግን አይቸግረንም፡፡››
እያወራን እንቅልፋችንን ጠበቅነው፡፡ ኢንቱዬ የመራብ ልምዱ ስላላት ነው መሰለኝ ትንሽ ቆይታ አሸለባት፡፡ እኔን ግን ረዘም ያለ ጊዜ ወሰደብኝ፡፡ ስታገል ከቆየሁ በኋላ ወደ እኩለ-ለሊት ገደማ አሸለበኝ፡፡ የረሀብ ክፋቱ ለሊት መቀስቀሱ ነው፡፡ ለሊት ዘጠኝ ሰዓት ላይ በጣም ርቦኝ ነቃሁኝ፡፡ በዚህ ሰዓት በልተው የምቾት እንቅልፍ በተኙት ሁሉ ላይ ቀናሁ፡፡ ደግሞም አናደዱኝ፡፡ እንዴት እኛ ተርበን በሰላም ይተኛሉ? ለነገሩ ጥፋቱ የፈጣሪ ነው፡፡ ድምፅ ላለማሰማት እየተጠነቀቅኩ አለቀስኩ፡፡ ረሀብ በሽታ ነው፡፡ ህመም አለው …… ያንገበግባል፡፡ ሰውነት ያሳስራል፡፡ ንጋት ናፈቀኝ፡፡ ግን ሩሩሩሩቅ ነበር፡፡ ለሊቱ ብቻውን የሳምንት ርዝማኔ ነበረው፡፡ የትናንትናው እንቅልፌ ናፈቀኝ፡፡ አይኔ እንደፈጠጠ አስራሁለት ሰዓት ሞላ፡፡ ኢንቱዬም ……… እማዬም አይናቸውን ከድነው ተኝተዋል፡፡ እኔን የሚሰማኝ የረሀብ ህመም እነሱንም አሟቸው ቻል አድርገውት እንደሆነ ተሰማኝ፡፡ ኢንቱዬ ከእንቅልፏ እንደተነሳች ‹‹መጣሁ!›› ብላኝ ወጣች፡፡ ያላስሞላሁት የደብተር ማርክ ስላለ ዛሬ ትምህርት ቤት መሄድ አለብኝ፡፡
ፊቴን ተጣጥቤ ዩኒፎርሜን መለባበስ ጀመርኩ፡፡ ኢንቱ ሁለት ዳቦ ይዛ ገባች፡፡ ቆራርሰን ተቃመስነው፡፡ ኢንቱዬ ግንባሬን ስማ ‹‹አይዞን ትንሽ ቀን ነው እሺ!›› አለችኝ፡፡
እማዬን ስስማት ጉልበቷ ደረቷ ላይ ተወሽቆ ነበር፡፡ የገረጣ ፊቷን ፈገግታ ለማልበስ ሞከረች፡፡ እንደዚህ ልብ ብዬ ካስተዋልኳት ቆይቻለሁ፡፡ አይኔ ላይ የቀድሞው መልኳ ድቅን አለብኝ፡፡ ቆንጆዋ …… ደንዳናዋ እናቴ ትዝ አለችኝ፡፡ ከአሁኗ እማዬ ጋር ቢገናኙ የሚተዋወቁ አይመስሉም፡፡ ሁሉ ነገሯ ተቀይሯል፡፡ የድሮዋን እማዬን የማየው በኢንቱዬ ፊት ውስጥ ነው፡፡
ትምህርት ቤት ውስጥ ሆኜ የማስበው በምን መልኩ ገንዘብ ማግኘት እንደምችል ነው፡፡ ለመስረቅ አሰብኩ፡፡ የራበው ሰው ቢሰርቅ ሀጥያት ነው እንዴ? ለምንስ ይታሰራል? የመስረቅ ችሎታው የለኝም እንጂ ባደርገው ደስ ይለኝ ነበር፡፡ ከክፍል ልጆች ስልክ ተውሼ ማህሌት ጋር ደወልኩ፡፡ ጠራ …… ጠራ …… አነሳችው፡፡ በጣም ደስ ብሎኝ ‹‹ሄለው ሚቾ!›› አልኩ፡፡ ተቋረጠ፡፡ ደግሜ ደወልኩ …… ዘጋችው፡፡ ተበሳጨሁ፡፡ ሰው በችግር ጊዜ ካልደረሰ ደስ ባለው ሰዓት ደግሶ ቢያበላ …… መዝናናት ሲፈልግ ፒዛ ቢጋብዝ ምን ትርጉም አለው፡፡ ራስ ወዳድ እንደሆነች ተሰማኝ፡፡ ‹‹ስረጋጋ ደግሞ ምን ሆና ይሆን ?›› ብዬ ማሰብ ጀመርኩ፡፡ ዛሬ አቤላም ምሳ ይዞ አልመጣም ነበር፡፡ ይኼ ሳምንት የጨለማ ሳምንት ሆኖብኛል፡፡
ወደ ቤተል ቤተ-መፅሐፍት ሄደን ማንበብ ጀመርን፡፡ ማህሌትን እዚህ ካገኘኋት ብዬ ተስፋ አድርጌ ነበር፡፡ አልነበረችም፡፡ ምህረት ጋር የመደወል ሀሳብ መጣልኝ፡፡ ግን የእኔም የአቤላም ስልክ ካርድ አልነበረውም፡፡ ማታ ሁለት ሰዓት ሲል ወደ ቤት ተመለስኩ፡፡ በጣም ርቦኝ ነበር፡፡
‹‹ኢቦዬ ዛሬ ጨረሳችሁ አይደል ትምህርት?›› ኢንቱ አይኔን በስስት እያየች ጠየቀችኝ፡፡
አንገቴን በአዎንታ ነቀነቅኩላት፡፡ ከመተኛት ውጪ ለማውራት የሚሆን አቅም አልነበረኝም፡፡ ኢንቱዬ አለቀሰች፡፡ ተቃቅፈን እየተላቀስን ተኛን፡፡ ግን ረሀብ ብልግናውን አልተወም፡፡ ለእንቅልፍ ሊያስረክበን ሰሰተ፡፡ እንደፈጠጥን የሆዳችንን ጩኸት እያደመጥን ሰዓታት ነጎዱ፡፡ ያሸልበናል መልሶ ይቀሰቅሰናል፡፡ ክፋቱ አበሳጨኝ፡፡ ረዥሙ የረሀብ ለሊት ለረሀበ-ቀን አስረከበን፡፡ የሆነ ቅጣት ውስጥ ያለን ያለን ያህል ይሰማኛል፡፡‹‹እኛስ አድገናል …… ገና በህፃንነታቸው እየተራቡ ያሉ የሰፈራችን ህፃናት እንዴት ይሰቃዩ ይሆን? …… ወላጆቻቸው እንዴት ልባቸው ይሰበር ይሆን?›› ስለ ሰፈራችን …… ስለ ድህነት ብዙ ብዙ አሰብኩ፡፡ ‹‹ገሀነም ከዚህ ይከፋል?›› አልመስልህ አለኝ፡፡
ቅዳሜ ጠዋቱን እንደተጋደምን ማውራት ጀመርን፡፡
‹‹ስማማ ኢቦ ረሀብ እንዳይሰማን …… የሆነ ጨዋታ እንጫወት!››
‹‹ምን አይነት ጨዋታ?››
‹‹መቆነጣጠጥ! እኔ እቆነጥጥሀለሁ …… ከዛ አንተ ከኔ አስበልጠህ ትቆነጥጠኛለህ …… እኔ ደግሞ ካንተ የበለጠ እቆነጥጥሀለሁ፡፡ ስለዚህ ቁንጥጫው ሲያመን ረሀቡን እንረሳዋለን፡፡››
‹‹እሺ ……›› አልኩና እጄን ሰጠኋት፡፡ በስሱ ቆነጠጠችኝ፡፡ እጇን ሰጠችኝ፡፡ ከሷ ትንሽ ከፍ አድርጌ በስሱ ቆነጠጥኳት፡፡ መቆነጣጠጡ እየጋለ መጣ፡፡ እጆቻችን ፍም መሰሉ፡፡ አዝኜላት ከሷ ያነሰ ስቆነጥጣት ድጋሚ በሐይል እንድቆነጥጣት ታስገድደኛለች፡፡ በህመሙ ተውጠን ረሀቡን ለጊዜው ዘነጋነው፡፡ ሆኖም መቀጠል አልቻልንም፡፡ እጃችን ሊበልዝ ምንም አልቀረውም፡፡
ቤታችን እንደተዘጋች ናት፡፡ ብንከፍተውም የምንሄድበት ቦታም ሆነ የመንቀሳቀስ አቅም የለንም፡፡ ስለአባዬ ስናወራ …… ድሮ ስለነበርንበት ድሎት ኢንቱ ስትተርክልኝ ……… ከአመታት በፊት በደጉ ጊዜ እኛ ቤት ስለተደገሰ ድግስ ስንጫወት ……… በትዝታ ጭልፋ ከድሮው ቡፌ የሀሳብ ምግብ ጨልፈን ስንበላ …… ሰዓቱ ሄደ፡፡ ደከመን፡፡ ማውራት አቆምን፡፡ በጀርባችን ተጋድመን የሆዳችንን የረሀብ ዜማ ብቻ እናደምጣለን፡፡ የእማዬም ሆድ ሲጮህ ይሰማል፡፡ ኢንቱዬ እንባዋ ፈሰሰ፡፡ አምስት ሰዓት ሊሆን ሲል ስልክ ስለተደወለላት ተጣጠበችና ፏ አለች፡፡ ያያት ሰው አሁን ይህቺን የመሰለች ቆንጆ ርቧታል ብሎ ያስባል?
ድምቅ ስትልብኝ ‹‹የት ነው የምትሄጂው ግን?›› አልኳት፡፡
‹‹እነያስሚን ጋር ነገ ሰርግ ነገር አለ፡፡ ሄጄ ላግዛት እስኪ! እንዳይከፋት!››
‹‹ልታገባ ነው እንዴ?››
‹‹እሷ ሳትሆን ቤተሰብ ነገር ነው፡፡››
በሰበቡ ኢንቱዬ ምግብ ልትበላልኝ ትችላለች ብዬ ስላሰብኩ ደስ አለኝ፡፡ ኢንቱ ልትወጣ ስትል ‹‹ኢቦዬ …… ምናልባት ካስገደዱኝ ላድር እችላለሁ፡፡ አይደብርህማ?!›› አለችኝ፡፡
‹‹አታስቢ …… ሰርግ አይደል እንዴ አታስደብሪያቸው! እኔ ከቤት ስለማልወጣ ችግር የለውም፡፡›› ባታድር ደስ ይለኝ ነበር፡፡ ሰሞኑን ለሊቱ እንኳን ያለሷ ከእሷ ጋር እንኳን ዳገት ሆኖብኛል፡፡ ግን ልጫናት አልፈለግኩም፡፡ ለእኔ ብቻ ሳይሆን ለእሷም ማሰብ አለብኝ፡፡ ኢንቱዬ እኔንና እማዬን ስማ ወጣች፡፡ ኢንቱዬ ስትሄድ ቤቱ ውስጥ የነበረችው ጭላንጭል ብርሀን የጠፋች መሰለኝ፡፡
በጣም ርቦኝ ስለነበር ቀኑ አልገፋም ብሎኝ ለማንበብ ስሞክርና ስገላበጥ ስምንት ሰዓት አለፈ፡፡ ቤታችን እንደተጠረቀመ ነው፡፡ ስምንት ከሀያ አካባቢ ሲሆን በራችን ተንኳኳ፡፡ ፖሊሶች ከሆኑ በሚል ስልኩን መደበቄን አረጋገጥኩ፡፡ በሩ ስር የተቀመጠውን አዳፋ ብርድ ልብስ አንስቼ አይኔን እያሸሁ በሩን ከፈትኩ፡፡ አቤል ከፊት ለፊቴ ቆሟል፡፡ ‹‹አቤ
203 views12:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 22:16:28 ና አሰልቺ ሆነብኝ፡፡ ህይወቴም ያለ ኢንቲሳር፣ ያለ እማዬ፣ ያለ አብዱኬ፣ ያለ ጋሼ ምን ያህል አሰልቺና መራራ ሊሆን እንደሚችል አሰብኩ፡፡ የህይወቴን ጉዞ ያቀለሉልኝ እነሱ ናቸው፡፡ የሁሉም ነገር ውበት ሰው ነው፡፡ ሀዘንም … ደስታም …… ችጋርም …… ድሎትም ያለ ሰው ጎምዛዛ ነው፡፡ እንደዛ አሰብኩ፡፡ ያለአብዱኬ መንገዱ ራሱ ያስጠላል፡፡
የማልደርስ ቢመስለኝም ከአሰልቺው መንገድ በኋላ ቤቴ ደረስኩ፡፡ ቤት ስገባ ኢንቱ እራት አቀራርባ እየጠበቀችኝ ነበር፡፡ ገብቼ ልስማት ስጠጋ አይኗ መቅላቱን ልብ አልኩ፡፡ እማዬም አይኗ ቀልቷል፡፡
‹‹ኢንቱዬ ምን የተፈጠረ ነገር አለ?›› ግራ እየተጋባሁ ጠየቅኳት፡፡
ወደ ትሪው እየተጠጋች ‹‹እንብላና እነግርሀለሁ፡፡›› አለች!
‹‹አብዱኬስ?››
‹‹በልቷል!››
መብላት ጀመርን፡፡ በውስጤ ምን ተፈጥሮ ሊሆን እንደሚችል አውጠነጥናለሁ፡፡ የሚያረካ ግምት አልመጣልኝም፡፡ በልተን እንደጨረስን ኢንቱ ላይ አፈጠጥኩ፡፡
‹‹ኢንቱዬ ምንድነው የሆናችሁት?››
በቀኝ እጇ ግራ እጇን እየዳሰሰች ‹‹ኢቦዬ …… አብዱኬ ……››
‹‹አብዱኬ ምን ሆነ?!›› ከተቀመጥኩበት ተስፈንጥሬ ተነሳሁ፡፡ በልቷል ስትለኝ ጀምሮ እየሸከከኝ ነበር፡፡
‹‹ተረጋጋ ምንም አልሆነም! ተቀመጥና እነግርሀለሁ!››
ልቤ አመታቱን ሲለውጥ እየተሰማኝ ነው፡፡ ከጎኗ ተቀመጥኩ፡፡
‹‹አብዱኬ …… ታሰረ!››
‹‹ለምን?››
‹‹የተሰረቀ እቃ ተቀብለሀል ተብሎ!››
‹‹የት ነው ያለው?›› ተነሳሁ፡፡
‹‹ኢቦ አሁን እኮ ማታ ነው አያስገቡህም! እኛ እዛ ነበርን! ነገ አብረን እንሄዳለን …… ተረጋጋ!››
ጭንቅላቴን ይዤ ቁጢጥ አልኩ፡፡ በእኔ ሐጥያት እየተቀጣ እንደሆነ ተሰማኝ፡፡ ኢንቱዬ አቅፋኝ ፀጉሬን መዳበስ ጀመረች፡፡
‹‹ነገ ፍርድ ቤት ይቀርባል ብለዋል፡፡ በነፃ ሊለቀቅም እኮ ይችላል፡፡››
‹‹ኢንቱዬ ስልኩ እኮ እኔ ጋር ነው ያለው!›› አውጥቼ አሳየኋት!
‹‹እና የእውነት ተቀብሏል ማለት ነው?›› ደነገጠች፡፡
‹‹አዎ ኢንቱዬ ……››
‹‹ለማንኛውም ስልኩን ደብቀው! ፖሊሶች ቤቱን ሊፈትሹ ሲመጡ ከተገኘ ለእሱ መጥፎ ነው፡፡››
መኝታችንን አነጣጥፈን ተጋደምን፡፡ ኢንቱ ትንሽ ቆይታ ተኛች፡፡ እኔን ግን እንቅልፍ ተጣላኝ፡፡ አብዱኬ እስርቤት ውስጥ እንዴት ይሆን ይሆን? መተውት ይሆን? ከአዕምሮዬ የሀሳብ ድር ያለ እረፍት ይመዘዛል፡፡ ከስምንት ሰዓት በኋላ እንቅልፍ ይዞኝ ጠፋ፡፡ ንጋት አስራ ሁለት ተኩል ገደማ ኢንቱ ከእንቅልፌ ቀሰቀሰችኝ፡፡
‹‹ኢቦዬ …… ተነስ ይረፍድብናል፡፡ ለባብስ!››
በፍጥነት ተነስቼ ለባበስኩ፡፡ እማዬን ተሰናብተን ከጋሼና ከአባይዬ ጋር ወደ ኮልፌ ተጣደፍን፡፡ ፍርድ ቤቱ አንድ የጃጀ ቤት ውስጥ ነበር፡፡ ግቢ ውስጥ ቆመን መጠባበቅ ጀመርን፡፡ ሁለት ሰዓት ከሀያ አካባቢ አንድ ሎንቺን እጃቸው በካቴና የታሰሩ ሰዎችን ማውረድ ጀመረ፡፡ መሳሪያቸውን ያቀባበሉ ፖሊሶች ከግራና ከቀኝ በኩል በተጠንቀቅ ቆመዋል፡፡ አብዱኬ እጆቹ በካቴና እንደተጠፈነጉ ከመኪናው ወረደ፡፡ አባይዬ ስታየው አለቀሰች፡፡ እንባ እየተናነቀኝ ለሰላምታ እጄን አወዛወዝኩለት፡፡ አንገቱን እያዟዟረ እየፈለገን ነበር፡፡ ሲያየኝ ፈገግ አለ፡፡ የታሰሩ እጆቹን ከፍ አድርጎ ሰላም አለን፡፡ እስረኞቹ ከገቡ በኋላ ወደ ችሎት ክፍሉ ገባን፡፡ ዳኛዋ በተራ በተራ የሚገቡትን እስረኞች ክስና ምርመራ እያዳመጠች ቀጠሮ ትፈቅዳለች፡፡ አንዳንዶቹ ላይ ውሳኔ ትሰጣለች፡፡ የአብዱኬ ተራ ደርሶ ወደ ክፍሉ ገባ፡፡ መርማሪው ክሱን ማስረዳት ጀመረ፡፡
‹‹ … ዋጋው 15 ሺህ ብር የሚጠጋ የሞባይል ቀፎ የስርቆት ወንጀሉን ከፈፀመው ከተከሳሽ ሰለሞን በላይ እኔ አሻሽጥልሀለሁ በማለት ተቀብሏል፡፡ በዚህም የሌባ ተረካቢ በመሆን ……›› አብዱኬ እዚህ ቦታ የቆመው ለእኔ ብሎ ብቻ እንደሆነ ተሰማኝ፡፡ እኔ እህቴን ማገዝ እንድችል ገንዘብ ማግኛ መንገድ ሊፈጥርልኝ በመሞከሩ ብቻ! አብዱኬ ለዳኛዋ፣ ለፖሊሶቹና ለመርማሪዎቹ ተጠርጣሪ ብቻ ነው፡፡ ለእኛ ህይወት ግን ትልቅ ትርጉም ያለው ወንድማችን ነው፡፡ ለጋሼና ለአባይዬ ደግሞ የምሽት ጧሪያቸው …… ጥላ ከለላቸው ነው፡፡ በእሱ መታሰር ስንት ጎሮሮ በረሀብ እንደሚደርቅ ያሰበ የለም፡፡ ዛሬ ቁርስ አልበላንም፡፡ አብዱኬ ባይታሰር ግን እንደምንበላ እርግጠኛ ነኝ፡፡
አብዱኬ ፖሊሶቹ ለማወጣጣት በሚል እንደደበደቡትና እሱ ግን የተባለውን ስልክ እንዳላየ ለዳኛዋ አስረዳ፡፡ ድምፁ ላይ ጥቂት እንኳን የፍርሀት ድባብ አልነበረም፡፡ ዳኛዋ ዳግም እንዳይመቱት ፖሊሶቹን አስጠነቀቀች፡፡ መርማሪው የአስራ አራት ቀን ቀጠሮ እንዲሰጠው ጠየቀ፡፡ ዳኛዋ የስድስት ቀን ቀጠሮ ፈቀደች፡፡
ችሎቱ እንደተጠናቀቀ በእግራችን አብዱኬ ወደ ታሰረበት አጠና ተራ ወዳለው እስር ቤት ሄድን፡፡ የእስረኞቹ መኪና እስኪመጣ ዘገየ፡፡ ከመኪናቸው ወርደው ወደ ውስጥ ከገቡ በኋላ በሩ ለጠያቂዎች ተከፈተ፡፡ አስጠርተነው አባይዬ የቋጠረችለትን ምግብ ሰጠነው፡፡
ፈገግ ብሎ ‹‹ኢቦ ……›› አለ፡፡
‹‹ወዬ ……››
‹‹ሞባይል የሚባል አልተቀበልኩም እሺ? እሺ? በቅርቡ በነፃ እፈታለሁ፡፡›› በአይኑ አወራኝ፡፡
ለማለት የፈለገው እንደገባኝ እንዲያውቅ አንገቴን በአዎንታ እየወዘወዝኩ ‹‹እሺ ……›› አልኩ፡፡
ትንሽ አዋርተነው ብዙ ጠያቂ ስለመጣ ቦታ ለቀን ወጣን፡፡ ለታክሲ የምንከፍለው ብር ስላልነበረን ከአጠና ተራ እስከ አንፎ በእግራችን መመለስ ጀመርን፡፡ መንገድ አሳብረን …… እያወራን …… ከፀሐዩ ጋር እየታገልን …… መድረስ አይቀርምና ቤታችን ደረስን፡፡
ቤት ውስጥ ምንም የሚበላ ነገር አልነበረም፡፡ ፍራሹ ላይ ተቀምጬ ምን ማድረግ እንዳለብኝ አሰብኩ፡፡ ማህሌት ጋር ከመደወል የተሻለ ሀሳብ ሊመጣልኝ አልቻለም፡፡ በኢንቱዬ ስልክ ደወልኩላት! ይጠራል ግን አታነሳም፡፡ ምህረት ጋር ደወልኩ፡፡ እሷም አታነሳም፡፡ ግራ ገባኝ፡፡ ሰላም አይደሉም ይሆን ብዬ ሰጋሁ፡፡ አሁን ከመተኛት ውጪ የመጣልኝ ሀሳብ የለም፡፡ ድካምና ረሀብን በእንቅልፍ መሸወድ! ኢንቱዬም ከጎኔ ተኛች፡፡ እማዬም ተኝታለች፡፡ በሩ ተዘግቶ ቤቱ ጨልሟል፡፡ ከምድር የተገለልን መሰለኝ፡፡ የሁሉም መከራ የኛ ቤት ላይ የወደቀ ይመስላል፡፡ በልቤ ‹‹ለምን?›› ብዬ ጠየቅኩ፡፡ ‹‹ለምን የማያባራ የመከራ ጎርፍ ይወርድብናል? እኛ ከሌሎች የሰው ልጆች በምን እንለያለን? ፈጣሪን ፍጠረን ብለነዋል? ለምን ፈጥሮን ችግር ላይ …… መከራ ስር ይጥደናል?›› ከራሴ ጋር ተጨቃጨቅኩ፡፡
የረሀብ መጥፎ ነገሩ እንቅልፍ እንዳትተኛ መከልከሉ ነው፡፡ እንቅልፍ እንዲወስደኝ ብታገልም በቀላሉ ማሸለብ አልቻልኩም፡፡ ‹‹ደሀ ጥሩ እንቅልፍ ይተኛል፡፡›› ያሉን ሽንገላ ቅኔ ነው ማለት ነው? ሲሞት ነው? ቶሎ ይሞታል ለማለት ነው? ይኸው አሁን ለምን እንቅልፍ አይወስደኝም? ምኔ ሀብታም ይመስላል? ፈጣሪ ላይ ያሉኝ ብሶቶች ሁሉ እንደአዲስ ሲገነፍሉ ተሰማኝ፡፡ ግን ለምን? ስለፈጣሪስ ለማን አቤት ይባላል?
.
ይቀጥላል …
.
283 views19:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 22:16:00 ከተራራው ላይ
ክፍል አስር
(ፉአድ ሙና)
.
‹‹ከሰማይ በላይ ያለኸው ፣ ነፍሴን ለስቃይ ፈጥረኸው፣
ለአፍታ ሊያርፍ ቢደገፍ፣ ምነው ምርኩዙን ቀማኸው፣
በሱም ቀናህ?››
***
እራት ከተበላ በኋላ አብዱኬ ትንሽ ተጫውቶ ሄደ፡፡ ትንሿ ጎጇችን ውስጥ ሶስታችን ብቻ ቀረን፡፡ እማዬ ተኝታለች፡፡ ከኢንቱዬ ፊት ለፊት ተቀምጬ አይን አይኗን እያየሁ እስክትነግረኝ መጠባበቅ ጀመርኩ፡፡ ፊቷ ላይ መከፋት ይነበባል፡፡ መከፋቷን በውሸት ፈገግታ ልትሸፍነው እየሞከረች ‹‹ምንድነው የምትቁለጨለጨው?›› አለችኝ፡፡
አይኖቼን ፊቷ ላይ እንደተከልኩ ‹‹ንገሪኛ!›› አልኩ፡፡
እንባዋ አይኗን ሞልቶ ለመፍሰስ መታገል ጀመረ፡፡ ሳግ ባጠረው ድምፅ ‹‹እነግርሀለሁ ……›› አለች፡፡
ፍራሹ ላይ ከጎኗ ተቀምጬ አቀፍኳት፡፡ ማልቀስ ጀመረች፡፡ እያለቀሰች ‹‹ኢቦዬ አልቻልኩም …… ሁሉም ከቁጥጥሬ ውጪ ሆነ!›› አለችኝ፡፡ በእጄ ፀጉሯን እየዳበስኩ በዝምታ እስክትቀጥልልኝ መጠበቅ ጀመርኩ፡፡
‹‹ኢቦዬ …… እጄ ላይ ምንም ገንዘብ የለም፡፡ ነገ እንኳን ለምሳ የምቋጥርልህ ነገር የለኝም! ከስራ ተባርሬያለሁ፡፡ በቻልኩት አቅም ለመሸፈን ሞክሬያለሁ፡፡ ግን አሁን ከአቅሜ በላይ ሆነ፡፡ አታፍርብኝም አይደል?››
ጭምቅ አድርጌ አቀፍኳት፡፡
‹‹ግን አይዞህ እሺ …… ብንራብም ይኼን ሳምንት ብቻ ነው፡፡ ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ ገንዘብ አገኛለሁ፡፡ እሺ?››
እንባዋን እየጠረገች ‹‹እሺ ኢቦዬ?›› አለች፡፡
ግንባሯን ሳምኳት፡፡
‹‹ኢንቱዬ …… እንደዚህ በግልፅ ስትነግሪኝ እኮ ላንቺም ለእኔም ይቀላል፡፡ አትጨነቂ …… ደግሞ ለዚህ ሳምንት መፍትሔ አናጣም!››
ተንሰቀሰቀች፡፡ አቅፌ ላረጋጋት ሞከርኩ፡፡
‹‹ኢንቱዬ …… እኔን እኮ ከረሀቡ በላይ የሚያመኝ አንቺ ከፍቶሽ ሳይ ነው፡፡ እኛ ለረሀብ አዲስ ነን እንዴ? ረሀቡንም መከራውንም መቋቋም የቻልኩት ግን አንቺን በማየት ነው፡፡ አንቺን ማየት …… ደስ ብሎሽ ማየት ከሁሉም በላይ ያጠነክረኛል፡፡ ኢንቱዬ በጣም እወድሻለሁ፡፡ በጣም! አትዘኚ! አብረን እናልፈዋን እሺ?!››
እንባዋን እየጠረገች ‹‹እሺ!›› አለች፡፡
‹‹ፈገግ በያ!››
‹‹እሺ›› ፈገግ ለማለት ሞከረች!
ጎኗን እየነካሁ ስኮረኩራት መሳቅ ጀመረች፡፡ መኝታችንን አነጣጠፍኩና ተቃቅፈን ተኛን፡፡
ጠዋት ከእንቅልፌ ስነቃ በእኔና በኢንቱ መካከል ትራስ ገብቷል፡፡ ኢንቱ ተዘርራ ጥልቅ እንቅልፍ ውስጥ ሰጥማለች፡፡ በመካከላችን ያለው ትራስ የእማዬ ፍራሽ ላይ የነበረ ነው፡፡ ግራ ግብት አለኝ፡፡ ማታ ተቃቅፈን እንደተኛን ትዝ ይለኛል፡፡ ተነስቼ ለትናንትና አቅጄው የነበረውን ለመጨረስ ማንበብ ጀመርኩ፡፡ ትንሽ ቆይታ ኢንቱዬ ነቃች፡፡ እየሳቀች መሀከላችን በነበረው ትራስ መታችኝ፡፡
ሳቋ እየተጋባብኝ ‹‹ይኼ ከየት መጥቶ ነው?›› አልኳት፡፡
‹‹ፍቅረኛ ምናምን ጀምረሀላ!?›› በአይኖቿ ልታወጣጣኝ ሞከረች፡፡ ሳቅኩኝ!
‹‹ተናገራ የምሬን እኮ ነው፡፡››
‹‹ኧረ ወፍ የለም!››
‹‹እሺ ትናንት የተመቸችህ…… የሳምካት ወይም ብስማት ምናምን ያልካት ሴት የለችም?››
‹‹ባይሆን የሚያምር ከንፈር አይቻለሁ፡፡ ግን ማንንም አልሳምኩም፡፡››
‹‹ወረኛ አሳሳምህማ ልምድ ያለው ሰው አሳሳም ነበር!››
‹‹የምን አሳሳም ነው?›› ግራ አጋባችኝ፡፡
‹‹ማታ በእንቅልፍ ልብህ ስትስመኝ ነበር …… ለዛ ነው ትራሱን መሀል ላይ ያደረግኩት!››
‹‹ማን እኔ? ምንሽን?››
‹‹ከንፈሬን ነዋ! የሆነ ሰዓት ስባንን አይንህን ዘግተህ ……›› ሳቀች፡፡
‹‹ቆይ እንዴት ይሆናል? ማለቴ እንዴት ከንፈርሽን አገኘሁት?››
‹‹ብዙም ሩቅ አልነበረም …… ፊት ለፊትህ ነበር እኮ!›› ሳቀች፡፡ ‹‹ደግሞ አቅፈኸኝ ስለነበር በደመ-ነብስም አይጠፋህም!››
አፈርኩ! እሷ ትስቃለች፡፡ በትራስ እየመታች ሙድ ትይዝብኛለች፡፡
‹‹ባይሆን እውነቱን ተናገር! ስመህ አታውቅም ማንንም?››
‹‹ኢንቱዬ …… ማንንም አልኩሽ እኮ! ማንንም!››
ተነስቼ መለባበስ ጀመርኩ፡፡ ከቻልኩ ስልኩን ዛሬ እንደምንም ለመሸጥ አስቤያለሁ፡፡ ወደ ትምህርት ቤት ለመሄድ ስዘገጃጅ አብዱኬ መጣ፡፡ እጁ ላይ ሁለት ፓስቲ ይዟል፡፡
እንደሌላው ጊዜ ምድጃው ላይ የተጣደ ነገር ሲያጣ ‹‹ሻይ የለም እንዴ?›› አለ፡፡
ኢንቱዬ ፈገግ ብላ እያየችው ‹‹ዛሬ ሻይ ፎርፈናል!›› አለች፡፡
‹‹አትነግሪኝም እንዴ!›› አኮረፈ!
‹‹በቃ እኛ ውጪ ‘ሚቀማመስ እንፈላልጋለን! ለእናንተ ስሪ!›› ከኪሱ ሀምሳ ብር አውጥቶ ሰጣት፡፡
‹‹ኧረ አብዱኬ ……›› ኢንቱዬ በሀፍረት አንገቷን ሰበረች፡፡
‹‹ምን ልትዪ ነው ደግሞ …… ወንድምሽ አይደለሁ እንዴ!?››
‹‹እሱማ ነህ …… አበዛሁት ብዬ እኮ ነው፡፡ አላህ ይስጥልኝ …… መቼስ ምን እልሀለሁ ……››
ፓስቲውን ከሰጣት በኋላ ተሰናብተናቸው ወጣን፡፡ መንገድ ላይ እየሄድን አብዱኬን ከሌላው ጊዜ በተለየ ተመለከትኩት፡፡ መልዓክ መልዓክ መሰለኝ፡፡
በስስት እየተመለከትኩት ‹‹አብዱኬ ……›› አልኩት፡፡
‹‹ኧ››
‹‹ታውቃለህ ትምህርት ቤት ስማር ሁሉም በጣም Smart እንደሆንኩ ይነግሩኛል፡፡ ለእኔ ግን በጣም smart ማን እንደሆነ ታውቃለህ?››
‹‹ማነው?››
‹‹አንተ ነህ!››
‹‹ምን ቀላቅለህ ቅመህ ነው?››
‹‹ቀልዴን አይደለም አብዱኬ! እኔን Smart የሚሉኝ በሚታወቅ ቀመር ሂሳብ፣ ፊዚክስ ወይም ደግሞ በሽምደዳም ቢሆን ሌሎቹን ትምህርቶች በደንብ መረዳትና መስራት ስለምችል ነው፡፡ ይኼ የሚታወቅ ነገር ነው፡፡ ጥረት እንጂ ልዩ ጥበብ አይጠይቅም፡፡ ልዩ ጥበብ የሚጠይቀው ያልተፃፈን ነገር መረዳት ነው፡፡ የሰውን ልጅ መረዳት! የሰውን ጭንቀት ያለምንም ንግግር መረዳት! ከጭንቀቱ መፈወስ! ህይወትን መረዳት! ተቋቁሞ መኖር መቻል! ብዙ ሰው እኔን መሆን ይፈልጋል፤ እኔ ግን የምፈልገው አንተን መሆን ነው!››
‹‹የእኔን Smart ልንገርህ?››
‹‹ንገረኝ ……››
‹‹የእኔ Smart ኢንቲሳር ናት፡፡ ለራስ ሳይጨነቁ ለሌላ ሰው የመኖር ምሳሌዬ ናት፡፡ ድሮ ስራ ስጀምር ገንዘብ እንዴት መጠቀም እንዳለብኝ አላውቅም ነበር፡፡ ሁሉንም ያስተማረችኝ እሷ ናት፡፡ የከፋኝ ቀን የምሄደው ወደሷ ነው፡፡ ከባድ የመሰለኝን አቅልላ ታሳየኛለች፡፡ ያጣሁ ጊዜ ያላትን በአቅሚቲ ታካፍለኛለች፡፡ አንዳንዴ ምናለ ከእሷ ጋር ከአንድ መሀፀን በወጣን …… የስጋም እህቴ በሆነች ብዬ እመኛለሁ፡፡ ኢቦዬ እህትህ በጣም በጣም ልዩ ሰው ናት!››
‹‹እሷስ ልክ ነህ ልዩ ናት!››
ባጃጅ ተራ ደርሰን አንድ ሻይ ቤት ገባንና ፓስቲ በሻይ በላን፡፡ አለምባንክ ደርሰን ከአብዱኬ ጋር ልንለያይ ስንል እጄን ይዞ ‹‹ይኸውልሽ ኢቦ …… ችግር ሁሌም ያጋጥመናል፡፡ ግን ደግሞ ያልፋል፡፡ ገባሻ! ዛሬ ቢቸግረን ነገ እናገኛለን፡፡ አትጨነቅ!›› አለኝ፡፡ አሁን አሁን አብዱኬን በአንድ አመት እንደምበልጠው መርሳት ጀምሬያለሁ፡፡ ታላቅ ወንድሜ …… ታላቅ ወንድሜ ይመስለኛል፡፡
ከአብዱኬ ጋር ተለያይተን ወደ ትምህርት ቤት ገባሁ፡፡ ቀኑን ሙሉ በቻልኩት መጠን ስልኩን ለመሸጥ ለብዙ ተማሪዎች ሳሳይ ዋልኩ፡፡ በርካሽ ስምንት ሺህ ድረስ ልሸጥላቸው ብዙዎችን አጠያየቅኩ፡፡ የሚደፍር አልተገኘም፡፡ ባዶ እጄን ወደ ቤት መግባት ቀፈፈኝ፡፡ ማህሌትን ላስቸግራት አሰብኩና ወደ ማታ ደወልኩላት፡፡ ስልኳ ዝግ ነበር፡፡ ማታ ቤተል ቤተ-መፅሀፍት ከአቤላ ጋር ተቀምጬ አብዱኬ ስለዘገየብኝ ለመደወል ሞከርኩ፡፡ ስልኬ ካርድ አልነበረውም፡፡ በአቤላ ስልክ ደወልን፡፡ ስልኩ ዝግ ነው፡፡ ግራ ገባኝ፡፡ ትንሽ ጠብቄው ሲቆይ ወደ ቤት ሄድኩ፡፡ ለብቻዬ ስለሆንኩ ነው መሰል መንገዱ በጣም ረዥም
301 views19:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ