Get Mystery Box with random crypto!

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiopian_orthodox — የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiopian_orthodox — የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች
የሰርጥ አድራሻ: @ethiopian_orthodox
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 30.48K
የሰርጥ መግለጫ

በዚህ Channel ውስጥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን ዶግማ ፤ ቀኖና እና ትውፊት የጠበቁ ትምህርቶች ይተላለፉበታል፡፡
ለአስተያየት: ጥቆማና ጥያቄ በዚህ ያግኙን ☞ @Ethiopian_Orthodox_bot
Buy ads: https://telega.io/c/Ethiopian_Orthodox

Ratings & Reviews

1.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 35

2022-10-07 13:12:48
ብሂለ አበው ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

https://t.me/abew_z_orthodox
https://t.me/abew_z_orthodox
1.1K views10:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-06 10:01:29 "ማርያም ድንግል እንወድሻለን" በማኅበረ ቅዱሳን መዘምራን

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
1.4K views07:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-06 09:59:06
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
1.4K views06:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-06 09:59:06 «በቤተክርስቲያን የጽጌ ማኅሌት እንጂ የጽጌ ጾም የሚባል ነገር የለም» ይባላልን
━━━━━━━✦༒ ༒✦━━━━━━━

የዛሬ ዓመት ነው፤ እጅ ለመንሳትና ደጅ ለመጥናት የ«ተክልዬ» የክብር ማረፊያ ወደሆነችው የምድር ጌጥ ደብረ ሊባኖስ አቀናሁ። "ተክልዬ"ን በውሥጣቸው እንዳይ ተስፋም እንዳልቆርጥ ለተሠጡኝ አባ ጌታዬ (የመጋቢ ምትክ) እንግዳ ልጃቸው ነኝ።

ወደ እርሳቸው ማልደን እንወጣና ከወንድሞች ጋር ገብተን ቅድመ ቅዳሴ ተምረን፣ ተመክረንና አድምጠን እንወጣለን።

በዚያ ቀን በተለየ መልክ በመጪው "የጽጌ ጾም" ስለሚገኘው በረከት እየነገሩን አባቶች በልዩ ፍቅር ተጠብቀው እንዴት እንደተጠቀሙባት እየነገሩን እንድንዘጋጅ ይመክሩን ጀመር ። በቸኮለ ማቅኛ (ድፍረት በነዳው አንደበት) ድንገት ማረም አማረኝና «በቤተክርስቲያን ወርኃ ጽጌ ፣ ዘመነ ጽጌ ፣ ማኅሌተ ጽጌ እንጂ የጽጌ ጾም የሚባል ነገርኮ የለም አባታችን!» አልኳቸው።

አልተናደዱም ግን አዘኑ። በትካዜ እጅጉን ዝግ ባለ ድምጽ "እንዲያ እያላችሁ ነው ምታስተምሩት? " አሉኝ። "ለምን መሰልዎት አባታችን… " ብዬ ለማስረዳት እኔ የጽጌን ጾም ንቄና አጥቅቼ ሳይሆን የፈቃድ ጾም ስለሆነ እያልኩ ላብራራ ስንደረደር በከንቱ መውተርተሬን ገትተው እንዲህ አሉ "ተወው የኔ ልጅ አባቴ ቅዱስ ያሬድ እንዲህ ብሎሃል «ጾም ታጸምም ኵሎ ፍትወታት ዘሥጋ ትሜህሮሙ ለወራዙት ጽሙና» #ጾም_የሚባል_የሌለው_በዓለ_ሃምሳ_ብቻ_ነው። ቀንበር አለዘብን ብላችሁ ሸክም አታክብዱ፤ መብል ሥጋን ያገዝፋል ጾም ግን ሰውነትን ያቀላል … ዛሬማ ፍቅር በራቀበት፣ ተስፋ በመነመነበት፤ ትውልድ እያለቀ ፣ እምነት እየደረቀ ያለጊዜዋ ምድርን ልታሳልፉ ጾም የለም እያላችሁ መስበክ ጀምራችኋላ? "
ተግሳጹ ከጅራፍ በላይ የሚያም ነበር! ያኔ ኅሊናውን ዋሻ ፣ አንደበቱን ጋሻ አድርጎ ራሱን የሚከላከል «ሰው» በተፈለገው ልክና በተገቢው መንገድ መጥፋቱ እያስጨነቃቸው «ምላሱ የሰላ አእምሮው የላላ» ከልክ በላይ የሚፈነጭ የኔቢጤው በየቦታው "ጾመ ጽጌን" ማውገዙ እጅጉን ሕመም እንደሆነባቸው አስረድተው በአላዋቂነት ስለሰጠሁት ማቅኛ ይቅርታዬን ተቀብለው አለፉኝ።
ከቅዱስ ያሬድ የነገሩኝን እያሰላሰልኩ
ጾመ … ጻመወ … ጸመወ … (ጾመ፣ መከራ ተቀበለ፣ ዝምአለ) የሚለውን ዘር እየቆጠርኩና እያዛመድኩ ጿሚ፣ ጸማዊ፣ ጽምው ለመሆን በመጣር ከጽሙና መንደር ደርሶ መቆጠብ ያለውን ዋጋ እየመዘንኩ ተመለስኩ።
ባለ ብዙ መልእክት ሆኖ "«ጾም ታጸምም ኵሎ ፍትወታት ዘሥጋ ትሜህሮሙ ለወራዙት ጽሙና» አለ አባቴ ቅዱስ ያሬድ" ያሉት በውስጤ ተመላለሰ።
ጾም የሥጋን ፍላጎቶች ሁሉ ጸጥ ታደርጋለች። ለወጣቶችም ዝምታን ታስተምራቸዋለች። (እውነት ነው እርጋታ፣ ዝምታ ፣ ጽሙና… የጾም ውጤት ነው)
በቤተክርስቲያናችን የበዙ የጾም ቀናት አሉን ፤ በዓመት ውስጥ በአጠቃላይ ወደ ፪፻፷ ገደማ ይደርሳሉ ከእነዚህ ውስጥ ወደ ፩፻፹ የሚጠጉ ቀናት ለሁሉም አማንያን እንደ ግዴታ በአዋጅ አጽዋማት ውስጥ ተካትተዋል። ቀሪዎቹ ደግሞ በካህናቱ እና ሌሎች ምዕመናን በቀኖና ፣ በፈቃድ… የሚጾሟቸው ናቸው። መናንያኑ ግን ከዓመት እስከ ዓመት የዱር ዕፀው ቅጠላ ቅጠል ከውኃ ጋር ሰንበትና በዓለ ፶ እየቀመሱ ከዓመት እስከ ዓመት ይጾማሉ።
【 Ethiopian Christians observe an extraordinary number of fast days, generally reckoned to be about 250. Of these approximately 180 are obligatory for all believers, while the rest are observed by the clergy and other particularly devout individuals. In addition to the organized calendric fasts, throughout the history of the Ethiopian Church there were ascetics renowned for their extreme fasting, often subsisting on little more than wild plants and water.】 ⇝ Sergew Hable Selassie “Worship in the Ethiopian Orthodox Church” & "The Church of Ethiopia: a Panorama of History and Spiritual Life"
✧ ቅዱስ ያሬድ ሌላ ምክርም አለው ፦
⇨ "በፍኖተ ጽድቅ ፍትሑ ለእጓለ ማውታ ወአነሂ እትመየጥ ኀቤክሙ ለሣህል ከመ ፈለገ ሰላም ዛቲ ጾም በቍዔት ባቲ ትፈሪ ጽድቅ ትሜህሮሙ ለወራዙት ጽሙና ወታበጽሕ ውስተ አዕምሮ ዚአሁ"
➺ በእውነት መንገድ ለድሃ-አደግ ፍረዱ (የተቸገረውን እርዱ) እኔም ወደእናንተ ለይቅርታ እንደ ሰላም ወንዝ እመለሳለሁ፤ ጥቅም የሚገኝባት ይህች ጾም ጽድቅን የምናፈራባት ለወጣቶች እርጋታን የምታስተምር እርሱን ወደማወቅ የምታደርስ ናት ።
✧ የተዋህዶ ዓይን የኢትዮጵያ ብርሃን ቅዱስ ያሬድ ሌላም ምዕዳን ይጨምራል
⇨ ጾም ቅድስት ትሜህሮሙ ለወራዙት ጽሙና ዛቲ ጾም ቅድስት ወበይእቲ ጾም ተመጠወ ሙሴ ሕገ እግዚአብሔር ጾም ቅድስት ወበይእቲ ጾም ኤልያስ ዓርገ ውስተ ሰማያት ጾም ቅድስት ወበይእቲ ጾም ዳንኤል ድኅነ እምአፈ አናብስት ጾም ቅድስት ሶስና ድኅነት እምዕደ ረበናት ጾም ቅድስት ዓቀመ ኢያሱ ፀሐየ በገባዖን ጾም ቅድስት ጳውሎስኒ ይቤ ትግሁ እንከ አኃውየ በጾም ወበጸሎት ዛቲ ጾም ቅድስት ወበይእቲ ጾም ጾም ቅድስት ትሚህሮሙ ለወራዙት ጽሙና።

➺ ቅድስት ጾም ለወጣቶች እርጋታ ዝምታን ታስተምራቸዋለች። ጾም የተለየችና የተቀደሰች ናት። በዚህች በተቀደሰችዋ ጾም ሙሴ የአምላኩን ሕግ ተቀበለባት፤ ጾም የተለየችና የተቀደሰች ናት። በዚህች ቅድስት ጾም ኤልያስ ወደ ሰማይ ዐረገባት ፤ ጾም የተለየችና የተቀደሰች ናት። በዚህች ቅድስት ጾም ዳንኤል ከአንበሶች አፍ ዳነባት በዚህች ቅድስት ጾም ሶስና ከመምህራኑ ክስ ተርፋለች በዚህች ቅድስት ጾም ኢያሱ በገባዖን ፀሐይን አቆመ ። ጾም የተለየችና የተቀደሰች ናት! ጳውሎስ እንዲህ አለ ‘ እንግዲህ ወንድሞቼ በጾምና በጸሎት ትጉ’ ጾም የተለየችና የተቀደሰች ናት። በዚህች ቅድስት ጾም ለወጣቶች እርጋታ ዝምታን ታስተምራቸዋለች።
✧ ደራሲውም እንዲህ ሲል መክሮናል
… ማርያም ታቦት ጽላተ ኪዳን ሐዲስ፣
ቅብዕኒ ርጢነ ጾም እስከ ሰኮና እግር ወርእስ፣ እስመ ጾም ትፌውስ ሕማማ ለነፍስ።
➺ ለሐዲስ ኪዳን ጽላት ታቦቱ ፡ ማርያም አንቺ ነሽና የጾም መድኃኒቱን ቀቢኝ ፡ ከራስጠጉር እስከ እግር ሰኮና
የነፍስ ሕመም የሚፈወስ ፡ በጾም «በጸሎት» ነውና።
እንግዲህ ከአባቴ ይኼን ያዝኩላቸው በቤተክርስቲያናችን ጾም የሌለው ለበዓለ ሃምሳ ብቻ ነው ይልቅ ሰውን በማንጠቅምበት አልፎም ለማያድንም ምክንያት ጾመ ጽጌን አንንቀፋት።
"ወዝኬ ዘሰ ዘይሜህር ዘእንበለ ይኅሥሡ እምኔሁ ወዘእንበለ ምክንያተ ድልወት ለበቁዔተ ሰማእያን ውእቱኬ አብድ ወአኮ ጠቢብ ➺ ይኸውም አስተምረን ሳይሉት እና ሰሚዎቹን የሚጠቅምበት ምክንያት ሳይኖረው ላስተምራችሁ የሚል ሰው አላዋቂ ነው እንጂ አዋቂ አይባልም፡፡ ሰነፍ እንጂ ጠቢብ አይባልም" (ፊልክስዩስ)
እንኳን ለጽጌ ጾም አደረሰን አደረሳችሁ። በማኅሌት የታጀበውን ተወዳጁን ዘመነ ጽጌ ወርኃ ጾም ተደርቦበት የበረከት ዋጋና በጎ ምላሽ የሚያሰጠን ያድርግልን።

ቴዎድሮስ በለጠ ፳፮/፩/፳፻፲፬

@Ethiopian_Orthodox
1.3K views06:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-05 21:41:31

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
583 views18:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-05 21:41:31ጽጌ መዓዛ ሠናይ

ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ከመስከረም ፳፮ እስከ ኅዳር ፮ ያለውን ወቅት ወርኃ ጽጌ ትለዋለች። ወርኃ ጽጌ የእመቤታችን ስደት የሚታሰብበት ወቅት ነው። ስደት አድካሚ ጉዞ አለው። ረኀብና ጥምም መገለጫው ነው። ጠቢቡ "እነሆ ክረምት ዐለፈ ዝናቡም አልፎ ሔደ፤ አበቦችም በምድር ላይ ተገለጡ፤ የዜማም ጊዜ ደረሰ፤ የቁርዬም ቃል በምድራችን ተሰማ" (መኃ. ፪÷፲፩-፲፪) ብሏል። “ክረምት ዐለፈ” ያለው የአዳም የመከራ ዘመን ማለፉን ሲናገር ነው። ሊቁ ቅዱስ ያሬድም እመቤታችንን መዓዛ ባላቸው ጽጌያት መስሎ "መዓዛሆሙ ለቅዱሳን " ብሏታል።
አባ ጊዮርጊስ በመጽሐፈ ምሥጢር" አዳም እንኳን ተሳሳተ ፣አዳም እንኳን ወደቀ በገነት ውስጥ ቢኖር ኑሮ አዳም ከሔዋን ጋር ዕፀ-ሕይወትን እየበላ ይኖር ነበር እንጂ እኛ አናገኛትም ነበር።፣አዳም ባይሳሳት ኑሮ አንቺ አትወለጅም ነበር። ስለዚህ በገነት የተነፈግነውን ዕፀ-ሕይወት አንቺ ሰጥተሽናልና እናመሰግንሻለን” ብሏታል።
ቅዱስ ዮሐንስ "ታላቅ ምልክትም በሰማይ ታየ፤ ፀሐይን ተጐናጽፋ ጨረቃ ከእግሮችዋ በታች ያላት በራስዋም ላይ የአሥራ ሁለት ከዋክብት አክሊል የሆነላት አንዲት ሴት ነበረች። እርስዋም ፀንሳ ነበር፤ ምጥም ተይዛ ልትወልድ ተጭንቃ ጮኸች። ሌላም ምልክት በሰማይ ታየ፤ እነሆም ታላቅ ቀይ ዘንዶ፤ ሰባት ራሶችና አሥር ቀንዶችም ነበሩት፤ በራሶቹም ላይ ሰባት ዘውዶች ነበሩ"(ራእ. ፲፪÷፫) ብሏል። ፀሐይ የተባለው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። እርሱ በቀንም፣ በሌሊትም የሚያበራ እውነተኛ ብርሃን ነው። ፲፪ የክብር አክሊል የተባሉት ፲፪ ሐዋርያት ናቸው። ቅዱሳን ሐዋርያት ለድንግል ማርያም ጌጦች በመናቸው አክሊል አላቸው። ድንግል ማርያምም ለሐዋርያት ጌጣቸው ናት። "ሞገሶሙ ለሐዋርያት" እንዲል ቅዳሴ ማርያም። በጨረቃ የተመሰለው ዮሐንስ መጥምቅ ነው። ጨረቃ ሠርቅ ካደረገችበት ጀምሮ ብርሃኗ እየጨመረ በ፲፭ኛው ቀን ሙሉ ትሆናለች። ቅዱስ ዮሐንስም አንገቱን ከተቆረጠ በኋላ ፲፭ ዓመት አስተምሯል። ጨረቃን ተጫምታ ነበር ማለት ዮሐንስ ገና ከእናቱ ማኅፀን ሁኖ ለድንግል ማርያም ሰገደ ማለት ነው።
ቅዱስ ዮሐንስ "ምጥ" ያለው ድንግል ማርያም የገጠማትን ጭንቅ ነው። ቅዱስ አትናቴዎስ " ያለ ዘር ፣ያለ ምጥ ወለደችው" (ሃይ.አበው ምዕ•፳፰ ክ፲፬ ቊ ፲፱) በማለት የወለደችው ያለ ምጥ መሆኑን ተናግሯል። እመቤታችን ድንግል ማርያም ስለሦስት ነገሮች ብትጨነቅም ክርስቶስን ስለመውለድ አልተጨነቀችም። ድንግል ማርያም የተጨነቀችው ልጇ በቀራንዮ በተሰቀለ ጊዜ፣ ስለ ኃጥአን ለመከራ መዳረግ እና የሦስት ዓመቱ የግብፅ በረሃ ስደቷ ያስጨንቃት ነበር።
እርሷም "ከእንግዲህ ትውልድ ሁሉ ያመሰግኑኛል” በማለት ትውልደ ሴም፣ ትውልደ ካም፣ ትውልደ ያፌት እንደሚያመሰግናት ተናግራለች። “እነሆ እግዚአብሔር በፈጣን ደመና ሁኖ ወደ ምድረ ግብፅ ይመጣል፤ የግብፅ ጣዖታትም በፊቱ ይርዳሉ"(ኢሳ ፲፱÷፩) ተብሎ የተነገረው በስደቷ ወቅት የተፈጸመውን ነው። ሆሴዕም "ሕፃን በነበረ ጊዜ ወደድኩት፤ ልጄንም ከግብጽ ጠራሁት"(ሆሣ ፲፩÷፩:) ብሏል። ጌታችን የተሰደደው ግብፅን እና ኢትዮጵያን ለመባረክ ነው። አንድም ሰይጣንን ከሰው ልቡና አስወጥቶ ለመስደድ ነው።

በድንግል ማርያም ስደት ምክንያት ክርስቲያኖች የሰማዕትነትን በረከት አግኝተዋል። ሰሎሜ ጌታን በማዘል ድንግል ማርያምን ስትረዳ የመከራዋ ተካፋይ በመሆን አብራ ተንከራታለች። ጥጦስም ጌታን በትከሻው ተሸክሞ ሸኝቷቸዋል። በቅዳሴያችን "በቀኝ የተሰቀለውን ሽፍታ በመስቀል ላይ እንዳሰብከው አቤቱ እኛንም በመንግሥትህ አስበን" በማለት እንማጸናለን። በእመቤታችን ስደት በረከትን ያጡት ሄሮድስ፣ ትዕማር፣ዳክርስ እና መሰሎቻቸው ናቸው። ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በየዓመቱ የድንግል ማርያምን ስደት በማሕሌት፣ በዝክርና በቅዳሴ ታስባለች። በዚህ ምክንያት ድንግል ማርያምን “አንቲ ውእቱ ጽጌ መዓዛ ሠናይ” በማለት እናመሰግናታለን።

የእመቤታችን ፍቅሯ በልባችን ምስጋናዋ በአንደበታችን እጥፍ ድርብ ሆኖ በእኛ በምናምን ክርስቲያኖች ላይ ይደርብን!

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
634 views18:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-05 09:31:18
+++ ጸአተ - ክረምት +++

ዛሬ መስከረም ፳፭ (25) በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን ትውፊት መሠረት "ጸአተ ክረምት" (የክረምት መውጫ) ይባላል። ክረምት ላዩ ውኃ ታቹ ውኃ ነው። አያስተላልፍም። አስቸጋሪ ወቅት ነው። ክረምት በምሳሌነቱ የመከራ ወቅት ነው። በመከራ የተመሰለው ወርኃ ክረምት ሲወጣ ደስ ያሰኛል።

በሌላ በኩል ክረምት በሞት ይመሰላል።
ቅዱስ ጳውሎስ ሮም ውስጥ ታስሮ ሳለ "አስተፋጥን ትምጻእ ኃቤየ ቅድመ ክረምት - ከክረምት በፊት እንድትመጣ ትጋ።"
(፪ኛ ጢሞ ፬፥፳፩ /4:21) እያለ ክታብ ጽፎ ቅዱስ ጢሞቴዎስን ይመክረዋል። ሞት ሳይመጣ ማለቱ ነው።

ጌታችንም በወንጌል "ኢይኩን ጉያክሙ በክረምት ወበሰንበት - ነገር ግን ሽሽታችሁ በክረምት ወይም በሰንበት እንዳይሆን ጸልዩ፤" (ማቴዎስ ፳፬፥፳ /24:20) ሲል አስተምሮናል።

ክረምትን ተከትሎት የሚመጣው ዘመን ደግሞ ወርኃ ጽጌ (ዘመነ መጸው) መሆኑ አበባና ፍሬ የሚታይበት ወርኃ ትፍሥሕት ነው። ለዓይን ይማርካል። ለልብ ደስ ያሰኛል።

እንደተመለከትነው ለኢትዮጵያ ሀገራችን ከባድ ክረምት ሆኖባት አልፏል። ሞትምና ሐዘን፣ ጥልና ክርክር፣ በሽታና ቸነፈር በብዛት ተፈራርቆብናል። ይህም በበደላችን ምክንያት የመጣ ደመወዝ ነው። ደመወዛችን ከፍ እንዳይል ከክፋት እንመለስ!

አምላከ ቅዱሳን እግዚአብሔር በቸርነቱ የመከራውን ክረምት ያሳልፍልን!

Kesis Getnet Aytenew

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
837 views06:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-04 09:03:44
ብሂለ አበው ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

https://t.me/abew_z_orthodox
https://t.me/abew_z_orthodox
1.6K views06:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-02 11:07:43
ወደ እውነተኛ ክርስትና የሚመሩንን የቅዱሳን አባቶቻችን ብሂል(ምክርና ተግሳጽ) በልዩ አቀራረብ የሚያገኙበት ቻናል!

ብሂለ አበው ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ


https://t.me/abew_z_orthodox
https://t.me/abew_z_orthodox
1.4K views08:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-01 17:42:19
"ኢሬቻ"ና ክርስትና በብፁዕ አቡነ ሄኖክ




@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
2.3K views14:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ