Get Mystery Box with random crypto!

Gumaa Saaqqataa

የቴሌግራም ቻናል አርማ gumaaoro — Gumaa Saaqqataa
የሰርጥ አድራሻ: @gumaaoro
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 42.17K

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2024-04-18 20:42:20 "በራስህ ላይ እንዲደርስ የማትፈልገውን በሌሎች ላይ አታድርግ"
.
.
ጥቅሷን የዘከርኳት ከትናንት በስተያ ከላይ ባስቀመጥኩት ምስል ወጣቶች በምስሉ ላይ የምንመለከታቸውን አባት ላይ ጸያፍ የሆነ እና ከሰውኛ ምግባር የወጣ ጋጠወጥነት በተጠናወተው ባህሪያቸው በእድሜ የሚበልጧቸውን አባት እያሸማቀቁ ቪድዮ ቀርጸው በተለያዩ ሚድያዎች ላይ ተለቅቆ እየተዘዋወረ ተመልክተናን።

እነዚህ አፋን ኦሮሞ እየተናገሩ በእኚህ አባት ላይ የሚዘባበቱ ወመኔዎችን መረንነትን በግልጽ ለመቃወም የግድ ከዚህኛው አልያም ከዛኛው ወገን መሆን ግዴታ አይደለም (ሰው መሆን ብቻውን በቂ ነው)

ይህ በዚህ እንዳለ ግን ቪድዮው ለየት ባለ መልኩ በሁሉም የሚድያ መረቦች ከፍየሏ በላይ ለምን ተስተጋባ ካልን ምክንያቱ ወጣቶቹ ኦሮምኛ ተናጋሪ ሰለባው ደግሞ አማርኛ መናገሩ ነው።

( በደል አድራሾቹ ኦሮምኛ መናገራቸው ኦሮሞ ያደርጋቸዋል ብሎ ድምዳሜ ላይ መድረስ ባይቻልም ማንነታቸውን በቀናት ውስጥ እናውቀዋለ። በነገራችን ላይ ይህ ተግባር የተፈጸመው ግንደበረት ላይ ሲሆን ሲዘባበቱ የነበሩት ሁለት ልጆች እና ቪድዮውን ሲቀርጽ የነበረው ሶስቱም በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ሰምተናል)
ወንጀለኛ ብሄር ባይኖረውም የሁነቱ ፈጻሚ "ኦሮሞ ነው " ከተባለ በአንድ ወገን በኩል ጩኸቱ ከድርጊቱ ከፍቶ መመልከቱ አዲስ አይደለም።
(አንዳንዶች የልጆቹን ተግባር ለመደገፍ "እኛም ከዚህ የበለጠ በተቃራኒ ወገን ተፈጽሞብናል ፣ በየ ቀኑ አስጸያፊ ስንሰደብ እንውላለን" የምትል ምክንያት ያቀርባሉ። ለዚህ የሚሆነው ምላሽ ግን " እኛ እነሱን አይደለንም ወላጆቻችን ያሳደጉን በሰፉ ነው" የሚል ነው መልሱ)

ሰዎቹ ይህን መሰል አጋጣሚን የሚጠቀሙበት ግለሰብን ለመኮነን ሳይሆን መላውን የኦሮሞን ህዝብ ለማሸማቀቂያ መጠቀም ክህሎታቸው ነው (በውርስ መልኩ ከትናንት እስከ ዛሬ ሲወርድ ሲዋረድ ከአባቶቻቸው የወረሱትም ይሄንኑ ነው)
ጀዋርን ሲኮንኑ ፣ ኦነግን አውሬ አድርገው ሲስሉ ብዙዎች በድርጅት አልያ በግለሰብ ደረጃ እየኮነኑ ይምሰላቸው እንጂ ሰዎቹ እያሉ ያሉት መላውን የኦሮሞ ህዝብ ነው።
(ይህንን ተግባር ቅዱስ አድርገው ሲያበረታቱ የነበሩ እንደ ጂጂ ኪያ እና የሚመስሏት በጣት የሚቆጠሩትን ብንመለከትም በመኮነኑ ላይ ያየናቸው ግምባር ቀደሞቹ የኦሮሞ ተወላጆች ናቸው።

ሳጠቃልል የህግ አካላት ወንጀለኞቹ ለፈጸሙት ጸያፍ ተግባር ለነገ አስተማሪ የሚሆን ፈጣን ፍርድ አግኝተው ለህዝቡ ማሳወቁ መልካም ነው እላለሁ።
12.8K viewsGumaa Saaqataa, 17:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-17 20:31:40
ከፍተኛ አውሎነፋስ የቀላቀለ ዝናብ በዱባይ ኤርፖርት
14.2K viewsGumaa Saaqataa, 17:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-17 17:03:16 Weeraara Faanoo ummata Godina saba oromo irraatti Guyyaa kaleessa fi Har'a gaggeefame irraatti Qotee Bultoonni miidhamun dhagahame jira.
Aanaa Dawwa caffa Ganda Gobaayya irraa 1.Adam Bullaa wareegame jira.
2.Ganda shakla irraa nama tokko
3.Ganda Abaayee irraa nama tokko.
Waluma galatti namoonni 3 wareegamu beekame jira.
15.0K viewsGumaa Saaqataa, 14:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-17 12:58:39
«እርዱኝ እርዱኝ እርዱኝ» ሰርካለም ማሞ

ሰርካለም ማሞ ትባላለች። የሁለተኛ ደረጃ ካንሰር ታማሚ ነች። ህክምና ከተከታተለች መዳን እንደምትችል ተነግሯታል። እናም በወዳጆቿ እገዛ እስካሁን ድረስ ህክምናውን ስትከታተል ቆይታ አሁን ግን በገንዘብ ምክኒያት ሊቋረጥባት እንደሆነ በሶሻል ሚዲያ ገጿ(TikTok) አጋርታለች።

«የህክምና ወጪየን በራሴ ለመሸፈን አረብ ሃገር ሄጄ እየሰራሁ ለመታከም ሞከርኩ ግን አልተሳካልኝም። ምን እንደማረግ አላውቅም። የሀገሬ ልጆች አግዙኝ»ትላለች።
እንደሌላው ሰው ሶሻል ሚዲያው ላይ ሚወራላት ልጅ አይደለችም። እባካችሁ እናግዛት።

ማገዝ ባንችል እንኳን ለብዙዎች እንዲደርስ #ሼር
አድርጉላት።

Serkalem Mamo
1000496895944
13.3K viewsGumaa Saaqataa, 09:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-15 22:24:51 ተራራው ድምጹን አጥፍቶ፣ ኮሽታ ሳያሰማ አላማጣን ለቆ ወጣ
16.5K viewsGumaa Saaqataa, 19:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-15 19:34:15
ሰበር የውጪ ዜና !!!

በአሁኑ ሰአት ታዋቂ የሆኑት የ አውስትራሊያው ጳጳስ ብፁእ አቡነ ማር ማርያም በአገልግሎት ላይ እያሉ በዚህ መልክ በስለት ተወግተው በ ሆስፒታል ይገኛሉ ።
@my_oromia
16.0K viewsGumaa Saaqataa, 16:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-15 19:29:57
Jaal Magarsaa Bariif jaallansaa imaluuf daandii yoo eegalan Jaal Galaasaa Dilboo jaallan imalaaf qopha'aniif gaaffii tokko dhiheessaniif.
"Akka isin Moqaadishoo geessan maaliin barraa?" Jedhanii jaallan imalaaf daandii qabatan garaa raasnaan Jaal Magarsaa Barii deebii murannoo qabdu tokko akkas jedhanii deebisaniif....
" Raadiyoo Somaalee Sagantaa Afaan Oromoodhaanin wallee Yuunus Abdullaayii 'Bilisummaan Aannanii' jedhun isin affeera" jedhanii imala dadhabsiisaa sana eegalan. Moqaadishoo osoo hin gahin Shinniggaa bakka jedhamutti harka shiftoota sanaa bu'anii wareegaman.

BAGA EEBILA 15, GUYYAA GOOTOTA OROMOO, Baga GEESSAN!

Waaqayyo nama kaayyoo jaallan kufanii galmaan gahu nu haa taasisu!

Abdisa Tumme
15.1K viewsGumaa Saaqataa, 16:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-15 18:17:37 ወደ ሁዋላ መመለስ እንደማይሆን አምኗል፡፡ ያለው አንድና አንድ አማራጭ ሊገድሉት ከተዘጋጁት ጋር መጋፈጥ ፡፡ ያቀባበለው ሽጉጡን እንደያዘ ከመኪናው እንደወረደ ተዘናግተው ወደ ቆሙት እና ከፊት በቆመው ላይ ተኮሰ፡፡ ቀጥሎም አላቅማማም ሽጉጡን በሌላው ላይ ሲደግን ሁለቱም እጆቻቸውን ወደ ላይ አነሱ፡፡

መሳሪያቸውን ከገፈፈ ቦሀላ በቀጥታ በአቅራቢያው ወዳለ ፖሊስ ጣቢያ በመሄድ የግድያ ሙከራ ባደረጉበት ሰዎች ላይ ተኩሶ ህይወት ማጥፋቱን በመናገር መሳሪያዎቹን በማስረከብ እስረኛ ሆነ፡፡ ይህ ግዜ ከአቦማም አልፎ በቤተሰቡ ላይ ከባድ እንግልት የደረሰበት ነው፡፡ መላው ቤተሰብ ሳይቀር ለእስር ተዳረገ፡፡

ከአቦማ አባት ጋር ቅርብ ጓደኛ የነበረው በወቅቱ የደረግ አባሉ ኮሎኔል ተካ ቱሉ በግሉ ሊደርስበት በሚችለው አንዳች ሳይሰጋ እነ መንግስቱን ጭምር በማሳመን አቦማ የወሰደው እርምጃ ራስን የመከላከል፣እንዲሁም እነዛን ሰዎች መንግስት ያልላካቸውና በግለሰብ ጥላቻ ተመስርቶ የተፈጸመ ጥቃት እንደሆነ ታምኖበት በፍርድ ቤት የቀረበበት ክስ እንዲቋረጥ ተደርጎ በቅጣት መልክ አቦማ ወደ ወለጋ (አንገር dhedhessaa) ተቀይሮ እንዲሄድ ተደረገ፡፡
ይህ ወቅት አቦማ ከፍተኛ ስራ የሰራበትና ለዘመናት እንዲበታተን የተደረገው የኦሮሞ ህዝብ እንዲገናኝ መንገዱን የጠረገበት ነበር፡፡

የኦሮሞ ህዝብ የባህል ተቋምን በመመስረት ቀደም ብሎ በምስራቅ በኩል በሙዚቃው ስለ ኦሮሞነት ማቀንቀን የጀመረውን እና የነ አሊ ቢራነ የአፍረን ቀሎ ቡድን ወለጋ ድረስ በመውሰድ ማንነትን እንዲያጠነክሩ ሲሰራ በሌላ በኩል ከድርጅቱ የተሰጠው ተልእኮ የትጥቅ ትግሉ በምስራቅ ብቻ ሳይሆን በመላው ኦሮሚያ ጥንስስ የሰራዊት ሀይል ለማቋቋም በደርግ ሽፋን እንደፈለገው የመንቀሳቀስ እድሉ የነበረው አቦማ በመሆኑ ቀን ከሌት መስራቱን ተያያዘው
በነ መ/አ ይገዙ ዋቄ የሚመራውና በገነቲ Dheሬሳ ካድሬነት ሙክታር ሙሳ፣ አብዲ፣መሀመድ ለተባሉ የነጻነት ታጋዮች ድብቅ መታወቂያ በማዘጋጀት እና መሳሪያ በማስታጠቅ አምቦመግቢያ አዋሮ ላይ በአቶ አገርጋው ዲንቃ (የደርጉ ጠ/ሚ የነበሩት የተስፋዬ ዲንቃ ወንድም) ቤት ተሰባሰቡ፡፡
ይህ የአቦማ እንቅስቃሴ ያሰጋቸውና እርሱ ላይ ክትትል እያደረጉ የነበሩ አካላት አቦማ አምቦ ላይ መታየቱን ለደርግ ሪፖርት በተደረገ ማግስት አምቦ ላይ የሽምቅ ተዋጊ ሀይል ለመመስረት ገና በጅምር ላይ የነበረው ሀይል ሙሉ በሙሉ ተከብቦ ባልታሰበብት ሰአት በቁጥጥር ስር ዋለ፡፡

ይህ እርምጃ መላው በከተማ የነበረው የኦሮሞ ነጻነት ሀይል አመራሮች ወደ ጫካ እንዲያመሩ ያስገደደ ነበር፡፡ የባሌ ክ/ሀገር አስተዳዳሪ የነበረው ጃል መገርሳ በሪ፣ የአየር ሀይሉ ኮከብ ፓይለት ይገዙ በንቲን ጨምሮ መላው የከተማው ሀይል ወዲያ የነጻነት ትግሉ ወደተጀመረበት ሀረርጌ በማምራት ትጥቅ ትግሉን ተቀላቀሉ፡፡ አቦማ አባጢቂ በሰዎች ዘንድ የሚታወቀው አስደናቂ በሆነው ድፍረቱና ሰውን የማሳመን ተጽእኖ ፈጣሪነቱ ነው፡፡ በተደረገው የኦነግ መስራች ጉባኤ ላይ የድርጅቱ ዋና ጸሀፊ በመሆን እየሰራ ባለበት 10 የድርጅቱ መስራች እና መሪዎች ወደ ሶማሊያ ካመራው አቻ የሌላቸው የድርጅቱ እንቁ መሪዎች አንዱ ነበር፡፡ ለስምንት ቀን ያህል በኦጋዴን በረሀ የእግር ጉዞ ካደረጉ ቦሀላ ሺንጋ ከምትባል አከባቢ እንደደረሱ አንድ ያልጠበቁት ክስተት ተከሰተ፡፡በታጠቁ እና ለክርስትና ሀይማኖት ከፍተኛ ጥላቻ ካላቸው አክራሪ ሶማሊዎች እጅ ወደቁ፡፡

በአጋጣሚ 4ያህሉ የክርስትና እምነት ተከታዮች በመሆናቸው አክራሪዎቹ የክርስትና እምነት ያላቸውን ለብቻ በማውጣት ጣቶቻቸውን በመሳሪያቸው ምላጭ ላይ እንዳዋሉ...የተቀሩት አባላት ከክርስትያን ወንድሞቻቸው ፊት ለመቆም መመካከር አላስፈለጋቸውም፡፡ ቀጥለውም...."
እኛ ኦሮሞዎች ነን ከቤታችን ያወጣን ሮሮ እንጂ ሀይማኖት አይደለም፡፡ብትለቁን ባንድነት ልቀቁን አልያም ባንድነት ግደሉን፡፡" በማለት በአንድ የኦሮሙማ መንፈስ ቆሙ፡፡ ከተደገነባቸው አፈሙዝ ዘወር እንዲሉ ቢጠየቁም አቋማቸው እንደሆነ በመግለፅ የአንድ እናት ልጆች ለአንድ አላማ በአንድነት ከቤታቸው እንደወጡ በአንድ ጉድጓድ በፍቅር አሸለቡ፡፡

yoom as geenye salphaatti;
Of-kenneeti Jabaan Sirratti!
14.7K viewsGumaa Saaqataa, 15:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-15 18:17:37 ዛሬ Ebla 15 ነው። በመላው ኦሮሞ ልብ ውስጠ ስለ እኩልነት፣ ነጻነት እና ማንነት ሲሉ ትግል ጀምረው የህይወት መስዋእትነት የከፈሉ ጀግኖቻችንን እንድንዘክርባት በሰባዎቹ መጀመሪያ የተወሰነች እለት።

አባ ጢቂ (አቦማ ምትኩ)

ይህንን ጽሁፍ የከተብኩት ከሶስት አመት በፊት ሲሆን ለዚህ ጽሁፍ ግዜያቸውን ሰውተው ሙሉ በሙሉ ትብብር ያደረጉልኝ የአቦማ አክስት ልጅ የሆኑትና በእድሜ አቻው እንዲሁም በወቅቱ በምእራብ በኩል ሲንቀሳቀስ የነበረው የኦሮሞ ነጻነት ሀይል መካከል ከነበሩት፣በእስር ቤት አስር አመት ያህል ሰቆቃ የደረሰባቸው ዛሬ በአሜሪካ የሚገኙት Daniel Daffa እና የአቦማ ምትኩ የመጨረሻዋ እህቱ Giftii Wako ናቸው)

ከቀድሞው አለመያ እርሻ ኮሌጅ ከዛሬው ሀረመያ ዩኒቨርስቲ የመጀመሪያ ተመራቂ ተብለው ከሚጠቀሱት አንዱ ናቸው የአባ ጢቂ ወላጅ አባት አቦ ምትኩ ዋቆ፡፡ የተወለደው በወለጋ ጊምቢ ከእናቱ አዴ መርጌ ሚጀና እና ከአባቱ ምትኩ ዋቆ ሲሆን ለቤተሰቡም ሀንገፋው ልጅ ተወለደ

አቦማ የአንደኛ ደረጃ ትምህርቱን የተከታተለው በትውልድ መንደሩ በጊምቢ የተማረ ሲሆን፣መካከለኛ ሁለተኛ ደረጃን በፊንፍኔ፣ በወቅቱ የውጭ ተወላጆች እና የገቢ ምንጫቸው ከፍ ባለ ደረጃ ላይ ያሉ ሰዎች ልጆች በሚማሩበት American Community School" ተብሎ በሚባለው ትምህርት ቤት የተማረ ሲሆን አቦማ ስለ ሰው ልጅ ነጻነት ትግልም በግላጭ መታየት የጀመረው በዚያን ወቅት እንደሆነ ቅርብ ቤተሰቦቹ ይናገራሉ፡፡

ገና የመካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እያለ ከመካከላቸው አለአግባብ የተባረረን ተማሪ ወደ ትምህርቱ ለማስመለስ ትንሹ አቦማ በትምህርት ቤቱ ያሉ ተማሪዎችን ውስጥ ለውስጥ በመቀስቀስ የትምህርት ማቆም አድማ እስከ መጥራት የደረሰና ወደ ቦሀላም መሪ ተዋናይ መሆኑ ተደርሶበት ከትምህርት ቤቱ እስከ መባረር ደርሷል፡፡

ቀጥሎም ለትምህርት የተጓዘው የትምህርት ጥራቱ ጠንካራ ወደሆነው

"Akaki Adventist School" ሲሆን እስከ አስረኛ ያለውን ያጠናቀ ሲሆን አስራ አንድና አስራ ሁለትን በሀገሪቱ በደረጃ የሚወጡ ተማሪዎች ተመርጠው ወደሚገቡበት በቀደምት ስሙ "ተፈሪ መኮንን አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት" ካልተሳሳትኩ የዛሬው (Entoto Academic, Technical and Vocational School)ሲሆን የአቦማ ምትኩ ስለ ብሄር ብሄረሰቦች የነጻነት ጥያቄም በግልጽ መቀጣጠል የጀመረበት ሰአት ነው፡፡ በወቅቱ ያመራው እስከዛሬም በዩኒቨርሲቲው አነጋጋሪ ዉጤት ወዳመጣበት በቀድሞው አጠራር ስሙ "Haile Selassie University" ነው፡፡

አቦማ በተፈሪ መኮንን አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ የተማሪ ሊደር በነበረበት ሰአት ፋርማሲስት እየተማረ የነበረውና የአክስቱ ልጅ ግርማ ደፋ ጀሞ በዩኒቨርስቲው ውስጥ ጠንካራ የነጻነት ትግል አቀንቃኝ በመሆኑ የርሱን አርአያ የተከተለ ጭምር ይመስላል፡፡

1953 "ንጉስ አይወቀስ " የተባለውን ስርአት ባለመቀበል የበሰበሰውን የዘውድ ስርአት ወንድማማቾቹ ጀነራል መንግስቱ እና ገርመሜ ንዋይ መገርሰስ እንደሚቻል በተግባር አሳይተው በማለፋቸው በየ አቅጣጫው የነጻነትን ቀንዲል ለማብራት ተማሪው ንቅናቄውን አጠንክሮታል፡፡
አቦማ ምትኩ የሶስተኛ አመት ተማሪ በነበረበት ሰአት ከፍተኛ ግምት የሚሰጠው የዩኒቨርስቲው ሴክሬተሪ ጀነራል ውድድር ላይ ከቀረቡት ውስጥ
መለስ ዜናዊ
ገላሳ ዲልቦ
አቦማ ምትኩ
መለስ ተክሌ (የቀድሞው ጠ/ሚ ለገሰ ዜናዊ ስማቸውን የተዋሱት በተማሪዎች ንቅናቄ ወቅት ከፍተኛ ተወዳጅነት ከነበረው እና በመጨረሻም ከነ ጀነራል ታደሰ ብሩ ጋር በአንድነት ከተረሸነ የትግራይ ክልል ተወላጅ ተማሪ መሆኑ ይታወቃል)

በመጨረሻም ማጣራቱን አልፈው ለውድድር የቀረቡት የወቅቱ ለገሰ(መለስ ዜናዊ ) እና የምትኩ ዋቆ ልጅ አቦማ ነበር፡፡ በቅድሚያ የጥናት ጽሁፉን ያቀረበው አቦማ ምትኩ ሲሆን በአዳራሹ የተሰበሰበው ማህበረሰብ አፍዝ አደንዝዝ ያላቸውን እና ውስጠትን ሰርስረው ሚገቡት የአቦማ መልእክት እንደተመሰጠ ተራው የለገሰ (መለስ) ዜናዊ ተሰጠ፡፡ መለስ እዚህ ጋር ትልቅ የሆነ ብልጠትን ነበር የተጠቀመው፡፡ እርሱ ጭምር በአቦማ የጽሁፍ አቀራረብና በዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ የተሰጠውን ግምት ውጤት እንደማይቀለብስ በመረዳቱ ወደ መነጋገሪያው ቀረብ በማለት እንዲህ አለ

" ለአቦማ ምትኩ ካለኝ ክብር አንጻር ውድድሩን አቋርጫለሁ"
1966 አቦማ ምትኩ የሀይለ ስላሴ ዩኒቨርስቲ የተማሪዎች ፕሬዝዳንት ሲሆን ምክትሉ ጌታቸው በጋሻው(በአሁኑ ሰአት ፕሮፌሰር ሲሆኑ ኑሯቸውን ያደረጉት በቺካጎ ነው፡፡ ጌታቸው በወቅቱም የደርግ አባል ከነበሩትና በሚስጥር የኢህአፓ አመራር ከነበሩት መ/አ አለማየው ሀይሌ ጋር በኢህአፓ የታቀፈ ነበር)

አቦማ ምትኩ በዚህ ወቅት በቤታቸው ጭምር ከነ ባሮ ቱምሳ ጋር በኦሮሞ ህዝብ ጥያቄ ላይ መመካከር ከጀመረ ሰንበትበት አድርጓል፡፡ ወቅቱ ደርግ የንጉሱን ስርአት በአዝጋሚ መፈንቅለ መንግስት አሰወግዶ ራሱን ለማደላደል በሚሯሯጥበት ሰአት በድርጅት መልክ ስለ ህዝቦች ነጻነት የሚያነሳበትና ህዝቡን የማንቀሳቀስ አቅም ያለው የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ብቻ ነበር(እነ ኢህአፓ ጭምር በግልጽ አልወጡም) የዩኒቨርስቲው የተማሪ መማክርት ለደርግ ፈተና ሆኑበት፡፡

አይደፈሩም የተባሉትን ንጉሰ ነገስት ከቤተመንገስት ለማውጣት ከተላከው ቡድን ውስጥ ወታደሩ በፍርሀት ቆፈን ሲያቀረቅር ደፈር በማለት የደርጉን ውሳኔ በንባብ ለንጉሱ ያሰማው (በወቅቱ የፖሊስ ሰራዊት ሻለቃ ማእረግ የነበረው ደበላ dhiንሳ) ደርግ አቦማ ምትኩን እንዲለሳለስ ለማድረግ እና ከደርግ ጋር እንዲሰራ ምሽት ላይ በአቦማ ቤተሰቦች ቤት በመምጣት ብዙ ጣረ፡፡ የአቦማ አሳማኝ ክርክሮች ግን ደበላን እስከማሳመን ነበር የደረሱት፡፡

ደርግ በዩኒቨርሲቲ ተማሪው ላይ እርምጃ መውሰድ ጀመረ፡፡ በዚህ ሰአት እነ ኤለሞ ቂልጡ ጭምር ወደ ፊንፍኔ ተጠርተው በድብቅ የኦሮሞ ነጻነት ግንባርን መሰረቱ፡፡
ፊንፍኔ ላይ የተመሰረተው የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) የመጀመሪያዋን ግዳጅ ለአቦማ ሰጠው። በእርግጥ ለአቦማ ከባድ ሚሸን ነበር። የደርግ አባላት እየተመላለሱ አባላቸው እንዲሆን ከጠየቁት እና በወቅቱ መንግስቱ ሀይለማርያም ከመሰረተው "ሰደድ" የተባለውን ድርጅት ሽፋን ለማድረግ እንዲቀላቀል ነበር የታዘዘው፡፡ አቦማ አላመነታም፡፡በመጨረሻ አቦማ ሰደድን ሽፋን በማድረግ እንደፈለገው መንቀሳቀስ ጀመረ፡፡

ለኦሮሞ ነጻነት ግንባር ጥንስስ ሰራዊት መሳሪያ መሰብሰብ ትልቁ ተልእኮው ነበር፡፡ ይህን እያሳካ ባለበት ሰአት ግን በአንድ የኦሮሞ ጥላቻ እንደዛሬዎቹ ከሚያንዘርዝራቸው አንድ የሻለቃ ማእረግ ያለው ሰው በእነ አቦማ ቤት በድብቅ ለኦሮሞ ነጻነት ግንባር እንደሚሰራ ይጠረጥረውና ሶስት ሰዎች እርምጃ እንዲወስዱበት ትእዛዝ ወረደ፡፡ አቦማ ምትኩ ንፋስ ስልክ አከባቢ እየነዳ በነበረበት ሰአት በመኪና ተከተሉት ፍጥነቱን ጨምሮ ለማምለጥ ሞከረ። በስድስት ኪሎ አድርጎ ግብጽ ኤምባሲ አከባቢ ካለችው ኮፊ ሀውስ ፊት ለፊት ወደምትገኘው የቤተሰቦቹ ቤት ሲደርስ ሶስት ክላሽንኮፍ የታጠቁ በአቋራጭ ቀድመውት መግቢያውን ዘግተው ቆመዋል፡፡
13.2K viewsGumaa Saaqataa, 15:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-15 18:17:24
አቦማ ምትኩ
13.0K viewsGumaa Saaqataa, 15:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ