2024-04-02 05:03:53
እየተደረገላቸው ይገኛሉ ።
$$$$$$$$ ቆላ ድባ $$$$$$$
ቆላ ድባ ከተማ ከጯሂት በመኪና የ 10 ደቂቃ አካባቢ ረቀት ያላት ጎረቤት ከተማ ስትሆን ትላንት መጋቢት 19 ( ረመዷን 18) አንድ ሙስሊም ወንድማችን ከሌሊቱ 7:00 ሰዓት ላይ አፍነው ወስደውታል አስከ አሁን በምን አይነት ሁኔታ እንዳለ ምንም አይነት መረጃ የለም ።
የዘረፋው ጉዳይ በጣም የከፋ ነው ቀበሌ 18 ገንፎ ቁጭ ከምትባል ትንሽ ሰፈር በአንድ ሌሊት ብቻ ስምንት ቤቶች ተዘርፈው አድረዋል ።
ይህን ሁሉ ችግር ከፊቱ ላይ ሲፈፀም የተመለከተው እና ከህዝበ ሙስሊሙም በየ ቀኑ የድረሱልን ሪፓርት የሚደርሰው የከተማችን እስልምና ጉዳዩች ምክር ቤት ( መጅሊስ) ችግሩን ተረድቶ ያለውን ግፍ አለም ያውቀው ዘንድ መግለጫ ለማውጣት ቢስማማም መግለጫው ከከተማ አስተዳደሩ እና ከፋኖ ጋር ያራርቀናል ባሉ ግለሰቦች አማካኝነት መግለጫው ሊቀር( ሊደናቀፍ ) ችሏል ።
የተከበራችሁ በመላው አለም የምትገኙ ሙስሊሞች በሙሉ እስከ አሁን የዘረዘርኩት ከብዙው በጣም ትንሹን ነው ፣እየታሰበብን የለው ደግሞ እጅግ በጣም የከፋ ነው ፣ ትላንት በግልፅ የገደለን መስጅዳችን ያቃጠለ ፓሊስ እና ሚሊሻ ዛሬም በድብቅ ከአጥፊወች ጋር አብሮ ሲሰራ እያየን ነው ለዚያም ነው የጎንደር ሙስሊም ምንም አይነት ወንጀል ሲፈፀምበት ፓሊስ ጣቢያ ሂዶ ሪፓርት አያደርግም ( ሁኔታ አይሞላም) ምክንያቱም የፀጥታ አካላት በተደጋጋሚ ከተጎጂው ይልቅ ለአጥቂው ወግነው ስላያቸው ።
ስለዚህ ከዚህ በላይ ገዳቱ ሳይከፋ ሁሉም ሙስሊም በዚህ በተከበረው ወር ዱዓ በማድረግ ፣ለመንግስት ቅርበት ያላችሁ ለመንግስት ግፊት በማድረግ ፣ለመጅሊስ ቅርበት ያላችሁ ወንድሞችም መጅሊሱ ሊፈፅማቸው ከሚገቡ ግዳጆች ሁሉ ከዚህ በላይ ከባድ ሀላፊነት ስለሌለው ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥቶ እንዲንቀሳቀስ ግፊት በማድረግ ሀላፊነታችሁን ተወጡ በማለት በአላህ ስም እንጠይቃለን ።
ከላይ የተዘረዘሩት መረጃወች በሙሉ ምንም አይነት ውሸት እና ግነት እንደለሌባቸው ከተጠቀሱ ቦታወች በመደወል ማረጋገጥ ይቻላል እንኳን የለሌ ግነት እና ውሸት ልጨምር ያለውንም እውነት በአግባቡ መግለፅ አልቻልኩም ።
ተፃፈ በ የጎንደር ሙስሊሞች ድምፅ
መጋቢት 20/2016 አ ል
13.2K viewsGumaa Saaqataa, 02:03