Get Mystery Box with random crypto!

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiopian_orthodox — የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiopian_orthodox — የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች
የሰርጥ አድራሻ: @ethiopian_orthodox
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 30.48K
የሰርጥ መግለጫ

በዚህ Channel ውስጥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን ዶግማ ፤ ቀኖና እና ትውፊት የጠበቁ ትምህርቶች ይተላለፉበታል፡፡
ለአስተያየት: ጥቆማና ጥያቄ በዚህ ያግኙን ☞ @Ethiopian_Orthodox_bot
Buy ads: https://telega.io/c/Ethiopian_Orthodox

Ratings & Reviews

1.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 34

2022-10-21 15:03:18 እንላለን፡፡ በመሆኑም የመምህራኑ እና የደቀመዛሙርቱ ችግር ዘርፈ ብዙ ከመሆኑ አንጻር ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት ከአሁኑ የተሻለ ትኩረት እንዲደረግ ት/ትን፣ ስብከተ ወንጌልን ያካተተ የአብነት መምህራን ከበዙበት አካባቢ መምህራን ወደሌሉበት አካባቢ አህጉረ ስብከት ከእነበጀታቸው እየተዛወሩ እንዲያስተምሩ ተማሪዎቹም ባሉበት አካባቢ ቋንቋ እንዲማሩ በሚያስችል መልኩ የመማር ማስተማሩ ሥርአት እንዲቀጥል ጉባኤው አደራ ጭምር አሳስቧል፡፡
7. ለስብከተ ወንጌል ተልእኮ ስኬታማነት ተናቦና ተግባብቶ መሥራት ሰባኪውና ተሰባኪው በቋንቋ በአመለካከት በአስተሳሰብ እንዲግባቡ ጥረት ማድረግ ብሔር ብሔረሰቦች በየልሳናቸው እንዲማሩ በዚህም ቃለ እግዚአብሔር ለሁሉም እንዲዳረስ የቤተ ክርስቲያናችን ዋነኛ ተልእኮ መሆኑ ይታወቃል፡፡ የአዳዲስ አማንያን ወደ ቤተ ክርስቲያን መምጣት በተለይም አንድ የፕሮቴስታንት አማኝ ከእነ ተቋሙ ወደ ቤተ ክርስቲያን መምጣት በሌሎችም አህጉረ ስብከቶች ከሌሎች የእምነት ተቋማት እየተመለሱ የተፈጸመው ጥምቀተ ክርስትና ከቤተ ክርስቲያናችን የሚጠበቅ የአገልግሎት ውጤት በመሆኑ ጉባኤው በአክብሮት ተቀብሎታል፡፡
በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ተደብቀው መዋቅሯን በመጠቀም የራሳቸውን የግል ፍላጎት ለማርካት የሚጥሩ ቢጽ ሃሳውያን አጥማቂ ነን፣ የዓለም ብርሃን ነን በሚሉ እና በልዩ ልዩ ስያሜ በየአህጉረ ስብከቱ ባሉ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናትን አዳራሾች ምእመኑን ግራ በሚያጋቡ ላይ ቅዱስ ሲኖዶስ በጥናት ላይ የተመሠረተ ውሳኔ እንዲሰጥ እናሳስባለን፡፡

ስብከተ ወንጌል የመንግስተ እግዚአብሔር ቅዱስ አዋጅ እና ለሰው ልጅ የዘለዓለም ድህነት የተሰጠ ኪዳነ ሰላም ስለሆነ በመምሪያው በኩል ስምሪት በማዘጋጀት በተለያዩ አህጉረ ስብከት በሚከበሩ ክብረ በዓላትና አጿማት ሰባኪያነ ወንጌል እየተገኙ ትምህርተ ወንጌል ለምእመናን እንዲያስተምሩ በትኩረት እንዲሠራ ጉባኤው አስገንዝቧል፡፡

በመንበረ ፓትርያርኩ የሚታተሙ ጋዜጦችና መጽሔቶች ውስን መሆናቸው የሚታወቅ ነው፡፡ እነዚህ ጋዜጦችና መጽሔቶች ስርጭታቸው ችግር እንዳለበት ይታወቃል፡፡ የቤተ ክርስቲያናችን ጠቅላላ ተልእኮ ይሳካ ዘንድ ጋዜጦችና መጽሔቶች ያላቸው አስተዋጽዖ ከፍተኛ ነው፡፡ ስለዚህ የቤተ ክርስቲያናችን ጋዜጦችና መጽሔቶች በሰው ኃይል በሊቃውንትም ተጠናክረው በብዛትና በጥራት እንዲታተሙ አቅም ያላቸው የአህጉረ ስብከት ጽ/ቤት እና የአብያተ ክርስቲያናት የሊቃውንት ተሳትፎ ያልተለያቸው ትምህርታዊ ጽሑፎችን እያሳተሙ እንዲያሰራጩ ጉባኤው አበክሮ ይጠይቃል፡፡
8. የሰ/ት/ቤት ተማሪዎች ቤተ ክርስቲያኒቱ በአሁኑ ወቅት የምታስተምራቸውን ት/ት ተምረው ቤተ ክርስቲያኒቱን ማገልገላቸው በታላላቆች አበይት የዓውደ ምህረት ክብረ በዓላት በየጊዜው የሚያሳዩት ሃይማኖታዊና አስተማሪ የሆነው የአሰላለፍ ስርዓት ከዓመት ዓመት እየደመቀ አስተማሪነቱ እየጨመረ መምጣቱ ዓለም በምልዓት እያደነቀው ያለ መንፈሳዊ ተግባር ሆኗል፡፡ በመሆኑም ይህ ውጤታማ እየሆነ የመጣውን ሂደት ለወደፊትም ለማስቀጠል እንዲቻል የሰ/ት/ቤት ማደራጃ መምሪያው በየደረጃው ዘርፉን በሰው ኃይል እና በማቴሪያል በማጠናከር ከሁሉም ቅድሚያ የሚሰጠው የቤተ ክርስቲያኒቱን ተረካቢና ተተኪ ትውልድ ማፍራት ወቅታዊ ጉዳይ ስለሆነ በሁሉም አቅጣጫ ትኩረት እንዲሰጠው ጉባኤው አጥብቆ ያሳስባል፡፡
በሰ/ት/ቤት ማደራጃ መምሪያ ስር ያለው ማኅበረ ቅዱሳን በርካታ መንፈሳዊ እና ሐዋርያዊ፣ ማኅበራዊ፣ ልማታዊ ሥራዎችን እያበረከተ እንደሚገኝ በየአህጉረ ስብከት ጽ/ቤቶቹ ሪፖርት በስፋት ተገልጿል፡፡ ስለዚህም ማኅበሩ የዘረጋቸውን የአገልግሎትና የልማት አውታሮች ካለፈው የበለጠ አጠናክሮ እንዲቀጥል ጉባኤው አሳስቧል፡፡
9. ለመጀመሪያ ጊዜ በከፍተኛ ጥንቃቄ በሊቃውንት ጉባኤ ሲዘጋጅ የቆየው የግዕዝ መጽሐፍ ቅዱስ በበጀት ዓመቱ ለሕትመት በቅቶ በቅዱስነታቸው መመረቁ እና መጽሐፉ በሥራ ላይ እንዲውል መደረጉ ጉባኤው በአድናቆት ተቀብሎታል፡፡ በቀጣይም የቤተ ክርስቲያናችን ሊቃውንት ጉባኤ ጥንታውያን የቤተ ክርስቲያን መጽሐፍቶች ጥንታዊነታቸውን ሳይለቁ ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት በስፋት ተዘጋጅተው እንዲደርሱ የማድረጉ ጥረቱን እንዲቀጥልበት በሚፈለገውም ሁሉ እገዛ እንዳይለየው ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን ጉባኤው ይጠይቃል፡፡ በቀጣይም መጽሐፍ ቅዱስን በኦሮምኛ እና በሌሎችም ቋንቋዎች መደበኛውንና ስርወ ቃል ትርጉም ባለቀቀ መልኩ እንዲታተም እና ለምእመናን እንዲሰራጭ ጉባኤው ይጠይቃል፡፡
10. ሀገራችን ኢትዮጵያ በዘመናት ውስጥ በዓለም የምትታወቅበት የነበረ ሃብቷ ሰላም አንድነት እና አብሮነት ሆኖ ሕዝቧን በፈርሃ እግዚአብሔር በበጎ ስነ ምግባር የሚታወቅ፤ የአየር ንብረቷ ለዜጎቿ ቀርቶ በውጭው ዓለም የሚገኙ የሚናፍቁት የሰው ልጆች መኖሪያና ምድረ ገነት መሆኗ ዓለም የተገነዘበው ሃቅ ነው፡፡ በእነዚህ በርካታ ዘመናትም በሀገሪቱ ውስጥ በመሪና በተመሪ በአጠቃላይ በዜጎች መካከል የነበረው የመከባበር እርስ በእርስ የመግባባትና የመፈቃቀር ሁኔታ አልፎ አልፎ እንቅፋት ቢያጋጥመውም የቀደሙ አባቶቻችን የነበራቸው የችግር አፈታትና ወደ አንድነት ለመመለስ ያደርጉት የነበረ ጥረትና ተቀባይነቱ በእጅጉ የሚያስመሰግን እንደነበረ የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነው፡፡ ስለዚህ የሀገራችን ዜጎች ሁሉ ለዚች እናት ሀገራችን ሲሉ ትላንት የነበረውን የመመካከርና የአንድነት ባህላቸውን አጥብቀው በመያዝ ለነገ ትልቅ ተስፋ ያላት ሀገራችን እንደምኞታችንና ሃሳባችን ካሰብነው ደርሳ ልማቷ አድጎ፣ አንድነቷ ተጠብቆ፣ ሕጻናት በሰላም የሚያድጉባት፣ ሽማግሌዎች የሚጦሩባት፣ የሁሉ ተስፋ የሆነች ሃገር እንድትኖረን ለማድረግ ጉባኤው ጥሪ እያቀረበ ሁላችንም ለሰላሙ መገኘት የዜግነት ድርሻችንን እንወጣለን፡፡ ከዚሁ ጋር በሀገራችን ያለው ጦርነት በሰላም እንዲፈታ ቤተ ክርስቲያን አዘውትራ የምትጸልይ ሲሆን መንግስት በየአቅጣጫው የጀመረውን የሰላም ሂደት ጉባኤው እያደነቀ በዚሁ እንዲቀጥልበትና እልባት ላይ እንዲደርስ ጉባኤው ጥሪውን ያቀርባል፡፡
ሰው ሁሉ በዚህ ዓለም ሲኖር ሠራተኛው ሠርቶ ለመበልጸግ፣ ነጋዴው ነግዶ ለማትረፍ፣ በሽተኛው ድኖ በጤና ለመኖር፣ ተማሪው ተምሮ ለማወቅ፣ በአጠቃላይ ዜጎች ማልደው ለመውጣትም ሆነ አምሽተው ለመግባት በምድራችን ሰላም ሲገኝ እርስ በእርስ መተማመን ሲኖር በመሆኑ ዜጎቻችን ለሰላምና ለአንድነት ተባብሮና ተከባብሮ ለመኖር እንዲችሉ የበኩላችንን ሁሉ እናደርጋለን፡፡
11. የሰላም እጦት በነበረባቸውና በጦርነቱ በተጎዱ የሀገራችን ክፍሎች ሕይወታቸውን ስላጡት ወገኖቻችን ጉባኤው ሐዘኑን እየገለጸ በመንግሥት በኩል የመልሶ ማቋቋም ሥራ ለማከናወን በተያዘው እቅድ መሠረት የመከራውና የችግሩ ገፈት ቀማሽ ቤተ ክርስቲያናችን እንደመሆኗ መጠን በጦርነቱ የወደሙ አብያተ ክርስቲያናት እንዲታነጹ፣ የተዘረፉ ንብረቶች እንዲተኩ፣ የፈረሱ መዋቅሮች መልሰው እንዲደራጁ፣ በሚመለከታቸው አካላትም እንዲታሰብበት ጉባኤው ያስገነዝባል፡፡
2.5K viewsedited  12:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-21 15:03:18 በሐሰተኛ አጥማቂያን ላይ ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ እንዲያስተላልፍ ተጠየቀ፡፡

በ41ኛው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ የውሳኔ ሃሳብ እና የአቋም መግለጫ በዛሬው ዕለት ጥቅምት 11 ቀን 2015 ዓ.ም ባስተላለፈበት ወቅት በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ተደብቀው መዋቅሯን በመጠቀም የራሳቸውን የግል ፍላጎት ለማርካት የሚጥሩ ቢጽ ሃሳውያን አጥማቂ ነን፣ የዓለም ብርሃን ነን በሚሉ እና በልዩ ልዩ ስያሜ በየአህጉረ ስብከቱ ባሉ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናትን አዳራሾች ምእመኑን ግራ በሚያጋቡ ላይ ቅዱስ ሲኖዶስ በጥናት ላይ የተመሠረተ ውሳኔ እንዲሰጥ ተጠየቀ፡፡

አጠቃላይ የጉባኤው የውሳኔ ሃሳብ እና የአቋም መግለጫ እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡

ጥንታዊት ታሪካዊት የሆነችው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የቤተ ክርስቲያናችንን ሁለንተናዊ ችግሮች ለመፍታት እና በተለይም መሠረታዊ ተልእኮ የሆነውን ስብከተ ወንጌልን በተገቢው መንገድ በማስፋፋት፣ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ በምእመናኖቻችን መካከል ግንዛቤ አግኝተው ይበልጥ እንዲደራጅ፣ የሰ/ት/ቤት ወጣቶች በሃይማኖትና በምግባር ተኮትኩተው እንዲያድጉና የነገዪቱ ቤተ ክርስቲያን ተረካቢ እንዲሆኑ፣ በልማቱም አቅጣጫ ለህብረተሰቡ ሁሉ ግንባር ቀደም ምሳሌ ሆና የልማት ውጤት ለማሳየት የቤተ ክርስቲያን የገቢ ምንጭ ከመፍጠር ጋር ገቢዋ ወቅታዊና ዘመናዊ በሆነ የአመዘጋገብ ስልት ለመጠበቅ፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ ት/ቤቶች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ፣ ከማዕከል እስከ አጥቢያ ያለው የቤተ ክርስቲያን ግንኙነት ካለፈው ጊዜ ይልቅ ወደፊት የተሻለ እንዲሆን፣ በተለይም ማንኛውም መንፈሳዊም ሆነ ዘመናዊ እንቅሳቃሴ ከግቡ ለማድረስ ለዚህም በቤተ ክርስቲያናችን ያለው የመልካም አስተዳደር ሥራ እንዲፋጠን ለማድረግ በዚህ 41ኛ የሰበካ መንፈሳዊ ዓለም አቀፍ አጠቃላይ ጉባኤ በተሰጡ ትምህርቶች እና በተደረጉ ውይይት ግንዛቤ ተወስዷል፡፡ በመሆኑም
1. ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በውጭ ሀገር እና በተለይም በሀገር ውስጥ ያከናወኑት መንፈሳዊ፣ ሐዋርያዊ እና ማኅበራዊ ተልእኮ ይልቁንም በሀገር ላይ የደረሰውን የሰላም እጦት፣ የኑሮ ውድነት፣ የወረርሽኝ በሽታን አስመልክቶ ያለመታከት ሀገርና ሕዝብን ለማረጋጋት ያከናወኑት የሰላም ተልእኮ ቤተ ክርስቲያናችን ክብሯ ሰላሟ እና አንድነቷ እንደተጠበቀ እንዲኖር በማረጋገጥ አባታዊ አመራር ያከናወኑበት በጀት ዓመት በመሆኑ የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንን ልዕልና ብቻ ሳይሆን የሀገራችን ኢትዮጵያንም ክብርና ሀገረ እግዚአብሔርነትን ያንጸባረቀ በመሆኑ ጉባኤው በታላቅ አድናቆት በሙሉ ልብ ተቀብሎታል፡፡
2. የቤተ ክርስቲያናችን 4ኛው ፓትርያርክ የነበሩት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ የሽኝት እና የቀብር ስነ ሥርዓት በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ መሠረት የተከናወነ ሲሆን በሥርዓቱ ላይ ክብርት የኢፌዴሪ ፕሬዘደንት ሣህለ ወርቅዘውዴ የአበባ ጉንጉን ማኖራቸው፣ ክቡር የኤፌዴሪ ጠ/ሚኒስትር ዓብይ አህመድ(ዶ/ር) በሰጡት ጥብቅ አመራር የቅዱስነታቸውን የሽኝት ፕሮግራም በደመቀ ሥነ ስርዓት ከመካሄዱም ሌላ የፌደራሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች መገኘታቸው ለተካሄደው የሽኝት ሥነ ስርዓት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ክብርት ወ/ሮ አዳነች አበቤ ለሰጡት አመራር በአጠቃላይ ከተማ አስተዳደሩ ላደረገው አጠቃላይ ድጋፍ ከቤተ ክርስቲያናችን ምሥጋና ማግኘቱን በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ ሪፖርት ተካቶ የቀረበውን ጉባኤው በምልዓት በአድናቆት ተቀብሎታል፡፡
3. ቤተ ክርስቲያን የሚፈለግባትንና ጊዜው የሚጠይቀውን ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና መንፈሳዊ ተልእኮ እንድትወጣ ለማስቻል የሚያዝ ጠንካራ የአስተዳደር ሥርዓት መዘርጋት እንዳለባት ወቅቱ የሚጠይቀው ነው፡፡ በመሆኑም እስካሁን የተገለጸው የመሻሻል ጅምር በመሆኑ ጉባኤው ተገንዝቧል፡፡ ቢሆንም እያንዳንዱ መምሪያና ተቋም የበላይ አካል ክትትል ሳይለየው ራሱን ችሎ ኃላፊነቱን በተጠያቂነት ሲወጣ ባለመታየቱ መልካም አስተዳደርን በማስፈን ጭምር የተቀላጠፈ ፍትሕና ርት የተመላ አስተዳደር ይታይ ዘንድ ማንኛውም መንፈሳዊም ሆነ ዘመናዊውን እንቅስቃሴ ከግቡ ለማድረስ መልካም አስተዳደር ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ በመሆኑ የሥራ ቦታዎችን በመልካም አስተዳደር እና አቅም ግንባታ የተደራጁ እንዲሆኑ፤ ሥራ እና ሠራተኛን በማገናኘት እንዲሠራ በመጠየቅ ጉባኤው በጎ ሐሳቡን ለግሷል፡፡ በመሆኑም የሥራ ተነሳሽነት ያለው ከተገልጋይነት ይልቅ አገልጋይነትን እንዲሁም ግልጽነትን ተጠያቂነትንና ታማኝነትን መርህ ያደረገ መልካም አስተዳደር እንዲጠናከር ተግተን እንሠራለን፡፡
4. የሰበካ ጉባኤ መጠናከር የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ህልውና ዋስትና ከመሆኑም በላይ በሮቿ ተከፍተው አምላክ አደራዋን ሕዝባዊ አገልግሎቷን ለመፈጸም የቻለችበት ህያው ተቋማችን መሆኑን ከልባችን ስለምናምን የማደራጃ መምሪያው ክትትልና ግምገማ ሳይለየን ከብፁዓን አባቶች ቡራኬና አመራር እየተቀበልን ከፍተኛ የሥራ ውጤት ለማስገኘት እያንዳንዷ የአጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ህልውናዋ እና መብቷ ተጠብቆ አስተዋጽዖውን በማሳደግ ግዴታዋን መወጣት ትችል ዘንድ በስብከተ ወንጌል መንፈሳዊ መሳሪያነት ከፍተኛ የመመካከር እና የማሳመን ተልእኳችንን ለመወጣት ቃል ገብተናል፡፡
5. ብፁዕ ወቅዱስ አባታችን በጉባኤው መክፈቻ ባሰሙት ቃለ ምዕዳን የሰበካ ጉባኤ አመሠራረት እና ጉዞ አሁን ያለበት ደረጃ ትክክል ነው ወይስ የሚቀረው አለ? የቀረው ካለስ ለምን አናስተካክለውም? ለወደፊትስ የሰበካ ጉባኤ ሀብተ በረከት እንደሚፈለገው በፍጥነት አድጎ ለሕዝቡ ተደራሽ እስከሚሆን ለምን አናደርሰውም? በሚል ትክክለኛና ሙያዊ ጥናት ተካሂዶ የማሻሻል ሥራ እንዲሠራ ያስገነዘቡትን ጉባኤው በምልዓት ተቀብሎ በሥራ እንዲተረጎም እያሳሰበ ለተግባራዊነቱም የየድርሻችንን ለመወጣት ቃል እንገባለን፡፡
6. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕልውናዋ ከታወቀበት ዘመን ጀምሮ እስከዛሬ ድረስ በትምህርት በኩል ለኢትዮጵያ ሕዝብ ያደረገችው አስተዋጽዖ ከፍተኛ ነው፡፡ የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊ፣ ሐዋርያዊና ማኅበራዊ አገልግሎት በሙሉ ሊፈጸም የሚችለው ከአብነት ት/ቤት ከሚገኝ የእውቀት በረከት ነው፡፡ የአብነት ት/ቤቶች በብዛት የሚገኙት በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በመሆኑና ለእነዚህም በቂ በጀት አለመመደቡና ይልቁንም በአብዛኛው አህገረ ስብከት ት/ቤቶች አለመኖራቸው ት/ቤቱ ባለበትም ቢሆን ትምህርቱ ወቅታዊና ዘመናዊ በሆነ መልኩ ካለመካሄዱም በላይ ለስብከተ ወንጌል ት/ት ትኩረት አለመሠጠቱ በጉባኤው ተወስቷል፡፡ በመሆኑም የአብነት ት/ቤቶቻችን ከዕውቀት እንዳይነጥፉ፤ መናብርተ ጥበብ የሆኑ ዐይናሞችም መምህራን ማስፈለጋቸው አያጠራጥርም፡፡ ሆኖም ለመምህራኑ በአሁን ጊዜ በቅዱስ ሲኖዶስ ታስቦበት እየተደረገላቸው ያለው ድጋፍ የሚያበረታታ መሆኑን ተገንዝበናል፡፡ ይሁን እንጂ የቤተ ክርስቲያኒቱን የአብነት ት/ቤቶች የሚያስተምሩ መምህራን የመጽሐፍት ኪራይ ክፈሉ፣ የምግብና የልብስ ዋጋ ስጡ ሳይሉ አደራቸውን እየተወጡ የሚገኙ ናቸው፡፡ ምንጊዜም ቢሆን መምህራኑ የሚሰጡት አገልግሎት በጥልቅ ሲገመገም በመንግስተ ሰማያት ካልሆነ በስተቀር በዚህ ዓለም ላይ ዋጋው ይህን ያህል ነው ብሎ መገመት ያዳግታል፤ ምሥጋናውም ቢሆን ሲያንሳቸው ነው፤ ከምሥጋናም በላይ ሌላ ቃል ካለ ለእነሱ ይገባል
2.9K viewsedited  12:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-16 10:46:12 የስደት ዘመንሽ

መከራን ታግሰሽ ገሊላ የገባሽ ፣
ለዓለም መፅናኛ ነው የስደት ዘመንሽ።

በጠላት ፈተና ከሀገር ተሰደሽ፣
ስትንከራተቺ አምላክን ታቅፈሽ፣
ከገሊላ አንስቶ እስከ ግብፅ በረሃ፣
የሚያዝንልሽ አጣሽ የሚሰጥሽ ዉኃ።
            አዝ
ሰሎሜ ትመስክር ያየሽውን ጭንቀት፣
ዮሴፍም ይናገር የሀዘንሽን ብዛት፣
እመቤቴ ማርያም ከአንድ ልጅሽ ጋራ፣
 በግብፅ በረሃ ያየሽዉ መከራ።
            አዝ
  ውርጭና ፀሓዩ ሲፈራረቅብሽ፣
  ረሀብና ጥሙ እንዲያ ሲያንገላታሽ፣     
  በለጋነት ዕድሜ በሄሮድስ ቅናት፣
  ከልጅሽ ጋር አየሽ መከራ ስደት።
            አዝ
   ልጅሽ አንዲምረን ስለእኛ እንዲራራ፣
   ለበረከት ሆነ ያየሽው መከራ፣  
   መልካም ፍሬ አፈራ ያነባሽው ዕንባ፣
   ምክንያት ለእኛ ሆነ ገነት እንድንገባ።
   
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
4.8K views07:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-15 09:20:44 "የአምላክ አቃቤ ሕግ"

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
4.1K views06:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-14 22:54:24
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
4.5K viewsedited  19:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-14 22:54:24 ጥቅምት ፭

የታላቁ አባት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ (ገብረ ሕይወት) የዕረፍታቸው መታሰቢያ

ጻድቁ የተወለዱት ግብፅ (ንሒሳ አካባቢ) ሲሆን አባታቸው ስምዖን እናታቸው አቅሌስያ ይባላሉ:: አባታችን ገብረ ሕይወት የጻድቃን አለቃ የቅዱሳን የበላይ ተጋድሏቸውና ድንቅ ተአምራቸው እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛ ቅዱስ ሰው ናቸው። የጻድቁን ክብር መናገር የሚችል ምን አንደበት ይኖራል? እንደ ምንስ ባለ ብራና ይጻፋል? ዜናቸውንስ ለመስማት የታደለ እንደ ምን ዓይነት ሰው ይሆን?

አባታችን ገብረ መንፈስ ቅዱስ ለ፭፻፷፪(562) ዓመታት በዚህች ዓለም ሲኖሩ እህል ያልቀመሱ /ምግባቸው ምስጋና ነውና/ ልብስ ያልለበሱ /ጠጉር አካላቸውን ይሸፍን ነበርና/ ሐዋርያዊ ሆነው ከግብፅ እስከ ኢትዮዽያ ብዙ ነፍሳትን ያዳኑ አባት፤ ሃገራችንን አስምረው አስራት እንድትሆናቸውም ተቀብለው ምድረ ከብድ አካባቢ አርፈዋል።

ጻድቁ ገብረ መንፈስ ቅዱስም ገብረ ሕይወትም ይባላሉ። በ፭፻፷፪ ዓመታት ሕይወታቸው እንደ ሐዋርያት ከምድረ ግብፅ እስከ ኢትዮጵያ ወንጌልን ሰብከዋል። በዚህም በሚሊዮን (አእላፍ) ለሚቆጠሩ ነፍሳት የድኅነት ምክንያት ሆነዋል።

ጻድቁ እንደ ሰማዕታትም ከከሃዲ ሰዎች ብዙ መከራን ተቀብለዋል። እንደ ባሕታውያን ለብዙ መቶ ዓመታት ሰው ሳያዩ ቆይተዋል። ለ'የ'ት የሚለው ግን የጽድቅ ሕይወታቸው ነው፤ ከዕልፍ አዕላፍ አጋንንት ጋር ተዋግተው ድል ማድረግ ችለዋልና።

የንሒሳው ኮከብ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ለኢትዮጵያ ልዩ ፍቀር አላቸው። ስለ ሃገሪቱና ሕዝቧ ፍቅር ሲሉ ለ፻(100) ዓመታት በደብረ ዝቋላ መከራን ተቀብለዋል። ምሕረትን ሲለምኑ ሥጋቸው አልቆ በአጥንታቸው ቁመው ነበርና ሃገራችን አሥራት ሆና ተሰጠቻቸው።

ስለዚህም ነው በሃገሪቱ ውስጥ ከ፳፻(2,000) በላይ የጻድቁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳማትና አድባራት ዛሬም ድረስ ያሉት። በ፰(8)ኛው ክ.ዘ አካባቢ የተወለዱት አባታችን ያረፉት በ፲፬(14)ኛው መቶ ክ.ዘ አካባቢ ነው። ፍጥረታትን ሁሉ አዝዘው መጋቢት ፭(5) ቀን ሲያርፉ ግሩማን መላእክት ገንዘው አካላቸውን ሠውረዋል።

ሥላሴን የተሸከመ አካላቸው በጐልጐታ ተቀብሯል የሚሉም አሉ። "ሰላም ለመቃብሪከ ዘኢተከሥተ ለባዕድ: ከመ መቃብሩ ለሙሴ ወልደ ዮካብድ: ዜና መቃብሪከሰ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ጸማድ: ቦ ዘይቤ በኢየሩሳሌም አጸድ: ወቦ ዘይቤ ኀለወ በከብድ።" እንዲል።

ጻድቁ አባታችን አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ እረፍቱ መጋቢት ፭(5) ቀን ነው ይህ ደግሞ በታላቁ ዓብይ ጾም ወቅት ነው። ፍትሃ ነገስት አንቀጽ ፲፭(15) ላይ በዓብይ ጾም በዓል ማክበር ይከለክላል የሀዘን ወቅት ነውና ከበሮ አይመታም እልልታና ጭብጨባ የለም ፍጹም ሀዘን እንጂ :የመጋቢት ፳፯(27) ስቅለት ጥቅምት ፳፯ ቀን እንደሚከበረው ሁሉ የአባታችን አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ እረፍታቸው ወደ ጥቅምት ፭ ቀን ተዛውሮ እንዲከበር ተደረገ፡፡

የጻድቁ አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ረድኤት በረከታቸው በእኛ በምናምን ላይ ይደርብን!

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
4.9K views19:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-13 07:12:06
ብሂለ አበው ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

https://t.me/abew_z_orthodox
https://t.me/abew_z_orthodox
444 views04:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-08 21:44:13 "በዙሪያችን ካሉ ድንቅ ምስክሮች" | ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
470 views18:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-08 21:40:41
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
512 views18:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-08 21:40:27 መስከረም ፳፱
ሰማዕት ቅድስት አርሴማ

የቅድስት አርሴማ አባቷ ቴዎድሮስ ከሌዋውያንና ከኃያላን ነገሥታት ወገን ሲሆን እናቷ አትኖስያ ደግሞ ከጳጳሳት አለቆች ወገን ናት፡፡ ወላጆቿ በሃይማኖት በምግባር ያጌጡ በበጎ ትሩፋት የተመሰገኑ ደጋግ ቅዱሳን ናቸው፡፡ በጾም፣ በጾሎት፣ በምጽዋትና ዓሥራት በኩራትን በማውጣት በመንፈሳዊ ሥራ ሁሉ እየተጉ ቢኖሩም ነገር ግን እስክ እርጅናቸው ዘመን ድረስ ልጅ ስላልነበራቸው ያዝኑ ነበር፡፡ እናቷ ቅድስት አትኖስያ እንደ ነቢዩ ሳሙኤል እናት ሐና ጠዋት ማታ ወደ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ በእግዚአብሔር ፊት ታለቅስ ነበር፡፡ እግዚአብሔር የልቧን ፈቃድ ይፈጽምላት ዘንድ ወደደና የቂሣርያውን ሊቀ ጳጳሳት ልድዮስን ስለ እርሷ ይጸልይላት ዘንድ አዘዘው፡፡
ሊቀ ጳጳሳቱም ስለ ቅድስት አትኖስያ ጸለየላት፡፡ እግዚአብሔር አምላክም የሊቀ ጳጳሳቱንና የቅድስት አትኖስያን ጸሎት ሰምቶ መልኳ እጅግ ያማረችን ሴት ልጅ ቅድስት አርሴማን ሰጣት፡፡ እናቷም እየተንከባከበች አሳድጋት ዕድሜዋ ከፍ ሲል አምላክን በወለደች በእመቤታችን ስም ወደተሠራች ቤተ ክርስቲያን ታገለግል ዘንድ ሰጠቻት፡፡ ቅድስት አርሴማ ወጣት በሆነች ጊዜ ወላጆቿ ባል ያጋቧት ዘንድ ወደዱ ነገር እርሷ ይህንን ፈጽሞ አልወደደችምና ወላጆቿን ‹‹እኔ የሰማያዊው የክርስቶስ ሙሽራ ነኝ እንጂ ምድራዊ ሙሽራ አይደለሁም›› አለቻቸው፡፡
ቅድስት አርሴማ ከእርሷ በፊትም ሆነ ከእርሷ በኋላ በመልክና በውበት የሚመስላት የለም፡፡ ይህን ዓለም እንደትቢያ በመቁጠርና ፍጹም በመናቅ ጌታችንን ከተከተሉት ቅዱሳት ደናግል አንስት ውስጥ በመልክና በውበት ቅድስት አርሴማን የሚመስል የለም፡፡ አምላክን ከወለደች ከእመቤታችን በቀር የሚበልጣት ማንም የለም፡፡ እርሷም በምግባር በሃይማኖት ያጌጠች በመንፈሳዊ ተጋድሎ የበረታች በትሩፋት የበለጸገች ናት፡፡ ብሉይን ከሐዲስ አጠናቃ ተማረች፡፡ የአገሮችንም (የሮምያን፣ የጽርዕን፣ የሶርያን፣ የኪልቅያን) ቋንቋዎች ታውቅ ስለነበር ቅዱሳት መጻሕፍትንም ወደ ተለያዩ አገራት ቋንቋዎች ትተረጉማለች፡፡

ቅድስት አርሴማ 15 ዓመት በሆናት ጊዜ ከሃዲውን ዲዮቅልጥያኖስን ሰይጣን አስነሥቶት ነገሠ፡፡ ይኸውም ከሃዲ ንጉሥ ሚስት ያባ ዘንድ በመልኳ ውብ የሆነች ሴት ልጅን ይመርጡለት ዘንድ በሀገሩ ሁሉ እንዲሄዱ ጭፍሮቹን አዘዘ፡፡ ያገኟትንም ውብ የሆነችን ሴት መልኳን ሥለው ያመጡለት ዘንድ ሠዓሊዎችንም አብሮ ላከ፡፡ የተላኩትም ሰዎች ወደ ሮሜ አገር በደረሱ ጊዜ ቅድስት አርሴማ ያለችበትን የደናግል ገዳም አገኙ፡፡ ወደ ገዳሙም ገብተው ቅድስት አርሴማን አይተዋት በመልኳ ማማር እጅግ ተደስተው ‹‹ለንጉሡ ሚስት የምትሆነው ይህች ናት›› ብለው መልኳን በሥዕል ቀርጸው ለንጉሡ ላኩለት፡፡ ንጉሡም ሥዕሏን በተመለከተ ጊዜ ፈጽሞ ተደሰተ፡፡ ስለ ሠርጉ ወደ እርሱ ይመጡ ዘንድ ሕዝቡን ይጠሩአቸው ዘንድ ወደ ነገሥታቱና ወደ መኳንንቱ ሁሉ ላከ፡፡

እሊያ ደናግልም ይህን ነገር በአወቁ ጊዜ ይረዳቸው ዘንድ ድንግልናቸውንም ይጠብቅ ዘንድ አልቅሰው ወደ እግዚአብሔር ለመኑ። ከዚህም በኋላ ተነሥተው በሥውር ሸሹ የንጉሥ ድርጣድስ ግዛት ወደ ሆነ ወደ አርማንያ ሀገርም ደርሰው በአንድ ቦታ ተቀመጡ ከእርሳቸውም ጋር የተሰደዱ ቁጥራቸው ሰባ አምስት የሆነ ወንዶች፣ ሴቶችም ሠላሳ ዘጠኝ የሆኑ ከእርሳቸው ጋራ አሉ። ምግባቸውን አያገኙም ነበርና በታላቅ ችግር ውስጥ ኖሩ ከእነርሱም መብራት የምትሠራ አንዲት ሴት ነበረች ከእርሷም የእጅ ሥራ ከሚገኘው በየጥቂቱ ይመገባሉ።

ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስም የከበረች አርሴማን በፈለጋት ጊዜ አላገኛትም ግን በአርማንያ አገር እንዳለች ስለርሷ ሰማ። ደግሞ ለአርማንያ ንጉሥ ለድርጣድስ ስለርሷ ከዲዮቅልጥያኖስ ሸሽታ እንደ መጣች የአርሴማን ሥራ ነገሩት እርሱም አንዱን የአርማንያ መኰንን ለእኔ ጠብቃት ወደ እኔም ላካት ብሎ አዘዘው።

ደናግሉም ይህን በሰሙ ጊዜ ወደ ሌላ ቦታ ተሠወሩ ወደ ንጉሥም ወነጀሉአቸው ንጉሡም ቅዱስት አርሴማን በክብር አድርገው ያመጧት ዘንድ አዘዘ እርሷም ወደ እርሱ መምጣትን እምቢ በአለች ጊዜ እየጎተቱ ወስደው ወደርሱ አደረሷት።

የቅድስት አርሴማንም ላህይና ደም ግባቷን በአየ ጊዜ ድንግልናዋን ሊያረክስ ሽቶ እናቷ አጋታን አባብላ እሺ ታሰኝለት ዘንድ አዘዛት አጋታም ወደርሷ ሒዳ ልቧን አስጨከነች እንዲህም አለቻት። ዕወቂ ይህ ርኲስ አረሚ እንዳያረክስሽና ሰማያዊ ሙሽራሽን እንዳትተዪ እርሱም ክብር ይግባውና የእግዚአብሔር ልጅ ሕያው ክርስቶስ ነው።

ንጉሡም ይዞ ወደ እልፍኙ ሊአስገባት ከአደባባይ መካከል ተነሥቶ ድንግል አርሴማን ያዛት። በዚያንም ጊዜ በቅድስት አርሴማ ላይ የእግዚአብሔር ኃይል አደረባትና በምድር ላይ ጣለችው እርሱ ግን በጦርነት እጅግ የጸና አርበኛ ስለ ነበር በታናሽ ሴት ብላቴና ስለተሸነፈ ያን ጊዜ አፈረ። ራሷንም በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘና ቆረጧት ከዚህም በኋላ ደናግሉን ሁሉ ከእናታቸው አጋታ ጋር ይገድሏቸው ዘንድ አዘዘ።

አንዲት የታመመች ድንግል ነበረች በዐልጋዋ ላይም እንደተኛች ወደ ወታደሮች ጮኸች መጥተውም እንደ እኅቶቿ ራሷን ቆረጡ ሁሉም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበሉ እነዚያንም ከሮሜ አገር አብረው የመጡ ወንዶችን ገደሏቸው ቁጥራቸውም ሰባ አምስት ናቸው ሥጋቸውም በተራራ ላይ የተጣለ ሁኖ ቀረ።

ሰማዕታትም ከተገደሉ በኋላ በንጉሡ ላይ ጋኔን ተጫነበት መልኩም ተለውጦ እንደ እርያ ሆነ። ቅዱስ ጎርጎርዮስ ወደርሱ መጥቶ በላዩ ጸልዮ እስከ አዳነው ድረስ ስለዚህም ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመነ። የቅዱሳን ሰማዕታትንም ሥጋቸውን ከተጣለበት ሰብስበው በአማረ ቦታ አኖሩአቸው ያማረች ውብ የሆነች ቤተ ክርስቲያንም ተሠራችላቸው። ከእነርሱም ታላላቅ ድንቆች ተአምራት ተገለጡ።

የእናታችን ቅድስት አርሴማ ምልጃዋ ይጠብቀን!

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
539 viewsedited  18:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ