Get Mystery Box with random crypto!

ሀላል ትዳር👫💍

የቴሌግራም ቻናል አርማ hayu_abdi — ሀላል ትዳር👫💍
የቴሌግራም ቻናል አርማ hayu_abdi — ሀላል ትዳር👫💍
የሰርጥ አድራሻ: @hayu_abdi
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 8.54K

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-09-21 13:58:06
1.1K views10:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-14 21:06:16
2.5K views18:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-12 08:15:57
2.8K views05:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-09 22:45:34
3.3K views19:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-05 08:34:53 በስፒከር ነው መሰለኛ የምታወራው?››
‹‹አዎ››
‹‹ሀፍሳ ካንተ ጋር ናት?››
‹‹አጠገቤ ተቀምጣለች፡፡››
‹‹ሀፊዬ ኧረ በእሁዱ ብቻዬን አታስውዪኝ ባሌን መልሺ!››
ሁላችንም ሳቅን፡፡ እየመጣን እንደሆነ ነግሬያት ተሰነባበትን፡፡
ስልኩ እንደተዘጋ ሀፍሳ ፈገግ ለማለት እየሞከረች ‹‹Trust level መቶ ከመቶ›› አለች፡፡
ቤተል ቢሯቸው ጋር ላወርዳቸው ስል ሀፍሷ ትክዝ እያለች ‹‹please ኢብሮ ከቻልክ ታሪክህን ፃፈው!›› አለችኝ፡፡ በጣም ከፍቷታል፡፡ ፈገግ ብዬ መልስ ሳልሰጥ ተሰናበትኳት፡፡ መኪናዬን በቤተል አደባባይ በኩል አዙሬ አርባ ሜትሩን እየዠለጥኩ ወደ ልቤ ንግስት …. ወደ ደግነት ሀውልት ….. ወደ ውዷ ሚስቴ ከነፍኩ፡፡
.
ተፈፀመ!!!
.
141 views05:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-05 08:34:02 ትን ካሳለፍን በኋላ ተሰናበትናቸው፡፡ ወደ መኪናችን እየተመለስን ‹‹ቁርዓን የት ነው የሚማሩት?›› አልኳት፡፡
‹‹አሁን እዚህ ትንሽዬ ቁርኣን ቤት አለች፡፡ የወር ክፍያ እኛ እንከፍልላቸዋለን፡፡››
‹‹ድሮ እኮ ምንም አልነበረም! የእውነት ሁሉም ነገር ደስ ይላል፡፡ ዛሬ ያደረግነው ነገር የልጆቹ ህይወት ውስጥ ምን ያህል ቦታ እንዳለው እንደነሱ ተቸግሬ ስለማውቅ እረዳዋለሁ፡፡ በርቱበት ከጎናችሁ ነኝ!››
‹‹አንድ የደፋር ጥያቄ ልጠይቅህ?›› ተሸኮረመመች፡፡
‹‹እስካሁን አንድም የፈሪ ጥያቄ አልጠየቅሽኝም እኮ!››
‹‹ማህሌትን የምትወዳት ስለውለታዋ ነው ወይስ?››
ገርማኝ ፈገግ አልኩ፡፡
‹‹ታውቂያለሽ ….. ቆንጆ ናት፡፡ ግን ደግሞ ከሷ የበለጡ ቆነጃጅት ይኖራሉ፡፡ ገንዘብ አላት ….. ከሷ የበለጡ ሀብታም የሀብታም ልጆች ይኖራሉ፡፡ በህይወት ዘመኔ ግን የሷን አይነት ስነ-ምግባር ማንም ላይ አልተመለከትኩም፡፡ ፍቅር ምንድነው? ከነብሷ በላይ ምኗን ላፈቅር እችላለሁ? ምንም! እሷ እኮ የህይወቴ ተዓምር ናት፡፡ እሷ በእኔ ህይወት ውስጥ ስትመጣ የስንት ሰው ህይወት ውስጥ ነብስ እንደዘራች ታውቂያለሽ? እህቴን ከነበረችበት የሰቆቃ ህይወት ወደተከበረች እመቤትነት የቀየራት …… አብዱኬን ከወያላነት ወደ አባወራነት ያሻገረው ….. አቤላን ያለሀሳብ በሄደበት በምቾት የሚያስተምረው ….. እኔን የሚሊየን ብር መኪና የሚያስነዳኝ …… ምን ይመስልሻል? የእሷ በህይወቴ ውስጥ መምጣት ነው፡፡ ሀብታም ሆና እልም ያልኩ መናጢ የሙት ልጅ መሆኔ እኔን ከመወዳጀት አላገዳትም፡፡ ብዙ ሀብታሞች ነበሩ በእምነትም የሚመስሉኝ! ዞር ብሎ ያየኝ ግን አልነበረም፡፡ እሷ ግን እኔን ለመደገፍ የሐይማኖታችን መለያየት አላገዳትም፡፡ ብቻ ምን ልበልሽ?  ስለራሴ ያለኝ አመለካከት እንኳን የተሻለ እንዲሆን ያደረገችው እሷ ናት፡፡ ሀፍሷ  …. ሚቾ እኮ ተዓምር ናት፡፡ ከፈጣሪ እንኳን ተስፋ ስቆርጥ …… ጨለማው አይነጋም ብዬ ሳስብ የፈነጠቀችልኝ ብርሀኔ ናት፡፡ የማፈቅረው ከሷ የሚወጣውን እያንዳንዱን ትንፋሽ ሳይቀር ነው፡፡ ነገርኩሽ እኮ ገሀነም እንደምትገባ ባውቅ ከሷ ጋር ገሀነም ለመግባት ዝግጁ ነኝ፡፡ ማፍቀር ማለት በአይኗ ማማር ….. በዳሌዋ ስፋት መማረክ ከመሰለሽ ተሳስተሻል፡፡ ማፍቀር ነብስን ነው፡፡ ሁሉ ነገሯን አፍቅሬዋለሁ፡፡ የሷ ስለሆነ ብቻ ሳላውቀው እንኳን ያለአንዳች ማንገራገር ሐይማኖቷን ተቀብያለሁ፡፡››
‹‹ግን ይኼን ሁሉ ነገር ያደረገችው ሐይማኖትህን ለማስቀየር ቢሆንስ?››
ብሶቴን ቀሰቀሰችው፡፡
‹‹ፍቅረኝነትን እስክንጀምር አንድም ቀን ስለሀይማኖቴ አንስታብኝ አታውቅም፡፡ ተርቤ ስታበላኝ ሀይማኖቴን አልጠየቀችኝም፡፡ የሚያስጠላኝን የሙስሊሞችና የኦርቶዶክሶች ወሬ ልንገርሽ? በዘይት ተታለሉ ምናምን የምትሉት ጉድ ነው፡፡ ስንራብ አብሉን ስንል የላችሁም፡፡ ሰው አብልቶን በጨለማችን ጊዜ ሲደርስልንና በእምነቱ ተማርከንም ይሁን በስነ-ምግባሩ ተስበን ሐይማኖታችንን ስንቀይር በዘይት ተታለሉ ትላላችሁ፡፡ የት ነበራችሁ ስንራብ? የት ነበራችሁ ጨጓራችን ሲነድ? የት ነበራችሁ ስንታሰር? የት ነበራችሁ ስንታመም? የናንተ ጭቅጭቅ ሱሪ ማስረዘም ይቻላል አይቻልም ነው አይደል? ለናንተ እምነት ማለት ዘፈን ሰማች፣ ቀሚሷ ተጣበቀ …. ከወንድ ጋር እንዲህ ሆነች እያሉ ሐጥያት መፈላፈል ነው አይደል? ከፈረ ….. መናፍቅ ምናምን ለማለት የሚቀድማችሁ የለም፡፡ በጣም ደግ ከተባላችሁ ደግሞ ቤተ-እምነታችሁ በር ላይ ለተኮለኮሉ ነዳያን እየተመፃደቃችሁ አንድ አንድ ብር ታድላላችሁ፡፡ ምን ይጠቅማቸዋል? ደግሞ ግዴታ መንገድ ላይ ወድቀን መለመን አለብን ማለት ነው? በኛ ቦታ ቆማችሁ የኛን ህመም አይታችኋል?  አላያችሁም፡፡ በወሬ ሳይሆን በተግባር ያሳየንን እንከተላለን፡፡ ይኼ ደግሞ መብታችን ነው፡፡››
ማልቀስ ጀመረች፡፡ ንዴቴ አልበረደም ቀጠልኩ፡፡
‹‹ሌላው ደግሞ እስኪ አንድ ቀን እንኳን ከቤተ እምነታችሁ ውጪ ላለው ሰው ስለሀይማኖታችሁ ጥሪ አድርጋችኋል? አታደርጉም! የሐይማኖቱም ተከታይ ሐይማኖቱን ለማወቅ ገንዘብ ከሌለው አይችልም፡፡ አሊያም ደግሞ በየሰዓቱ ቤተ-እምነታችሁ እየተመላለሰ ካሪኩለም የሌለው የለብለብ ትምህርት ማዳመጥ ግድ ይለዋል፡፡ ገና የራሳችሁን ኮተት ሳትሞሉ ጴንጤው ወይም ሌላው መንገድ ላይ ወጥቶ የገነት መንገድ ተገልጦልኛል ኑ አብረን እንግባ እያለ የገባውን ሲያስረዳ ትቀጠቅጡታላችሁ፡፡ እናንተ ያላሳያችሁትን መንገድ በጠቆመ? እናንተ ያልሞላችሁትን ክፍተት በሞላ? ምን አይነት ሀይማኖተኝነት ነው ይኼ?  እውነቱን ልንገርሽ አብዛኛው የሀገራችን ህዝብ የአባቴ እምነት እያለ ሐይማኖቱን የያዘ ነው፡፡ ስለሐይማኖቱ ገና ምንም የሚያውቀው ነገር የለም፡፡ እናንተ እስክትነቁ ፕሮቴስታንቱም፣ ሐዋርያቱም፣ ጆቫውም ሁሉም ና አብረን ገነት እንግባ እያለ ይጠራዋል፡፡ ሲርበው ያበላዋል፡፡ ሲቸገር ይደርስለታል፡፡ አባቶቼ ልክ አልነበሩም እያለ ሐይማኖቱን ይቀይራል፡፡ እኔ በግልፅ ነግሬሻለሁ፡፡ ፈጣሪ ጉዳዬ አይደለም፡፡ ማህሌት ነገ ሌላ ሐይማኖት እንከተል ካለችኝ ደስ ያላትን እቀበላለሁ፡፡ ለምን መሰለሽ፡፡ እኔ እሷን ተቀብያለሁ! የኔ ሐይማኖት የሷ ደግነት ነው፡፡››
መራመድ አቅቷት መንገዱ ላይ ተቀምጣ መንሰቅሰቅ ጀመረች፡፡ ፊቷ ቲማቲም መስሏል፡፡ እሷ ላይ እንደዚህ መጮህ እንዳልነበረብኝ ተሰማኝ፡፡ ስትረጋጋ ይቅርታ ጠየቅኳት፡፡
‹‹ይቅርታ ሀፊ …… እናተን እንደዚህ ማለት አልነበረብኝም …. የቻላችሁትን እየሰራችሁ ነው፡፡››
እንባዋን እያበሰች ከተቀመጠችበት ተነሳችና ‹‹ምንም አላጠፋህም፡፡ ያልከው ሁሉ ልክ ነው፡፡ እኛም የቻልነውን እናግዝ ብለን እየተንቀሳቀስን ነው፡፡ እኛን እንኳን ተረድቶ ከጎናችን የሚቆመው ሰው በጣም ትንሽ ነው፡፡ በጣም ይቀረናል፡፡ በጣም!››
ወደ መኪናችን ተመልሰን እንደተቀመጥን ድጋሚ መንሰቅሰቅ ጀመረች፡፡
‹‹ሀፊ ….. Please በቃ ተረጋጊ!››
‹‹ታውቃለህ ነገ ጌታዬ ተርቤ አላበላችሁኝም ….. ስጠማ አላጠጣችሁኝም ….. ስታረዝ አላለበሳችሁኝም የሚልበት ቀን አለ ….››
‹‹ፈጣሪ ደሞ ይበላል? ይጠጣል? ይለብሳል?››
‹‹ያኔ እኛ አሁን አንተ ያልከውን ጥያቄ እንጠይቀዋለን፡፡ መልሱ ምን መሰለህ? ….›› መንሰቅሰቋ በረታ፡፡
‹‹ምንድነው መልሱ?››
‹‹ባርያዎቼ ሲታረዙ አላለበሳችኋቸውም፡፡ እነሱን ብታለብሱ እኔን ታገኙ ነበር፡፡ ሲራቡ አላበላችኋቸውም፡፡ እነሱን ብታበሉ እኔን ታገኙ ነበር፡፡ ሲጠሙ አላጠጣችኋቸውም ብታጠጧቸው በነሱ ውስጥ እኔን ታገኙ ነበር ይላል፡፡ ላንተ ሐይማኖት መቀየር ተጠያቂው ስትቸገር ያልደረስንልህ እኛ ነን፡፡ ያኔ ጌታዬ በተራቡት ሰዎች ጉዳይ ሲጠይቀኝ ምን ብዬ እመልሳለሁ?›› ተንሰቀሰቀች፡፡
‹‹ራስህ ቀጥታ ለምን አልሰጠሀቸውም ትይዋለሽ አትጨነቂ!››
ሁሉም አባላት መጡ፡፡ ፕሬዝዳንቱ የኔ መኪና ውስጥ ከኋላ ተቀመጠ፡፡
ትህትናውን እንደተላበሰ ‹‹ወደድከው?›› አለኝ፡፡
‹‹እሷ አለቃቀሰች እንጂ በጣም ወድጄዋለሁ፡፡ ከዚህ በኋላ ቤተሰብ ነኝ እንደውም!››
‹‹ደስ ይለናል! …. እና ድሮ የምታውቀውን ሰው አላገኘህም?››
‹‹አይቻለሁ ማንንም ማናገር አልፈለግኩም፡፡ ትዝታዬን መቀስቀስ ይሆንብኛል ብዬ ፈራሁ፡፡ ባይሆን ወደፊት ከደፈርኩ እስኪ ….››
መኪናችንን አስነስተን መመለስ ጀመርን፡፡ እየተመለስን ሚቾዬ ደወለች፡፡ በመኪናው ስፒከር ማዋራት ጀመርኩ፡፡
‹‹አብርሽዬ ማር …..››
‹‹ሚቾዬ ቆንጆ …..››
‹‹ውሎ እንዴት ነው?››
‹‹ምርጥ ነበር በጣም! ያልደፈርኩትን ደፈርኩ፡፡››
‹‹ስማ ደግሞ
140 views05:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-05 08:33:42 ከተራራው ላይ
ክፍል አስራአምስት
የመጨረሻው ክፍል
(ፉአድ ሙና)
.
‹‹ባጎረስሽኝ ጉርሻ፣ ረሀብ ከሰመ፣
በደጉ ስብዕናሽ፣ ችጋር ተፈፀመ፡፡
አንቺን አምኛለሁ!››
***
ሚቾዬ እሁድ በጠዋት ቀሰቀሰችኝ፡፡ እኔ በእንቅልፍ አሳብቤ ለመቅረት ሳስብ ነበር፡፡ አልሆነልኝም፡፡ ቱታ ሱሪ በባለኮፍያ ቱታ ጃኬት ለበስኩ፡፡ የሰፈሬ ሰዎች እንዲለዩኝ አልፈለግኩም፡፡ ትንሱዬን ይዘን መሄድ ስለማንችል ሚቾ አትሄድም፡፡ መኪናዬን አስነስቼ ቤተል አደባባይ ስደርስ ሀፍሷ ጋር ደወልኩኝ፡፡ ‹‹ኡሚ›› የሚል ፅሁፍ ያለበት አረንጓዴ ፒፕስ አባያዋ ላይ እንደደረበች እየተፍለቀለቀች መጣች፡፡ 
ፈገግ እንዳልኩ ‹‹መኪና አልያዝሽም እንዴ?›› አልኳት፡፡
‹‹ይዣለሁ ሰጥቻቸው ነው፡፡ እየተጫወትን እንድንሄድ ነው …… ያው የኔ እንግዳ ነህ ብዬ ነው፡፡››
መኪናዬ ውስጥ ከጎኔ ተቀምጣ መንገድ ጀመርን፡፡
ወደኔ ተመቻችታ እየተቀመጠች ‹‹ሚስትህ አልደበራትም አይደል?›› አለችኝ፡፡
‹‹ለምን ይደብራታል?››
‹‹ወደ እስልምና እንድትመለስ ልንሰብክህ መስሏት ምናምን?››
‹‹እና አይደለም እንዴ?›› ሳቅኩኝ፡፡
‹‹አዝግ ነገር ነህ!›› ሳቄ ተጋባባት፡፡
‹‹የምር ግን ሚቾ ልቧ በጣም ንፁህ ነው፡፡ እንደምወዳት ታውቃለች፡፡ ሲቀጥል ደግሞ ፈጣሪ ጉዳዬ እንዳልሆነም በደንብ ትረዳለች፡፡ ስለዚህ አትሰጋም፡፡››
‹‹ትዳር የማንበጠብጥ ከሆነ መልካም ነው፡፡ የመረዳት ፕሮጀክታችን አካል ነህ! ሐይማኖትህን መቀየርህ ምንም አይነት ኢስላማዊ እውቀት ያልነበረውና ከትክክለኛ ሙስሊሞች ጋር ያልተገጣጠመ ሰው እንደመሆንህ የሚጠበቅ ይመስለኛል፡፡ ሐይማኖትህን በተመለከተ ልንጫንህ አንፈልግም …… አንተ ትልቅ ነህ፡፡ ወደፊት ላንተም ለሚቾም የሚሻለውን ተመራምረህ ትደርስበታለህ ብዬ አስባለሁ፡፡››
‹‹እሺ መልካም እና የመረዳት ፕሮጀክት ማለት ምን ማለት ነው?››
‹‹አንተ በልጅነትህ ስለእስልምና በስርዓቱ ብታውቅ ባሳለፍካቸው የመከራ ጊዜያት ሁሉ ትልቅ ስንቅ ይሆንህ ነበር ብዬ አስባለሁ፡፡ ግን ትምህርቱን አላገኘህም …. እንደነገርከኝ ከባድ ነበር፡፡ ስለዚህ አንተ በጣም ትፈልጋቸው የነበሩ ግን ያጣሀቸውን ነገሮች መረዳት የምናግዛቸውን ቤተሰቦች ለመርዳት በጣም ይጠቅመናል፡፡››
‹‹እናንተ እንኳን ተረድታችሁታል ….››
ትንሽ ዝም ካለች በኋላ ትንሽዬ ማስታወሻ ደብተሯን ገልጣ እያየች ‹‹ኢብሮዬ ባለፈው ከተለያየን በኋላ ብዙ ጥያቄዎች ተፈጥረውብኝ ነበር ….. ልጠይቅህ?››› አለች፡፡
‹‹ይቻላል ….››
‹‹ጓደኛህና እህትህ እንዴት ተጋቡ?››
‹‹በጣም ቅርርብ ነበረን፡፡ ወንድሜ ብዬ ነው የማስበው! ኢንቱ የአዕምሮ ህመም የገጠማት ጊዜ የምትቀርበን እኔን፣ እሱንና ሚቾን ብቻ ነበር፡፡ እሱ ደግሞ ከድሮም በጣም ይወዳታል፡፡ በጣም ያስብላታል …. ይረዳታልም፡፡ እሷም ይኼን ነገሩን በጣም ትወድለታለች፡፡ እኔና ሚቾ ከተጋባንና እሱ የሚቾ አባት ወሳኝ ጉዳይ አስፈፃሚ ከሆነ በኋላ ከአንፎ ለቅቆ ቤተል ቤት ተከራየ፡፡ እናቱ ወዲያው ስለሞተች ከአባቱ ጋር ቤቱ በጣም ሰፋው፡፡ እና የዚያን ጊዜ የልቡ እውነተኛ ፍላጎት ምን እንደሆነ ማሰብ ጀመረ፡፡ በመጨረሻም ኢንቱዬ ገና እያገገመች እያለ ሀሳቡን አካፈለኝ፡፡ መጀመሪያ በጣም ደነገጥኩ፡፡ አንደኛ በእድሜ እኔ እንኳን እሱን በአንድ አመት እበልጠዋለሁ፡፡ኢንቱዬ ደግሞ በጣም ታላቁ ነበረች፡፡ በሰባት አመት ምናምን መሰለኝ የምትበልጠው!  እና እንዴት ይሆናል አልኩት፡፡ አንተ ለወደድካት ልጅ ሐይማኖትህን ቀይረህ እኔ ላይ እንዴት እድሜ እንቅፋት ይሆናል ሲል ሞገተኝ፡፡ ውሳኔውን ለሷ እንድንተወው ግን በደንብ እስከሚሻላት ሀሳቡን ላናቀርብላት ተስማማን፡፡ በደንብ ሲሻላት ነገርናት፡፡ ኢቦዬ ከፈቀደ አልቃወምም አለች፡፡ ያው እሺ ማለቷ ነው እንግዲህ በግሪክኛ! ድሮም እንደሚዋደዱ ስለማውቅ ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ እህቴን አስረከብኩት፡፡ አሁን ድረስ እንደሁለቱ መጋባት የሚያስደስተኝ ነገር የለም፡፡ አብዱኬ ተዛመደኝ፡፡ ደግሞ ቶሎ ቶሎ ወለዱ፡፡ ሁለት ልጅ አላቸው፡፡ በጣም የምወዳቸው ሁለት ሰዎች ተጣምረው እንደማየት ለእኔ ደስ የሚል ነገር የለም፡፡››
‹‹ይቅርታ ይረብሽህ ከሆነ አላውቅም ግን አሰሪዋን ምንም አላልከውም?›› መረበሽ አለመረበሼን ከፊቴ ላይ ለማንበብ ሞከረች፡፡ ፈገግ አልኩኝ፡፡
‹‹ታውቂያለሽ ዲያሪውን እንዳነበብኩ ሀሳቤ ሙሉ ንብረቱን ለማውደም ነበር፡፡ ውስጤ በጥላቻ ተሞልቶ ነበር፡፡ ከአብዱኬ ጋር ሆነን ስለሰውየው አጣራን፡፡ ባለትዳር ነው፡፡ ልጆችም ነበሩት፡፡ በመሀል ግን ማህሌት አወቀችብን፡፡ መጀመሪያ ተባባሪ መስላ ሁሉንም እንቅስቃሴያችንን አወቀች፡፡ ከዚያ ግን በአጭር ንግግር ረታችን፡፡ ‹‹የሱን ንብረት አውድማችሁ ወይም እሱን ጎድታችሁ ልጆቹ እናንተ የማቀቃችሁበትን አይነት ህይወት እንዲኖሩ ትፈልጋላችሁ ወይ?›› አለችን፡፡  ስናስበው ልክ ነበረች፡፡ እሱ ለኛ መጥፎ ቢሆንም ለልጆቹ ግን አባት ነው፡፡ እናም በጣም እየከበደኝ ይቅርታ አደረግኩለት፡፡ ያኔ ሁሉም ነገር ቀለለኝ፡፡››
‹‹እህትህ ዲያሪ ለምንድን ነበር የምትፅፈው?››
‹‹ያኔ ህመሟን የምታዋየው ሰው ስላልነበረ ይመስለኛል፡፡ ሲቀጥል ደግሞ ያሳለፍነውን ታሪክ ሁሉ ለእኔ ልታሳውቅ ስለምትፈልግም ነው፡፡ እሷ አሁንም ዲያሪዋን እንዳነበብኩ አታውቅም፡፡ ሁሌም ከተመረቅኩ በኋላ እንደምትሰጠኝ ትነግረኛለች፡፡››
አንፎ ባጃጅ ተራው ጋር ስንደርስ መኪናዬን አቆምኩ፡፡
‹‹ምነው?›› አለችኝ፡፡
‹‹ከዚህ በኋላ መንገዱ መኪና ይጎዳል!››
ሳቀች! ከሳቋ ሳታባራ ‹‹አንተ እውነትም ከመጣህ በጣም ቆይተሀል! ተራራው ድረስ እኮ መንገድ ተሰርቷል፡፡›› አለች፡፡
መኪናዬን አስነስቼ በፒስታው መንገድ ላይ በዝግታ እያዘገምኩ ወደ ተራራው መሄድ ጀመርን፡፡ ተራራው ጋር ስንደርስ የልብ ምቴ ፍጥነት ጨመረ፡፡ ከዚህ ተራራ ስር የእናቴን እና የአባቴን ሬሳ በተለያየ ጊዜ አንዲት አሮጌ ፒካፕ መኪና ላይ ጭነናል፡፡ ድርጊቱ ሁሉ አሁን እየሆነ ያለ ያህል ፊቴ ላይ ድቅን አለብኝ፡፡  ማልቀስ ጀመርኩ፡፡ መሪው ላይ ተደፍቼ ተንሰቀሰቅኩ፡፡
‹‹አይዞን ኢብሮ ….. አይዞን!›› ሀፍሷ ልታፅናናኝ ትሞክራለች፡፡ አንብቼ ሲወጣልኝ ይቅርታ ጠየቅኳት፡፡ ሌሎች መኪናዎች ከኋላችን መጥተው ሲቆሙ ከመኪናችን ወረድን፡፡ ፕሬዝዳንቱ ከሀፍሷ መኪና ወርዶ ሀፍሷ የለበሰችው አይነት ፒፕስ ሰጠኝ፡፡ ከኋላ ከነበረችው አሮጌ ታክሲ ላይ ለወር አስቤዛ የተሸመተውን ተሸክመን ወደምንጠይቀው ቤተሰብ ሄድን፡፡ ተራራውን ትንሽ እንደወጣን ህፃናት እየተሯሯጡ እየመጡ ያቅፉን ጀመር፡፡ የምናልፍበት ቤት ሰው ሁሉ ሰላምታ ይሰጠናል፡፡ አንዲት ደከም ያለች ጎጆ ጋ ስንደርስ ህፃናቱ ‹‹ኡሚዎች መጡ …… ኡሚዎች መጡ ….›› እያሉ ወደኛ መሮጥ ጀመሩ፡፡ ሀፍሷና አብረውን የነበሩ ወጣቶች ህፃናቶቹን አቅፈዋቸው ወደ ቤት ገባን፡፡ አንዲት ህመም ከአልጋ ላይ የጣላት እናት በፈገግታ ተቀበለችን፡፡ ቤቱ ውስጥ አረፍ እንዳልን አባላቱ ስለጤናዋ መጠያየቅ ጀመሩ፡፡
‹‹አቡኪዬ ና እስኪ የቀራኸውን አሰማኝ!›› ሀፍሷ ከመካከላቸው አንዱን ህፃን በእጇ እየጎተተች አቀፈችው፡፡
ቀይዋን ትንሽዬ ቁርዓን ከፍቶ በሚገርም ፍጥነት ማንበብ ጀመረ፡፡ ሌሎቹም በተራ በተራ አሰሟቸው፡፡ በግርምት እንደተዋጥኩ ፈገግ ብዬ ተመለከትኳቸው፡፡ ሀፍሷ የቆሸሹ ልብሶቻቸውን ሰብስባ አወጥታ ማጠብ ጀመረች፡፡ ሌሎቹ ምግብ ለማብሰል ከሰል ማያያዝ ጀመሩ፡፡ ምግብ መስራቱ ላይ ተሳተፍኩ፡፡ የህፃናቱን ገላ አጥበንና ቤቱን አፀዳድተን ግማሽ ቀን ያህል እየሰራንና ከልጆቹ ጋር እየተጫወ
145 views05:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 15:02:21
‹‹ግቢ ውስጥ ነኝ እኮ!››
‹‹ና ልብስ ቀይራ መኝታ ቤት ነን!›› 
ወደ መኝታ ቤት ስገባ ሚቾና ኢንቱዬ  ልጃችንን እያለበሱ ነበር፡፡ ሶስቱንም ስሜ ልብሴን ቀያየርኩ፡፡
ተዘገጃጅተን እንደጨረስን ሚቾ ‹‹እስኪ dad አንተን ካላየ ከዛ ክፍል አይወጣም …… please ሂድና እንደጨረስን ንገረው!›› አለችኝ፡፡ ወደ ቢሮው ሄጄ በሩን ከፈትኩትና ‹‹ክቡር አቶ በየነ ትወጣለህ ወይስ በግድ ጎትተን እናስወጣህ?›› አልኩት፡፡ እየሳቀ ከወንበሩ ላይ ተነስቶ ተከተለኝ፡፡ ማህሌት ነጭ ሙሉ ቀሚስ …… ኢንቱዬ ደግሞ ነጭ ሂጃብና ሙሉ አረንጓዴ ቀሚስ ለብሰዋል፡፡
ወደ በረንዳው ስንወጣ ሁሉም በጭብጨባ ተቀበሉን፡፡ የበየነ ጓደኞችም ከቤተሰባቸው ጋር ተገኝተዋል፡፡ ሰዉ በልቶ እንደጨረሰ የኬክ መቁረሻው ሰዓት ሲደርስ እኔና ሚቾ ልጃችን ትንሳኤን አቅፈን ወደ ኬክ መቁረሻው ቦታ ቀረብን፡፡ ኬኩ ላይ አንድ ቁጥር ሻማ ተሰክታለች፡፡ አብዱኬ አቤላን በቪዲዮ አስገብቶ ዝግጅቱን በቀጥታ እያሳየው ነው፡፡
ኬኩ እንደተቆረሰ አቶ በየነ ፀሎት አድርገው ንግግራቸውን ከፈቱ፡፡
‹‹የዛሬ አመት ጌታ ይህችን የመሰለች ቆንጅዬ ልጅ አሳቅፎናል፡፡ ክብርና ምስጋና ለእርሱ ይሁን!››
‹‹አሜን!›› የታዳሚው ድምፅ አስተጋባ፡፡
‹‹እናም ዛሬ ጌታ እኛን የባረከበት ቀን ነውና ይህን አስመልክቼ ለሁለቱ ውድ ልጆቼ የማበረክተው አንድ ስጦታ ይኖራል፡፡›› አብዱኬ ልጁን እንዳቀፈ በእጁ በስጦታ ወረቀት የተጠቀለለ ትልቅ ፍሬም አቀበላቸው፡፡ ሁሉም በአንድነት እያጨበጨበ ስጦታውን ተቀበልን፡፡
‹‹ይከፈት …… ይከፈት!›› የሚል ድምፅ ተስተጋባ፡፡
ሚቾና እኔ በአንድነት ሆነን ስጦታውን ከፈትነው፡፡ ያየነውን ማመን አልቻልንም፡፡ ‹‹ትንሳኤ ሆስፒታል›› የሚል ፅሁፍ በትልቁ ሰፍሮበታል፡፡ በዮካን አቅፈነው በደስታ አነባን፡፡
በዮካ እንዳቀፈን ‹‹እንግዲህ ሆስፒታሉ በሁለቱ ልጆቼ ስም እየተገነባ ያለ ነው፡፡ ሁለቱም የህክምና ትምህርታቸውን ሲጨርሱ ቀስ በቀስ ሙሉ ለሙሉ ተረክበው ያስተዳድሩታል፡፡ ስራው ለስጋም ለነፍስም አትራፊ ነው፡፡ ጌታ ደግሞ እንዲባርክላችሁ ፀሎቴ ነው፡፡›› አለ፡፡
መሰናዶው ተጠናቆ ቤተሰብና የፌሎው ልጆች ብቻ ቀረን፡፡ ኢንቱዬ እንባ እየተናነቃት ‹‹በእናንተ ሆስፒታል ግን መታከም አቅቶት የሚሞት አይኖርም አይደል?›› አለችን፡፡ ሚቾዬ እየተፍለቀለቀች ‹‹በፍፁም!›› አለች፡፡
እንደተሰበሰብን አቤላን በቪዲዮ አስገብተነው ማውራት ጀመርን፡፡
ኢንቱ እየሳቀች ‹‹የጅማው …… እንዴት ነው ሀገሩ? ›› አለች፡፡ አቤላ ጅማ ዩኒቨርሲቲ ደርሶት የህክምና ትምህርቱን እየተከታተለ ነው፡፡ የሚያስፈልገውን ነገር ሁሉ እናሟላለታለን፡፡
እየሳቀ ‹‹ጅማ ቀሽትዬ ናት …… እናንተ ናፈቃችሁኝ እንጂ!›› አለ፡፡
እየተወራ በመሀል አቤላ ‹‹ሚቾ ግን ምን እግር ጥሎሽ ነበር የዛን ቀን ላይብረሪ ኢቦዬ ጋ የመጣሽው?›› አለ፡፡
‹‹እኔስ ባሌ እንደሚሆን ታውቆኝ ይሆናል፡፡ አንተ ምን ሆነህ ነበር አጠገብህ ስቀመጥ ያመናጨቅከኝ?›› ሳቀች፡፡
‹‹እኔማ የሀብታም ልጅ አጠገቤ ሲቀመጥ ይጨንቀኝ ነበር፡፡ የምሸታቸው ምናምን ይመስለኝ ነበር፡፡ ከዚያ በፊት ሙድ ይዘውብኝ ያውቃሉ፡፡ ለዚያ ነው፡፡››
‹‹እሱማ ትሸታለህ እኮ!›› አልኩ፡፡ ሁላችንም በአንድነት ሳቅን!
‹‹ቆይ ልምጣላችሁ ብቻ!›› ዛተብን፡፡
እየተጫወትን መሸ፡፡ ሁሉም ሄደው አብዱኬና ኢንቱ ከልጆቻቸው ጋር ቀሩ፡፡ አብዱኬ ‹‹ጋሼ እንዳይደብረው ቶሎ እንሂድ!›› ብሎ ተነሳ፡፡ ከኢንቱዬ ጋር ተያይዘው ወጡ፡፡ መኪናቸው ከበር እስኪወጣ ድረስ ሸኝተናቸው ተመለስን፡፡ የአብዱኬ እናት አልፈዋል፡፡ እነአብዱኬ ቤተል ላይ ቆንጅዬ ቪላ ቤት ተከራይተው ይኖራሉ፡፡
እኔና ሚቾ ወደ መኝታ ክፍላችን ገብተን መጫወት ጀመርን፡፡
‹‹ስሚማ ሚቾዬ ዛሬ አንዲት የክፍላችንን ልጅ ተዋውቄ ……››
‹‹አምስት አመት ሙሉ ሳትተዋወቃት ……… እሺ?››
‹‹አንቺ ታውቂያታለሽ እኮ መሰለኝ ሀፍሷ ምናምን ነው ስሟ!››
‹‹አዎ አውቃታለሁ፡፡›› ሚቾ ለመውለድ ብላ ትምህርት ስላቋረጠች ከኛ አንድ አመት ትዘግይ እንጂ አንድ ባች ነበርን፡፡
‹‹እነሱ እዚህ ቤተል ቢሮ አላቸው ………›› የነገረችኝን ሁሉ ተረክኩላት፡፡
አብረን ለመሄድ ተስማማን፡፡
ሀፍሷ ጋር ደውዬ ቅዳሜ እንደሚመቸን ነገርኳት፡፡ ለምን እንደሆነ ባላውቅም ከነገረችኝ በኋላ ቢሯቸውን የማየት ፍላጎቴ ጨምሯል፡፡
ቅዳሜ ከጠዋቱ አራት ሰዓት ገደማ ከሚቾዬ ጋር ትንሳኤን እንደያዝን ወደ ቤተል አደባባይ አቀናን፡፡ ሀፍሷ ቤተል አደባባዩ ጋር እየጠበቀችን ነበር፡፡ ቤተል አልመሻን ህንፃ ፓርኪንግ ውስጥ መኪናችንን አቁመን የህንፃው መግቢያ ጋር ቆማ እየጠበቀችን ወደነበረችው ሀፍሷ ሄድን፡፡ ሀፍሷ ሚቾን ስማ እኔ ትንሳኤን እንዳቀፍኩ ወደ ፎቅ መውጣት ጀመርን፡፡ ሶስተኛው ፎቅ ላይ ደርሰን ወደ ግራ ታጠፍንና በትልቁ ‹‹ኡሚ›› የሚል ፅሁፍ ወዳለበት ቢሮ ገባን፡፡ ሚቾዬ በትናንሽ የውሀ መጠጫዎች ላይ የተነቀሰውን የተቋሙን መሪ ቃል አስነበበችኝ፡፡ ‹‹ለበጎነት መስፈርት የለውም!›› ይላል፡፡ ፈገግ አልኩ፡፡ ፕሬዝዳንቱ መጥቶ በትህትና ከተዋወቀን በኋላ ስለሚሰሯቸው ስራዎች እና ስለሚደግፏቸው ቤተሰቦች ችግር በደንብ አስረዳን፡፡ በልቤ እውነትም ችግሩን ተረድተውታል ብዬ አሰብኩ፡፡ ኖሬ ስላየሁት ከማንም በላይ ችግሩን አውቀዋለሁ፡፡ ሚቾ የአባልነት ፎርም እየሞላች ሀፍሷ ወደ ሌላኛው ክፍል ወስዳ ህፃናትን በጎነት ለማለማመድ የቀረፁትን ፕሮጀክት ታሳየኝ ጀመረች፡፡ ኮምፒዩተር ከፍታ ከዚህ ቀደም የሰሯቸውን ስራዎች በፎቶ አስጎበኘችኝ፡፡
እነሚቾ ወዳሉበት ክፍል ስንመለስ ፕሬዝዳንቱ ትህትና ተላብሶ ‹‹ነገ ከቻላችሁ አንፎ ቤተሰቦችን ልናይ ስለምንሄድ ብትመጡ ደስ ይለናል፡፡›› አለ፡፡ ሚቾ ዞር ብላ ተመለከተችኝ፡፡ አንገቴን በአሉታ ወዘወዝኩ፡፡
‹‹አንፎ ምንም አያደርግህም …… ሂድና ፍርሀትህን አሸንፈው፡፡›› አፈጠጠችብኝ፡፡
ውሳኔያችንን እንደምናሳውቃቸው ተነጋግረን ተመለስን፡፡
ለሊቱን ሙሉ ልሂድ አልሂድ የሚለውን ሳስብ ቆየሁ፡፡ ፍርሀቴን የማሸንፍበት ጉልበት ፈለግኩ፡፡ ሚቾ እንድሄድ ለማድረግ የቻለችውን ያህል ጣረች፡፡ ተሳካላት፡፡ እየቀፈፈኝም ቢሆን እናትና አባቴ ወደ ሞቱበት ሰፈር ለመሄድ ተስማማሁ፡፡
.
ይቀጥላል ….
696 views12:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 15:01:59 ከተራራው ላይ
ክፍል አስራአራት
(ፉአድ ሙና)
.
‹‹በፍቅርሽ እሳት፣ ባንቺው ሱባዔ፣
ጨለማው ነጋ፣ መጣ ትንሳኤ!
እሳት ያበራል?››
.
ፈገግ ስል ድፍረት አገኘች መሰል ውትወታዋን ቀጠለች፡፡ ‹‹በላ ንገረኝ!›› በጉጉት ትመለከተኛለች፡፡
ታሪኬን ዘና ለማለት እየሞከርኩ አጫወትኳት፡፡ ምናልባት ለሚሰሩት ስራ ይጠቅማቸው ይሆናል ብዬ አስቤያለሁ፡፡
ማኪያቶዋን እየማገች ‹‹ግን እኮ አሁንም ለምን ሐይማኖቱን ቀየረ የሚለውን ጥያቄ አልመለስክልኝም!›› አለች፡፡
በረዥሙ ተንፍሼ ማብራራት ጀመርኩ፡፡
‹‹እንደነገርኩሽ ሙስሊም ልባል እንጂ ስለእስልምና ምንም የማውቀው ነገር አልነበረም፡፡ ድሀ እንደመሆኔ ልማር የምችልበት ቀላል መንገድም አልነበረም፡፡ በዚህ ላይ ደግሞ የመከራ አይነት ያለማቋረጥ ይዘንብብን ነበር፡፡ በመከራችን ጊዜ ሁሉ ከጎናችን ሆነው ያላቸውን ያካፈሉን ደግሞ ሙስሊሞች ሳይሆኑ እነማህሌት ነበሩ፡፡››
‹‹ሚቾ የኛ ግቢዋን ነው?››
አንገቴን በአዎንታ ነቅንቄ ቀጠልኩ፡፡ ‹‹እና ከእኔ ምንም ሳይፈልጉ …… የተረጂነት መንፈስም እንዳይሰማኝ ጓደኛ ሆነው ያገዙኝ እነሱ ነበሩ፡፡ በሂደት ደግሞ ከማህሌት ጋር የነበረን ግንኙነት ወደ ፍቅር ተቀየረ፡፡ እኔ እልም ያልኩ ድሀ …… እሷ የናጠጠ ሀብታም ልጅ! ግን የኪስ ብቻ ሀብታም አልነበሩም፡፡ አባቷ እንዴት ከደሀ ጋር ተፋቀርሽ አላላትም፡፡ መሰናክል የሆነብን የሀይማኖቱ ጉዳይ ብቻ ነበር፡፡ እሷ ስለሀይማኖቷ በደንብ ታውቃለች፡፡ እኔ ደግሞ ምንም የማውቀው ነገር አልነበረም፡፡ ፍቅረኛ በሆንን ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ አባቷ ጠርቶ አናገረኝ፡፡ እንደልጁ እያየ የሐይማኖቱ ጉዳይ እንዳሳሰበውና ምን መፍትሔ ልናበጅለት እንደምንችል ጠየቀኝ፡፡ ምንም ሳላመነታ ሐዋርያት እሆናለሁ አልኩት፡፡ በጣም ደስ አለው፡፡ ከዚህ በኋላ ልጁ እንደሆንኩ ነገረኝ፡፡ ከህመምተኛ እህቴ ጋር ተቀብሎን በቤቱ እንድንኖር አደረገ፡፡››
‹‹ስለሀይማኖቱ ሚቾ የነገረችህ ነገር ነበር? አምነህበት ነው ወይስ?››
‹‹ስለሐዋርያት እንኳን ስለእስልምና ከማውቀው ያነሰ ባውቅ ነው፡፡ ሐይማኖት ያኔም ሆነ አሁን ጉዳዬ አይደለም፡፡ ያመንኩት ማህሌትን ነው፡፡ ፈጣሪ ካለ እንኳን ያለ የሚመስለኝ ማህሌት ላይ ነው፡፡ የደስታዬ …… የእረፍቴ ሁሉ ምንጭ እሷ ነበረች፡፡ እሷን ሳይ ደስታን የማይ ይመስለኛል፡፡ ተያይዘን ወደ ገሀነም እንግባ ብትለኝ እንቢ አልልም፡፡ ገሀነምን ገነት የማድረግ አቅም ያለው ደግነት እንዳላት ይሰማኛል፡፡ እንደዚያ ተርቤ በእጇ የበላሁትን አልረሳም፡፡ በየአንዳንዱ አዲስ ቀን እንደ አዲስ የማስታውሰው ጨጓራዬ ሲነድ ማህሌት ያጎረሰችኝን ጉርሻ ነው፡፡  ሙስሊሞችን ሳይ ……… በተለይ ሙስሊም ሀብታሞችን ሳይ በጣም እናደዳለሁ፡፡ እኛ ስንራብ እነሱ ከቤተሰባቸው ጋር በምቾት ሲደሰቱ ነበር፡፡ እዚያ የመከራ መሸሸጊያ ተራራ ላይ ስናነባ አንዳቸው እንኳን አለንላችሁ አላሉንም፡፡ እህቴ ሀይማኖቷን መማር ፈልጋ ገንዘብ ስለሌላት መማር አልቻለችም፡፡ አንዳንዱ በራሱ ጫማ እየለካን ስለእህቴ ቀሚስ መወጣጠር ሊወቅሰን ይፈልጋል፡፡ እሷ እኮ እሱን እንኳን በስርዓቱ ለመማር ፈልጋ ገንዘብ የላትምና አልቻለችም፡፡ እኔን ከሴት ጋር በነበረኝ ግንኙነት ሊተቹኝ ይፈልጋሉ፡፡ እኔ መጀመሪያ እምነቱን ሳውቅ ነው እኮ እንደነሱ ሊያሳስበኝ የሚችለው አይደል እንዴ? መጥፎ ነገር መፈለግ ብቻ! ስትሳሳቺ አሉ! ሲርብሽ ግን የሉም! በሰዎች ደግነት ተማርከሽ ሀይማኖትሽን ስትቀይሪ በዘይት አታለሏቸው እያሉ ያሙሻል፡፡››
እንባዋ አይኗን ሞልቶ ለመውረድ እየታገለ ሳግ ባጠረው ድምፅ ‹‹ግን እኮ ሐይማኖቱ እንደዚያ አይደለም ……›› አለች፡፡
‹‹እኔ ሐይማኖቱን ሳይሆን ሐይማኖተኞቹን ነበር ያገኘሁት! ወሬ ሳይሆን ተግባር ነው የሚታየው!››
‹‹እህትህስ? እሷስ እንዴት ሆነች?››
‹‹ህክምናዋን ተከታትላ …… አሁን ባለ ትዳርና የሁለት ልጆች እናት ናት፡፡››
‹‹እሷም ሀይማኖቷን ቀየረች?››
‹‹አልቀየረችም!››
‹‹ሙስሊም ነው ያገባችው?››
‹‹አዎ!›› 
ልጅቷ እየተንሰቀሰቀች ማልቀስ ጀመረች፡፡ አቅፌ ላባብላት አልኩና ሙስሊም መሆኗ ትዝ ሲለኝ እጄን ሰበሰብኩ፡፡ እንድትረጋጋ በማሰብ ‹‹ሰፈርሽ የት ነው?›› ብዬ ጠየቅኳት፡፡
እንባዋን እየጠራረገች ‹‹አየርጤና ……›› አለች፡፡ 
ሰዓቴን ስመለከተው የትምህርት ሰዓታችን እየደረሰ ነበር፡፡ እንድንመለስ ጠየቅኳት፡፡ ሂሳብ ለመክፈል ከተጨቃጨቅን በኋላ እሷ ከፍላ ወደ መኪናዋ ተመለስን፡፡ ወደ ጥቁር አንበሳ እየነዳች ዋናውን መንገድ እንደያዝን ‹‹ከዚያ በኋላ ወደ ድሮ ሰፈርህ ሄደህ ታውቃለህ?›› አለችኝ፡፡
‹‹አላውቅም! የሰፈሩ ስም ሲጠራ ትዝ የሚለኝ ያሳለፍነው መከራ ነው፡፡ አባቴም እናቴም የሞቱበት ሰፈር ነው፡፡ ብሄድ እዚያው የምቀር …… ድጋሚ ድሀ የምሆን የምሆን ይመስለኛል፡፡  ድርሽ ብዬ አላውቅም፡፡››
‹‹በአቅምህ የድሮ ሰፈርህ ላይ የነበሩ ሰዎችን ለመርዳት አልሞከርክም?››
‹‹እኔ አልሂድ እንጂ እነማህሌት አሁንም ይሄዳሉ፡፡ ኢንቱዬም ትሄዳለች፡፡››
ልጅቷ መረበሿን ላለማሳየት እየጣረች ‹‹ድፍረት አይሁንብኝና ድጋሚ ብንገናኝ ደስ ይለኛል፡፡ እዚህ ሳይሆን እዚያው ሰፈርህ ማለት ነው፡፡ ቢሯችንን ባሳይህ …… ፕሬዝዳንታችንን ባስተዋውቅህ ደስ ይለኛል፡፡›› አለች፡፡
‹‹ችግር የለውም፡፡ ስራችሁ ተመችቶኛል ቀኑን ንገሪኝና ከሚቾ ጋር እንመጣለን፡፡››
‹‹ሲመችህ!››
ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ግቢ ውስጥ ገብተን መኪናዋን ቦታ ፈልገን ካቆምን በኋላ ወደ ክፍል ገባን፡፡ የተቀመጥነው አብረን ነበር፡፡ ትምህርቱ እንዳለቀ ተማሪው በግርምት ይመለከተን ጀመር፡፡ በፍፁም ይሆናል ብለው ያላሰቡትን ነገር ያዩ ይመስላሉ፡፡ በእርግጥ ከሙስሊም ተማሪ ጋር አብሬ ስቀመጥ የመጀመሪያዬ ነበር፡፡ ከወትሮው በተለየም ፊቴ ላይ ፈገግታ ነበር፡፡ ልጅቷ አስገድዳኝም ቢሆን ስላወራሁ ደስ ብሎኛል፡፡
‹‹ስምሽ ግን ማነው?›› አምስት አመት አብረን ተምረን ስሟን አለማወቄ አሳፍሮኛል፡፡
በግርምት እያየችኝ ‹‹የምርህን ነው? ማለቴ አታውቀውም?›› አለች፡፡
አንገቴን በአዎንታ ነቀነቅኩ፡፡ እየሳቀች ‹‹ሀፍሷ እባላለሁ፡፡›› አለችኝ፡፡
ከሀፍሷ ጋር እስከ መኪናዬ እያወራን ከሄድን በኋላ ተሰነባበትን፡፡ ከእሷ ጋር እንደተሰነባበትን ማህሌት ደወለች፡፡
‹‹ሚቾዬ የኔ ቆንጆ ……››
‹‹አብርሽዬ ማር ……››
‹‹ወዬ ምን ልታዘዝ?››
‹‹ከclass ወጣችሁ አይደል?››
‹‹አዎ አሁን መኪናዬ ውስጥ ገባሁ፡፡ እየመጣሁ ነው፡፡››
‹‹በቃ አፍጥነው ሁሉም ሰው መጥቷል አንተ ነህ የቀረኸው! One last thing ርችት ረስቻለሁ፡፡ ይዘህ ና!››
‹‹ሰምቻለሁ ክቡርነትዎ! በመቶ ሰማንያ ነው እየነዳሁ የምመጣው!››
‹‹ስርዓት ያዝ!››
ሳቅኩኝ፡፡ ተሰነባብተን ወደ ቤት መንዳት ጀመርኩ፡፡ ያዘዘችኝን ገዛዝቼ ቤት ደረስኩ፡፡ ግቢው ውስጥ ድንኳን ተጥሎ ምግቡ ሁሉ በአይነት በአይነቱ ተዘጋጅቷል፡፡ ገና ስገባ ምህረት እየሳቀች ‹‹በልጅህ ልደት ቀን እንኳን Class የማትቀጣ ጉድ!›› አለችኝ፡፡ እየሳቅኩ አቅፌያት ወደ ድንኳኑ ተጠጋሁ፡፡ የፌሎው ልጆች በሙሉ አሉ፡፡
አብዱኬ ልጁን አቅፎ እንደቆመ ‹‹እሺ አባትየው …… ለልጅህ ልደት እንኳን ቀድመህ አትገኝም አይደል? …… ምነው ግን እኔ ካልገባሁ የአስተማሪው ልብ አይመታም አልክ?›› አለኝ፡፡ የሚያምር እርሳስ ቀለም ያለው ሱፍ ለብሷል፡፡ እየሳቅኩ ተጠመጠምኩበት፡፡  ምህረት ርችቱን ተቀብላኝ ሄደች፡፡ ሁሉንም እየዞርኩ ሰላም ካልኩ በኋላ ማህሌት ደወለችልኝ፡፡
‹‹አልደረስክም እንዴ?›
648 views12:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 17:53:45
623 views14:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ