Get Mystery Box with random crypto!

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiopian_orthodox — የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiopian_orthodox — የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች
የሰርጥ አድራሻ: @ethiopian_orthodox
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 30.48K
የሰርጥ መግለጫ

በዚህ Channel ውስጥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን ዶግማ ፤ ቀኖና እና ትውፊት የጠበቁ ትምህርቶች ይተላለፉበታል፡፡
ለአስተያየት: ጥቆማና ጥያቄ በዚህ ያግኙን ☞ @Ethiopian_Orthodox_bot
Buy ads: https://telega.io/c/Ethiopian_Orthodox

Ratings & Reviews

1.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 33

2022-11-05 23:26:16
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
1.6K views20:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-05 23:24:11 መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ

ጌታችን መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ ለእኛ ሲል በፈጸመው የማዳን ሥራ ክፉዎች አይሁድ ከምሽቱ 3:00 ጌቴሴማኒ ውስጥ ያዙት::

¤ሙሉውን ሌሊት ከቀያፋ ወደ ሐና: ከሐና ወደ ቀያፋ ሲያመላልሱት: አስረው ሲደበድቡት አድረዋል::

ዝም ቢላቸው ዓይኑን ሸፍነው በጥፊ መቱት::
¤ምራቃቸውን ተፉበት:: ዘበቱበት::
¤ራሱንም በዘንግ መቱት::
¤እርሱ ግን ሁሉን ታገሰ::
¤በጧት ከገዢው ዘንድ ሞት እንዲፈረድበት አቀረቡት::

በሠለስት (3:00 ላይ) አካሉ እስኪያልቅ እየተዘባበቱ 6,666 ገረፉት::

ሊቶስጥሮስ አደባባይ ላይ እርጥብ መስቀል አሸክመው ወደ ቀራንዮ ወሰዱት:: 6:00 ላይ በረዣዥም ብረቶች 5 ቦታ ላይ ቸንክረው ሰቀሉት::

7 ታላላቅ ተአምራት በምድርና በሰማይ ታዩ:: ዓለም በጨለማ ሳለች ጌታ በመስቀል ላይ 7 ቃላትን
ተናገረ:: ከቀኑ 9:00 አካባቢ በባሕርይ ስልጣኑ ቅድስት ነፍሱን ከቅዱስ ሥጋው ለየ::

በዚያች ሰዓትም ወደ ሲዖል ወርዶ የታሠሩትን ሁሉ ፈታ::

11:00 ላይ ደጋጉ ዮሴፍና ኒቆዲሞስ ከታላቅ ክብርና ሐዘን ጋር በአዲስ መቃብር ቀበሩት:: በዚአች ቀን ድንግል ማርያም ልቧ በሐዘን ተቃጠለ:: ወዳጁ ቅዱስ ዮሐንስም ፍፁም ለቅሶን አለቀሰ:: ቅዱሳት አንስት በዋይታ ዋሉ::

ፈጣሪያችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለው መጋቢት 27 ቀን ቢሆንም በዓሉ ወደ ጥቅምት እንዲመጣ ያደረጉት አበው ሊቃውንት ናቸው:: ምክንያቱም ብዙ ጊዜ መጋቢት 27 የሚውለው ዓቢይ ጾም ውስጥ በመሆኑና የንግሥ በዓላት በዓቢይ ጾም ስለማይፈቀዱ ነው::

ምንም እንኩዋ በቅርብ ጊዜ በዓቢይ ጾም የሚያነግሡ አንዳንድ አብያተ ክርስቲያናት ቢኖሩም አባቶቻችን ግን እንዲህ ያለውን ሥርዓት አላቆዩልንም:: ከበሮና የቸብቸቦ ዝማሬም በወቅቱ የተፈቀደ አይደለም::

+በዚህም ምክንያት የበዓለ ስቅለት ንግሡ ወደ ጥቅምት 27 ሲመጣ: የመጋቢት 5 ገብረ መንፈስ ቅዱስ ንግሥ ወደ ጥቅምት 5: የመጋቢት 10 መስቀል ወደ መስከረም 17 መጥቶ እንዲከበር ሆኗል::

አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቸርነቱ ይማረን ለሀገራችን ሰላሙን ይላክልን፤ አሜን!

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
1.6K viewsedited  20:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-31 08:44:05 @Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
1.4K views05:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-31 08:43:09
በአባቶች ልመና

በአባቶች ልመና እስኪ ልለምንሽ ፤
እኔማ ግብር የለኝ ለመቆም ከፊትሽ ፤
ረሃብሽን አሳስቢ ድንግል ሆይ እባክሽ።
አዝ-------------//
ግብሬን አውቀዋለሁ ምንም ምን ጽድቅ የለኝ /2/፤
ውኃ ያልጎበኘው አዳፋ ልብስ ነኝ።
አዝ----ጥምሽን
ለብሼ ሲያምርብኝ ጻድቅ እመስላለሁ /2፤
ድንግል ሆይ ታውቂያለሽ ውስጤን ጎስቁያለሁ።
አዝ----ልቅሶሽን
በኃጢያቴ ሳለቅስ ከጠዋት እስከ ማታ /2/፤
ድንግል ሆይ አትርሺኝ ሁኝልኝ አለኝታ።
አዝ-----ስደትሽን
ካጠጣሽው ውሻ ያን ጊዜ ተጠምቶ /2/፤
እኔም በምግባሬ አልሻልም ከቶ።
አዝ----ሃዘንሽን አሳስቢ

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
1.4K views05:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-28 11:46:13
ብሂለ አበው ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

https://t.me/abew_z_orthodox
https://t.me/abew_z_orthodox
2.4K views08:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-25 13:47:38 +++ ‹‹በእግዚአብሔር ፈንታ›› +++

የአእምሮ ሕመም ሕክምና ይሰጥባቸው ከነበሩ ማዕከላት በአንዱ እንዲህ ሆነ፡፡ ነርሷ ሕመምተኛውን ‹‹አንተ ማን ነህ?›› ስትል ትጠይቀዋለች፡፡ እርሱም ‹‹ናፖሌዎን›› ነኝ ብሎ ይመልሳል፡፡ ‹‹ናፖሌዎን መሆንህን ማን ነገረህ?›› ብትለው ‹‹እግዚአብሔር ነዋ›› ሲል ፈርጠም ብሎ መለሰ፡፡ ይህን ጊዜ ከአጠገባቸው ሆኖ ምልልሱን ይሰማ የነበረ ሌላ ታካሚ ድንገት ጣልቃ ገብቶ ‹‹ኸረ እኔ አልነገርኩት›› አለ፡፡

  ይህን ታሪክ ስትሰማ ፈገግ አላልህም? ‹ሰው ራሱን ‹‹እንደ እግዚአብሔር›› አድርጎ የሚቆጥረው አእምሮውን ሲታመም ብቻ ነው› ብለህስ አላሰብህም፡፡ እውነታው ግን ሌላ ነው፡፡ ጤነኛ አእምሮ እንዳለን የምናስብ ብዙዎቻችን ኑሯችን እና እንቅስቃሴያችንን ብንፈትሽ ነገረ ሥራችን ሁሉ ‹‹በአምላክ ፋንታ›› ነው፡፡ አፍ አውጥተን ‹‹እኔ እግዚአብሔር ነኝ›› አንበል እንጂ እንዲህ ከማለት የማይተናነስ ሥራ ግን እንሠራለን፡፡

  ፍርድ የእግዚአብሔር ነው፡፡ እኛ ግን ወንድሞቻችን ላይ በመጨከን ስንት ጊዜ በክርስቶስ የፍርዱ ዙፋን ላይ ተቀመጥን፡፡ የሰውን ድካም ሳንረዳ ፈጥነን በመፍረድ ስንት ጊዜ ራሳችንን በእግዚአብሔር ቦታ አስገባን? እስኪ ዮሴፍን እናስበው፡፡ ወደ ግብጽ ባሪያ አድርገው በግፍ የሸጡት ወንድሞቹ ከአባታቸው ሞት በኋላ እርሱ ወደ ተሾመበት ግብጽ መምጣት በፈለጉ ጊዜ፣ የክፋታችንን ብድራት ያስከፍለናል ብለው ስለፈሩ ‹‹በደላችንን ተውልን›› ሲሉ መልእክተኛ ልከውበት ነበር፡፡ የዋሁ ዮሴፍም ይህንን ሲሰማ እያለቀሰ እንዲህ አላቸው ‹‹አትፍሩ፤ እኔ በእግዚአብሔር ፋንታ ነኝን?››፤ አይደለም ሳታውቀው ዐውቀኸው እንኳን በበደለህ ወገንህ ላይ ለመፍረድ ልብህ በከጀለህ ጊዜ ለራስህ የዮሴፍን ጥያቄ ጠይቀው፡፡ ‹‹እኔ በእግዚአብሔር ፋንታ ነኝን?›› (ዘፍ 50፡19)

ራሱን መምራት ያልቻለ ደካማ ሌላው ላይ በፍርድ ለመሠልጠን ሲሞክር ከማየት በላይ እግዚአብሔርን ምን የሚያሳዝን ነገር አለ?

ሁሉን የሚያውቅ እግዚአብሔር ነው፡፡ ነገር ግን የሁሉ ጥበብ መፍለቂያዎች እንደ ሆንን፣ ከእኛ የተሠወረ አንዳች እንደሌለ እያሰብን ‹‹አምላክ አምላክ የምንጫወት›› ጥቂቶች አይደለንም፡፡ የእኛ ጣት ያልገባበት ሁሉ የማይጥመንና ትክክል የማይመስለን፣ እኛ ካልመራን፣ የእኛ ቡራኬ ከሌለበት የምናራክስ፣ ‹‹አላውቅምን›› የማናውቅ፣ ብዙኃኑን እንደ ጨዋ (ምንም የማያውቅ) የምንቆጥር አያሌ ነን፡፡ የሚያሳዝነው ግን ዓለም በአንድ ወይም በጥቂት ሰው ፈቃድ ስላልተገነባች በአንድ ወይም በጥቂቶች ፈቃድ ብቻ ልትመራ አትችልም፡፡ ሁሉን በሁሉ ማድረግ የሚችለው ሁሉን የሚያውቀው እግዚአብሔር ብቻ ነው፡፡

‹‹ዕረፉ፤ እኔም አምላክ እንደ ሆንሁ ዕወቁ›› መዝ 46፡10

ዲያቆን አቤል ካሳሁን

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
3.8K views10:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-24 09:27:33
@Ethiopian_Orthodox
3.6K views06:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-24 09:27:33 ጥቅምት ፲፬
ጻድቁ አቡነ አረጋዊ


ጥቅምት ዐሥራ አራት በዚህችም ቀን ታላቁና የከበረው አባታችን አቡነ አረጋዊ (ዘሚካኤል) የተሰወሩበት ነው።

እኚህ አባት ከ፱(9) ቅዱሳን አባቶች አንዱ ሲሆኑ
አባታቸው ይስሐቅ የሮም ንጉስ ነበሩ፡፡ እናታቸው ንግስት እደና ይባሉ ነበር፡፡ የመጀመሪያ ስማቸው ዘሚካኤል ነው፡፡ ጥበብ መንፈሳ ሲማሩ አድገው ወደ እስክንድርያ ገዳም ገቡ፡፡ አበምኔቱ አባ ጳኩሚስ በፈቃደ እግዚአብሔር የመጡ መሆናቸውን አውቀው መዓረገ ምንኩስና ሰጥተዋቸዋል፡፡

የንጉሳዊ የቅንጦት ኑሮ ንቀው ትተው ገዳም ገብተው በምንኩስና ተወስነዋል፡፡ አባታችን በተጋድሏቸውም ከአባ እንጦንስ፣ ከአባ ጳውሊ እና ከአባ መቃርስ ቀጥሎ በአራተኛ ማዕረግ አበ መነኮሳት ሆነው ተመርጠዋል።

በገዳመ ዳውናስ ፯ ዓመት ከቆዩ በኋላ ወደ ሮም ተመልሰው ሲያስተምሩ የሀገራችን ኢትዮጵያን ዜና ሰምተው ለመምጣት በ፬፻፹ ዓ.ም ከአባ ፍሬምናጦስ በኋላ መንገድ ጀመሩ፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም በክንፉ ተሸክሞ አክሱም አድርሷቸዋል፡፡

ተመልሰውም ሄደው ስለ ቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ መስክረዋል፡፡ ሐዋርያ ሳይላክላት በሃይማኖት በምግባር ጸንታ ትኖራለች ብለው ለሰባቱ ዘመዶቻቸው አበው መነኮሳት ነገሯቸው፡፡ ስምንቱም ጓዛቸውን ጠቅልለው በሮም ነግሶ የነበሩ ይስሐቅን (አባ ገሪማን) ጨምረው ንጉስ አልአሜዳ በነገሰ በአምስተኛ ዓመት ማለትም በ፬፻፹ ዓ.ም ወደ ኢትዮጵያ ዘጠኝ ሆነው መጥተዋል፡፡

አባ አረጋዊ እናታቸው ቅድስት እድናን ደቀ መዝሙራቸውን ማትያስን አስከትለው እግረ መንገዳቸውን እያስተማሩና ድውያንን እየፈወሱ ደብረ ዳሞ ደርሰዋል፡፡

ከእግረ ደብር ሆነው አሁን ይህን ተራራ በምን ልወጣው እችላለሁ እያሉ ሲያወጡ ሲያወርዱ በንግግሩ ሐሰት የሌለበት አምላካችን በነቢዩ ዳዊት ላይ አድሮ በመዝሙር ፺/፺፩፥፲፩-፲፮ ላይ “በመንገድህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ መላእክቱን ስለ አንተ ያዝዛቸዋልና፤ እግርህም በድንጋይ እንዳትሰናከል በእጆቻቸው ያነሡሃል። በተኵላና በእባብ ላይ ትጫማለህ፤ አንበሳውንና ዘንዶውን ትረግጣለህ። እንዳለው የታዘዘ ዘንዶ መጥቶ ስደሳ ክንድ በሚያህል ጅራቱ ጠምጥሞ ቅዱስ ሚካኤል ሰይፈ እሳት ይዞ እየጠበቃቸው ከተራራው አናት አድርሷቸዋል፡፡

ወዲያው ሃሌ ሉያ ለአብ ሃሌ ሉያ ለወልድ ሃሌ ሉያ ለመንፈስ ቅዱስ ብለው አመስግነዋል፡፡ ቦታውም ደብረ ሃሌ ሉያ ተብሏል፡፡ በዚያ ዕለት ግማሽ ህብስት በልተው ጠገቡ፤ ከዚያ በኋላ ግን ምድራዊ ሕብስት አልተመገቡም፡፡ በሰንበተ ክርስታያን ከቅዳሴ በኋላ ሕብስተ ሰማያዊ እያመጡላቸው ይመገቡ ነበር እንጂ፡፡ ኋላም ዜና ጽድቃቸውን ሰምተው ከስድስት ሺህ ያላነሱ ደቀ መዛሙርት ተሰብስበውላቸዋል፡፡

ዘጠና ዘጠኝ አመት ሲሞላቸው ጌታ በመንፈቀ ሌሊት ተገልጾ ምድራዊ መንግስትህን ትተህ ስላገለገልከኝ ህልፈት ሽረት የሌለባት ሰማያዊ መንግስቴን አወርሰሃለሁ ብሎ ቃልኪዳን ሰጣቸው፡፡ በስምህ የተማጸነውን እስከ አስራ አምስት ትውልድ ድረስ እምርልሃለሁ አንተም ከሞት ገጽ ትሰወራለህ ብሎ ተስፋቸውን ነገራቸው፡፡ እሳቸው መነኮሳቱን ሰብስበው ከእንግዲህ በሥጋ አታዩኝም ብለው ነግረዋቸው አበምኔት ሾመውላቸው በዚህች ዕለት በዚያው በደብረ ዳሞ ተራራ በስተምስራቅ አቅጣጫ ተሰውረዋል፡፡

በረከታቸው ይድረሰን!

ስንክሳር

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
3.4K views06:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-21 15:03:18
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
4.0K views12:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-21 15:03:18 12. በሀገራችን በልዩ ልዩ ቦታዎች የተፈጠረውን ችግር አስመልክቶ ቤተ ክርስቲያናችን ከመሠረቱ ችግሩ እንዳይፈጠር ለማድረግ የሰላም ጥሪ ማቅረቧ፣ ችግሩም ከተፈጠረ በኋላ ሰብዓዊ ድጋፍን ስታደርግና ስታስተባብር መቆየቷ፣ በዋናነትም ችግሩ እንዲፈታ ሕዝቡን በማስተማር የሰላም ጥሪ በማቅረብ መግለጫዎችን በማውጣት፣ ጾምና ጸሎት እንዲያዝ በማድረግ ያበረከተችው አስተዋጽዖ እውቅና እንዲያገኝ ጉባኤው እየጠየቀ በቀጣይም በሰብዓዊ ድጋፍም ሆነ በጸሎት ሕዝቡን በማስተማርና ወደአንድነት እንዲመጣ በማድረግ በየጊዜው የሰላም ጥሪ በማስተላለፍ ቀጣይነት ያለው ሥራ እንዲሠራ ጉባኤው አሳስቧል፡፡
13. ከቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት ጀምሮ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ስር በሚገኙ መምሪዎች እና ድርጅቶች ለመልካም የሥራ ውጤት የተደረገውን ጥረት ጉባኤው በደስታ ተቀብሎታል፡፡ በመሆኑም ለበለጠ የሥራ ውጤት በመልካም አስተዳደር እየታገዙ አስፈላጊውን ክትትል እየተደረገ ሥራቸውን አሻሽለው እንዲቀጥሉ ጉባኤው አሳስቧል፡፡
14. ቤተ ክርስቲያን በጎቿን የምታሰማራበት መንፈሳዊ መሣሪያ ሁለገብ ትምህርት ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለጨለማው ዓለም ብርሃን እንድትሆን የመሠረታት ናት፡፡ የቤተ ክርስቲያን መኖር ደግሞ የምእመናን የመኖር ነጸብራቅ በመሆኑ ምእመናንን በቃለ እግዚአብሔር አንጾና በሚፈለገው መልኩ ቀርጾ ማውጣት የቤተ ክርስቲያን ተግባር ነው፡፡ በመሆኑም በአባቶቻችን ለዚሁ ዓላማ ታስቦ የተከፈቱ ሁሉም መንፈሳዊ ኮሌጆች የሰባኪያንና የዘመናዊያን ምሁራን መፍለቂ ምንጮች የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን አገልጋዮች መገኛዎች ናቸው፡፡ በመሆኑም ከየኮሌጆቹ የሚመረቁ ደቀ መዛሙርት በየተመደቡበት አህጉረ ስብከት እየተገኙ የተጣለባቸውን አደራ በተገቢው መንገድ እንዲወጡ፣ ኮሌጆቹን የቅበላ አቅማቸውን ከፍ አድርገው በብቃትና በጥራት በማስተማር ተመራቂዎችን እንዲያበዙ ከእኛ የሚጠበቀውን ሁሉ ለማድረግ ቃል እንገባለን፡፡
ቀደም ሲል ከነበሩት የቤተ ክርስቲያኒቱ ጥቂት መንፈሳውያን ኮሌጆች በተጨማሪ በአሁኑ ጊዜ የተከፈቱ አዳዲስ ኮሌጆች መኖራቸው ጉባኤው መሠረታዊ ጉዳይ አድርጎ ወስዶታል፡፡ በመሆኑ ኮሌጆቹ የቤተ ክርስቲያኒቱ መንፈሳዊና ማኅበራዊ ሂደትን እንዲያስቀጥሉ፣ የችግሮች መፍትሔ እንዲሆኑና በዕቅድና ጥናት ላይ ተመሥርተው የመማር ማስተማር ሂደቱን እንዲያፋጥኑ ጉባኤው አሳስቧል፡፡
በየአህጉረ ስብከቱ ጽ/ቤቶችና መንፈሳዊ ኮሌጆች እየተሰጡ ያሉ የአቅም ግንባታ ሥራዎች መልካም ጅምር በመሆናቸው ጉባኤው አድናቆቱን እየገለጸ ቀጣይ ሂደቱ ግን የቤተ ክርስቲያኒቱን አቅም ባገናዘበ ሃብትን በጠበቀና በዕቅድ ላይ በተመሠረተ እንዲሆን ጉባኤው አሳስቧል፡፡
15. ለቤተ ክርስቲያናችን ሐዋርያዊ ተልእኮ መሳካት ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባ ተግባር ልማት ላይ በማተኮር እየተደረገ ያለውን ጥረት በማጠናከር እና ቤተ ክርስቲያናችን በገቢ ራሷን ማስቻል እንዳለብን ቅድሚያ የሚሰጠው ተግባር ነው፡፡ ሆኖም በቤተ ክርስቲያኒቱ እየተከናወነ ያለውን የአዳዲስ ሕንጻ ግንባታ አስመልክቶ ከብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ ሪፖርት ካገኘነው ግንዛቤ ከፍተኛ መሻሻል እንዳለ ተገንዝበናል፡፡ በመሆኑም በቀጣይ የተጀመሩ ሕንጻዎች የሚጠናቀቁበት፣ አዳዲስ ሥራዎች የሚጀመሩበት ሂደት ትኩረት ተሰጥቶት እንዲቀጥል ጉባኤው እያሳሰበ የልማት ሥራዎችን አጠናክሮ በመቀጠል ቤተ ክርስቲያን አስተማማኝ የገቢ አቅም እንዲኖራት የበኩላችንን አስተዋጽዖ እናደርጋለን፡፡
16. የሕጻናትና ቤተሰብ ጉዳይ ድርጅት ከ1964 ዓ.ም ጀምሮ ከውጭ ሀገር በሚገኝ የገንዘብ ድጋፍ እስከ አሁን ድረስ ከ45 ሺህ በላይ ሕጻናትን ያሳደገ መሆኑን ጠቅሶ አሁን ግን እርዳታው በመቆሙ ሕጻናት የማሳደግ ኃላፊነቱን ለመወጣት አለመቻሉ የተገለጸ ሲሆን በአንጻሩ ደግሞ በአሁኑ ጊዜ በሀገሪቱ ውስጥ ወላጆቻቸውን ያጡና ድጋፍና እንክብካቤ የሚፈልጉ ሕጻናት ቁጥር በጥናት እንደተረጋገጠው ከ4 ሚሊየን በላይ መሆናቸው ተነግሯል፡፡ ስለዚህ የድርጅቱ ጠንካራ እና ደካማ ጎን በሚገባ ተፈትሾ ኃላፊነቱን በሚገባ ይወጣ ዘንድ አስፈላጊው ድጋፍና መመሪያ እንዲሰጠው እንዲሁም አህጉረ ስብከት ቅዱስ ሲኖዶስ ቀደም ሲል ባሳለፈው መሠረት በየአካባቢያቸው የሚገኙ ሕጻናት ማሳደጊዎች አድባራትና ገዳማትን፣ ካህናትና ምእመናንን በማስተባበር ችግረኞች ሕጻናትን እንዲያሳድጉ ጉባኤው ያሳስባል፡፡

በጉባኤው እነዚህና ሌሎች የአቋም መግለጫዎች ተነበዋል፡፡

EOTCMK

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
3.4K viewsedited  12:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ