Get Mystery Box with random crypto!

University of Ethiopia

የቴሌግራም ቻናል አርማ temihert — University of Ethiopia U
የቴሌግራም ቻናል አርማ temihert — University of Ethiopia
የሰርጥ አድራሻ: @temihert
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.27K
የሰርጥ መግለጫ

MOE / STAR ACADEMY
✅ይህ በአይነቱ ልዩ የሆነ ቻናል የተዘጋጀው በ ማህበረሰቡ ጥያቄ መሰረት ሲሆን በውስጡም ለተለያዩ የክፍል ደረጃዎች የሚሆኑ ኖቶች፣pdf፣ሞዴል ፈተናዎች፣ማትሪክና የተለያዩ መረጃዎችን ያገኛሉ።
📚Freshma tutorial በዮኒቨርስቲ ተማሪዎች የተቋቋ
ad service: 📚 MOE በተለየ መልኩ
✅መረጃዎች በፍጥነት እንዲደርሶት ቻናላችንን #UNMUTE ✔ ያድርጉ ⏳

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-28 11:44:33 Live stream started
08:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 09:40:42 ተወዳጆች ሆይ Entrance Exam ላይ በየአመቱ ከዚህ part ላይ ፈተና ስለሚወጣበት ደጋግሜ ለቀቁላችሁ። እንዳትሰላቹ ።


Future Perfect Tense
_________________

Affirmative form
Sub + will + have + V3.

Negative form
Sub + will not + have + V3.

Question form
Will + Sub + have + V3?

Usage

#1) to talk about an event that will be finished and complete before a specified time in the future.

ከተገለፀው ወይም ከተጠቀሰው ጊዜ በፊት የሚከናወን የወደፊት ድርጊትን ለመግለፅ - ማለትም ወደፊት ወይም future ላይ የሚከናወን አንድ ድርጊት አለ ፡ ታድያ ይህ ወደፊት የሚከናወነዉ ድርጊት ከ ተጠቀሰው ጊዜ በፊት አስቀድሞ የሚከናወን ከሆነ ፡ ይህ ከተጠቀሰው ጊዜ በፊት አስቀድሞ፡ future ላይ ወይም ወደፊት የሚከናወነው ድርጊት በ future perfect ይገለፃል ማለት ነው። ስለዚህ ሁለት ሀሳቦችን መረዳት አለብን።

ሀሳብ 1 -- የተጠቀሰው ወይም የተገለፀው ጊዜ(specified time).
ምሳሌ ከ 2021 በፊት÷ ቀጣይ ሳምንት እህን ጊዜ፡ ከማግባቴ በፊት ወዘተ።

ሀሳብ 2: ወደፊት ወይም future ላይ የሚከናወነው ድርጊት።

ስለዚህ ከተጠቀሰው ወይም ከተገለፀው ጊዜ በፊት አስቀድሞ: future ላይ ወይም ወደፊት የሚከናወነውን ድርጊት ለመግለፅ future perfect ን እንጠቀማለን ማለት ነው። ምሳሌዎችን እንመልከት፡

ምሳሌ 1-- መምህራችሁ assignment ዛሬ ሰጣችሁ፡ ከዛ ከነገ ጀምረህ እየሰራህ እስከ ሰኞ መጨረስ አሰብክ። ከዛ ጓደኛህ አሳይመንቱን መቼ ትጨርሳለህ ብሎ ሲጠይቅህ ከሰኞ በፊት እጨርሳለሁ አልከው። ስለዚህ

ሀሳብ 1: የተገለፀው ወይም የተጠቀሰው ጊዜ ማለትም ከሰኞ በፊት።

ሀሳብ 2: future ላይ ወይም ወደፊት የሚከናወነው ድርጊት፡ እርሱም ነገ፡ ነገወድያ ምናምን አሳይመንት ሰርቶ መጨረስ።
ስለዚህ አሳይመንት ሰርቶ መጨረስ ወደፊት የሚከናወን ድርጊት ነው፡ ታድያ ይህ ድርጊት ከተገለፀው ጊዜ በፊት ማለትም ከሰኞ በፊት የሚከናወን ድርጊት ስለሆነ future perfect እንጠቀማለን ማለት ነው።

I will have finished the assignment by monday.(by means before.) ከሰኞ በፊት አሳይመንቱን ሰርቼ እጨርሳለሁ።

ምሳሌ2: አሁን ላይ አንተ የድግሪ ወይም ቅድመ ምረቃ ተማሪ ነህ፡ ገና አላገባህም። እናም ከማግባትህ በፊት ማስትሬት ድግሪ የመስራት ሀሳብ አለህ ወይም እሰራለሁ ብለሀል። ስለዚህ ሁለት ሀሳቦችን ልንረዳ ይገባል።

ሀሳብ 1: የተጠቀሰው ጊዜ ማለትም ከ ማግባትህ በፊት።

ሀሳብ 2: ወደፊት ወይም future ላይ የሚከናወነው ድርጊት ፡ ማለትም ማስትሬት መስራትህ።

ስለዚህ ማስትሬትህን መስራት ወደፊት የሚከናወን ድርጊት ነው። ታድያ ይህ ወደፊት የሚከናወነው ድርጊት ከተጠቀሰው ጊዜ በፊት ማለትም ከማግባትህ በፊት የሚከናወን ነው፡ ስለዚህ ከተጠቀሰው ጊዜ በፊት የሚከናወነውን ይኸን ድርጊት በ future perfect እንገልፀዋለን ማለት ነው።

By the time I get married, I will have made M.SC degree in Ecology.(ከማግባቴ በፊት በ Ecology የማስትሬት ድግሪ እሰራለሁ።)

I will have made M.Sc degree in Ecology by the time I get married.( ከማግባቴ በፊት በ Ecology የማስትሬት ድግሪ እሰራለሁ።)

ሁለቱም ምሳሌዎች possible ናቸው። 'by' ማለት 'before' እንደማለት ነው።

#2) to make prediction about future event that will be complete before a specified future time.(ከተጠቀሰው ጊዜ በፊት ፡ ይከናወናል ወይም አይከናወንም ተብሎ የተተነበዬን ድርጊት ለመግለፅ።) ሁለት ሀሳቦችን ልንረዳ ይገባል።

ሀሳብ 1: የተጠቀሰው ወይም የተገለፀው ጊዜ።

ሀሳብ 2: ወደፊት ወይም future ላይ ይከናወናል ወይም አይከናወንም ተብሎ የተተነበዬ ድርጊት።

ስለዚህ ከተገለፀው ወይም ከተጠቀሰው ጊዜ በፊት ይከናወናል ወይም አይከናወንም ተብሎ የተተነበየውን የወደፊት ድርጊት ለመግለፅ፡ future perfect ን እንጠቀማለን ማለት ነው።

ምሳሌ፡ በአሁኑ ሰአት የ corona virus መድሓኒት አልተገኘለትም። እናም አንተ ሳይንቲስቶች መድሀኒቱን ከ 2022 በፊት ያገኙታል ብለህ ተነበይክ። ስለዚህ ሁለት ሀሳቦችን እንረዳ፡

ሀሳብ 1: የተጠቀሰው ጊዜ ማለትም ከ 2022 በፊት።

ሀሳብ 2: ወደፊት ይከናወናል ብለህ የተነበይከው ድርጊት፡ እርሱም የኮሮና መድሐኒትን ሳይንቲስቶች ማግኘት።

ስለዚህ ወደፊት ይከናወናል ብለህ የተነበይከው ድርጊት ማለትም ሳይንቲስቶች የኮሮና መድሐኒት ማግኘት ከተጠቀሰው ጊዜ በፊት ማለትም ከ 2022 በፊት ይከናወናል ወይም ይደረጋል ብለህ ስለተነበይክ future perfect ን ትጠቀማለህ።

Scientists will have discovered the cure for corona virus by the year 2022.(ከ2022 በፊት ሳይንቲስቶች የኮሮና መድኒትህን ያገኛሉ።)

ነገር ግን 2022 ላይ ሳይንቲስቶች የኮሮና መድሐኒት ያገኛሉ ብለህ ከተነበይክ ወይም predict ካደረክ future perfect ን ሳይሆን simple future ን ነው የምንጠቀመው። ልዩነቱ፡

Scientists will have discovered the cure for corona virus by the year 2022.( ሳይንቲስቶች ከ 2022 በፊት የኮሮና መድሐኒትን ያገኛሉ።)

Scientists will discover the cure for corona virus in 2022.(ሳይንቲስቶች 2022 ላይ የኮረና መድሐኒትን ያገኛሉ።)

ማስታወሻ -- Entrance Exam ላይ በየአመቱ future perfect ን የተመለከቱ ጥያቄዎች ስለሚወጡ፡ በደንብ ልንረዳው ይገባል።

join and share

@Temihert
157 viewsB£k, 06:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 19:37:51 Live stream finished (2 minutes)
16:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 19:35:28 Live stream started
16:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 20:31:01 የ2014 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ከመስከረም 30 እስከ ጥቅምት 11 ቀን 2015 ድረስ በሁለት ዙር እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል

ለዚህም ተማሪዎች እራሳቸውን እንዲያዘጋጁ ጥሪ አቅርቧል።

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ ረዲ ሽፋ ለኦቢኤን በሰጡት ቃል ፤ በአጠቃላይ በሁለት ዙር በሚሰጠው ፈተና ከ984,000 በላይ ተማሪዎች ፈተናውን እንደሚወስዱ ገልፀዋል።ፈተናውን ከሚወስዱት ውስጥ የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ቁጥር 622,739 መሆኑን አመልክተዋል።

የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ብዛት ያላቸው በመሆኑ በመጀመሪያው ዙር ከመስከረም 30 እስከ ጥቅምት 3 /2015 አስቀድሞ ፈተናው እንደሚሰጣቸው አቶ ረዲ ተናግረዋል።

የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ቁጥር ደግሞ 361,279 ሲሆን በሁለተኛው ዙር ከጥቅምት 8 እስከ 11/2015 ፈተናውን እንደሚወስዱ አስረድተዋል።

ከዚህ ቀደም የነበሩ የፈተና ችግሮችን ለመፍታት ፈተናው በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች እንደሚሰጥ አረጋግጠዋል ፤ ፈታኞቹ ደግሞ የዩኒቨርሲቲ መምህራን መሆናቸውን አሳውቀዋል።

በተጨማሪም ፤ ፈተናው ከዚህ ቀደም ከነበረው ከ4 ኮድ ከፍ ማለቱን ገልፀዋል። ፈተናው ተዘጋጅቶ እየታተመ ሲሆን ፈተናው እስከሚሰጥበት ቀን ድረስ ተፈታኞች እራሳቸውን ማዘጋጀት እንዳለባቸውም አሳስበዋል።
@Temihert
@Temihert
313 viewsB£k, 17:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-23 22:12:38 https://t.me/Iwellej
302 viewsB£k, 19:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-23 18:53:25 የ2014 የ12ኛ ክፍል ፈተና ከመስከረም 30 እስከ ጥቅምት 11 ቀን 2015 ይካሄዳል።

ከ984,000 በላይ ተማሪዎች ይፈተናሉ

የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ቁጥር 622,739 ስሆኑ በ 1ኛ ዙር ከመስከረም 30 እስከ ጥቅምት 3 ይፈተናሉ።

የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ቁጥር 361,279 ሲሆኑ በሁለተኛው ዙር ከጥቅምት 8 እስከ 11ይፈተናሉ።

የፈተናው ቦታ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ስሆን ፈታኞች ደግሞ የዩኒቨርሲቲ መምህራን ናቸው።

@Temihert
@Temihert
364 viewsB£k, 15:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-31 14:35:02 " ፈተናው የሚቀር አይደለም " - ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ

* ዩኒቨርሲቲዎችና ኮሌጆች ተማሪዎቻችሁን አዘጋጁ !

የመውጫ ፈተና በ2015 ዓ/ም መሰጠት ይጀምራል። ይህን በተመለከተ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ለኢፕድ ከሰጡት ማብራሪያ ፦

" ... በሙሉ አቅማችን እየተዘጋጀን ነው። የሚቀር ነገር አይደለም ፤ 2015 ትምህርት ዘመን ማብቂያ ላይ ፤ ከዚህ በፊት እንደነበረው ዝም ብሎ ዲግሪ የሚሰጥበት ነገር ሀገሪቱን በጣም ክፉኛ ጎድቷታል የሚል እምነት አለን።

ይሄንንም ከዩኒቨርሲቲ ፕሬዜዳንቶች ጋር፣ ከግል ኮሌጆች ፕሬዜዳንቶች እና ኃላፊዎች ባለቤቶች ጋር ፣ ከዩኒቨርሲቲ መምህራን እና ተማሪዎች ጋር ሰፊ ውይይት ያደረግንበት ነው።

ይሄ አዲስ ሀሳብ አይደለም አተገባበሩ ነው አዲስ የሆነው። ከዚህ በፊት ተሞክሮ ተቃውሞ ስለንበር ነው የተተወው።

የህግና የህክምና ትምህርቶችን ብቻ እንዲሰጡት አድርጎ አሁንም እየተሰጡ ሌሎች በሙሉ ተትተው ነበር።

አሁን ግን በአጠቃላይ ከከፍተኛ ትምህርት ጥራት ችግር ጋር በተገናኘ ምንም ልንወጣው የማንችለው እና ያን ጥራት ለማስተካከል ዩኒቨርሲቲዎቹ በራሳቸው ባስተማሩበት እና እራሳቸው በሰጡት ፈተና ብቻ የሚለኩበት ሁኔታ ከጀርባው ያለ ጠንካራ የሞራል መሰረት ይጠይቃል።

ዩኒቨርሲቲዎቹ እራሳቸው ድግሪ ስንሰጥ ለማህበረሰቡ ይሄ ሰው እንዲህ እንዲህ አይነት ትምህርቶችን፣ እውቀቶችና ክህሎቶች አሉት ብለን ነው እየነገርን ያለነው።

... ከዚህ በፊት አንዱ የነበረው ችግር ማሳለፍ የሚባል ነገር አለ። ዝም ብሎ ማሳለፍ ምክንያቱም ተማሪዎች ከወደቁ የትምህርት ክፍሉን ድክመት ያሳያል እየተባለ ሲሳራበት የነበረው ነገር ምን ያህል ሀገሪቱን እንደጎዳት አሁን ለውይይትም የሚቀርብ አይደለም።

እኔ በዚህ ጉዳይ ባለፉት ሰባት (7) ወራት በትምህርት ዘርፍ ከሚሰሩ የዩኒቨርሲቲ ፕሬዜዳንቶች የግል ኮሌጆች ባለቤቶች እንደዚህ አይን ያወጣ የለም መሆን የለበትም የሚል ክርክር አልሰማሁም። ሁሌ የሚሰማው ለምን በኛ ጊዜ ? ለምን ባንተ ጊዜ ለምን በሌላውስ ሰው ጊዜ የሚለውን ልትመልስ አትችልም ይሄ ዝም ብሎ ደረቅ ክርክር ነው።

በአንድ በሆነ ጊዜ መጀመር አለበት ምክንያቱም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጥራት ላይ እየደረሳ ያለው ጉዳት ሀገሪቱን ከፍተኛ ዋጋ እያስከፈላት ነው። ይሄንን ዝም ብለን ማለፍ አንችልም ብለን እየሄድንበት ነው።

ለተማሪዎችም ፣ ለወላጆችም፣ ለቤተሰብም አንድ (1) ዓመት የመዘጋጃ ጊዜ ሰጥተናል። ለኮሌጆችም ተማሪዎቻቸውን እንዲያዘጋጁበት ጊዜ ሰጥተናል ይሄን ጊዜ በደንብ ተጠቅመው ስራቸውን መስራት አለባቸው።

ይሄ የመውጫ ፈተና የተማሪዎች ፈተና ብቻ አይደለም። ከተማሪዎች በላይ የትምህርት ክፍሎች፣ የኮሌጆች ፣ የዩኒቨርሲቲዎች ፈተና ነው። ምን እያደረጉ ነው ዩኒቨርሲቲዎቹ የሚለውን እንደትምህርት ሚኒስቴር ከዚህ የምናገኘው ፤ እነዚህ ኮሌጆች ፣ ዩኒቨርሲቲዎች በእርግጥም ተማሪዎችን እያበቁ ነው ? ወይስ የዲግሪ ወፍጮ ቤት እንደሚሏቸው ዝም ብሎ ጊዜ እያስቆጠሩ ድግሪ የሚሰጡ ናቸው የሚለውን የምንለይበት ነው።

ስለዚህ የሚቀር አይደለም። ሁሉም እንደማይቀር አውቆ የተሰጠውን የመዘጋጃ ጊዜ በደንብ ተጠቅሞ ትምህርትን በደንብ አስተምሮ በደንብ አስጠንቶ ቢያዘጋጅ ነው የሚሻለው "

ኢፕድ/ቲክቫህ

ቻናላችን ይቀላቀሉ
╔════════════╗
JOIN:@Temihert
JOIN:@Temihert
╚════════════╝
732 viewsB£k, 11:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-30 14:18:12 #tutor

የ 12 ክፍል ፈተና ከመስከረም 20 በኋላ እንደሚሰጥ ይታወቃል ።


ከ 9-12 ክፍል ሙሉ ቻፕተር ያጠቃልላል ።


ከእኛም የተማሪዎችን ጭንቀት ለመቀነስ < maths&physics > በ 50 ብር ከ9-12ኛ ክፍል ያለውን እንድሁም ድሮ 10 ኛ ከፍል ሲሰጠ የነበረውን አና ኢንተራንስ ጥያቄዎችን ይሠራል ።


በየቀኑ ጠቃሚ ይለቀቃሉ።


አምና ከፍተኛ ዉጤት ባመጡ ተማሪዎች የአጠናና ዘዴ ፣ የገዜ አጠቃቀም ፣ የምርጫ ጥያቄዎች መስሪያ መንገድ
ሚሰጥ ይሆናል ።


ሁሉንም < subject > ደሞ በ 100
ብር ማግኘት ይቻላል።


ከተፈታኝ ውጪ ላላቸው

ለ9 እና ለ 10, 50ብር

ለ11 አና ለ 12 80 ብር


ማሳሰቢያ

ኦንላይን ትምህርት ከ ጾታዊ ትንኮሳ ነጻ ነው ቶሎ ተመዝገቡ
https://t.me/Iwellej
620 viewsB£k, 11:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-29 14:36:17 #ትምህርት_ሚኒስቴር

" ፈተናው የሚቀር አይደለም " - ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ

* ዩኒቨርሲቲዎችና ኮሌጆች ተማሪዎቻችሁን አዘጋጁ !

የመውጫ ፈተና በ2015 ዓ/ም መሰጠት ይጀምራል። ይህን በተመለከተ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ለኢፕድ ከሰጡት ማብራሪያ ፦

" ... በሙሉ አቅማችን እየተዘጋጀን ነው። የሚቀር ነገር አይደለም ፤ 2015 ትምህርት ዘመን ማብቂያ ላይ ፤ ከዚህ በፊት እንደነበረው ዝም ብሎ ዲግሪ የሚሰጥበት ነገር ሀገሪቱን በጣም ክፉኛ ጎድቷታል የሚል እምነት አለን።

ይሄንንም ከዩኒቨርሲቲ ፕሬዜዳንቶች ጋር፣ ከግል ኮሌጆች ፕሬዜዳንቶች እና ኃላፊዎች ባለቤቶች ጋር ፣ ከዩኒቨርሲቲ መምህራን እና ተማሪዎች ጋር ሰፊ ውይይት ያደረግንበት ነው።

ይሄ አዲስ ሀሳብ አይደለም አተገባበሩ ነው አዲስ የሆነው። ከዚህ በፊት ተሞክሮ ተቃውሞ ስለንበር ነው የተተወው።

የህግና የህክምና ትምህርቶችን ብቻ እንዲሰጡት አድርጎ አሁንም እየተሰጡ ሌሎች በሙሉ ተትተው ነበር።

አሁን ግን በአጠቃላይ ከከፍተኛ ትምህርት ጥራት ችግር ጋር በተገናኘ ምንም ልንወጣው የማንችለው እና ያን ጥራት ለማስተካከል ዩኒቨርሲቲዎቹ በራሳቸው ባስተማሩበት እና እራሳቸው በሰጡት ፈተና ብቻ የሚለኩበት ሁኔታ ከጀርባው ያለ ጠንካራ የሞራል መሰረት ይጠይቃል።

ዩኒቨርሲቲዎቹ እራሳቸው ድግሪ ስንሰጥ ለማህበረሰቡ ይሄ ሰው እንዲህ እንዲህ አይነት ትምህርቶችን፣ እውቀቶችና ክህሎቶች አሉት ብለን ነው እየነገርን ያለነው።

... ከዚህ በፊት አንዱ የነበረው ችግር ማሳለፍ የሚባል ነገር አለ። ዝም ብሎ ማሳለፍ ምክንያቱም ተማሪዎች ከወደቁ የትምህርት ክፍሉን ድክመት ያሳያል እየተባለ ሲሳራበት የነበረው ነገር ምን ያህል ሀገሪቱን እንደጎዳት አሁን ለውይይትም የሚቀርብ አይደለም።

እኔ በዚህ ጉዳይ ባለፉት ሰባት (7) ወራት በትምህርት ዘርፍ ከሚሰሩ የዩኒቨርሲቲ ፕሬዜዳንቶች የግል ኮሌጆች ባለቤቶች እንደዚህ አይን ያወጣ የለም መሆን የለበትም የሚል ክርክር አልሰማሁም። ሁሌ የሚሰማው ለምን በኛ ጊዜ ? ለምን ባንተ ጊዜ ለምን በሌላውስ ሰው ጊዜ የሚለውን ልትመልስ አትችልም ይሄ ዝም ብሎ ደረቅ ክርክር ነው።

በአንድ በሆነ ጊዜ መጀመር አለበት ምክንያቱም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጥራት ላይ እየደረሳ ያለው ጉዳት ሀገሪቱን ከፍተኛ ዋጋ እያስከፈላት ነው። ይሄንን ዝም ብለን ማለፍ አንችልም ብለን እየሄድንበት ነው።

ለተማሪዎችም ፣ ለወላጆችም፣ ለቤተሰብም አንድ (1) ዓመት የመዘጋጃ ጊዜ ሰጥተናል። ለኮሌጆችም ተማሪዎቻቸውን እንዲያዘጋጁበት ጊዜ ሰጥተናል ይሄን ጊዜ በደንብ ተጠቅመው ስራቸውን መስራት አለባቸው።

ይሄ የመውጫ ፈተና የተማሪዎች ፈተና ብቻ አይደለም። ከተማሪዎች በላይ የትምህርት ክፍሎች፣ የኮሌጆች ፣ የዩኒቨርሲቲዎች ፈተና ነው። ምን እያደረጉ ነው ዩኒቨርሲቲዎቹ የሚለውን እንደትምህርት ሚኒስቴር ከዚህ የምናገኘው ፤ እነዚህ ኮሌጆች ፣ ዩኒቨርሲቲዎች በእርግጥም ተማሪዎችን እያበቁ ነው ? ወይስ የዲግሪ ወፍጮ ቤት እንደሚሏቸው ዝም ብሎ ጊዜ እያስቆጠሩ ድግሪ የሚሰጡ ናቸው የሚለውን የምንለይበት ነው።

ስለዚህ የሚቀር አይደለም። ሁሉም እንደማይቀር አውቆ የተሰጠውን የመዘጋጃ ጊዜ በደንብ ተጠቅሞ ትምህርትን በደንብ አስተምሮ በደንብ አስጠንቶ ቢያዘጋጅ ነው የሚሻለው "

#tikvahethiopia

Join at and share

https://t.me/Temihert
636 viewsB£k, 11:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ