2022-05-24 15:46:59
#GambellaUniversity
በ2014 ዓ.ም በጋምቤላ ዩኒቨርስቲ የተመደባችሁ የቅድመ ምረቃ መደበኛ መርሃ-ግብር ተማሪዎች ምዝገባ የሚካሄደው ከግንቦት 29 - 30/2014 ዓ.ም መሆኑን አውቃችሁ በተጠቀሰው ቀን በዩኒቨርሲቲው ሬጅስትራር በአካል ቀርባችሁ እንድትመዘገቡ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡
ውድ ተማሪዎቻችን ወደ ዩኒቨርሲቲው ስትመጡ፡
1ኛ. የ8ኛ፣ 10ኛ እና 12ኛ ክፍል ክልላዊና ብሔራዊ ፈተና ውጤት ሰርተፊኬቶች ዋና እና የማይመለስ 1 ኮፒ፣
2ኛ. ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ዋና ትራንስክሪፕት ከማይመለስ 1 ኮፒ ጋር እንዲሁም ስድስት 3x4 ጉርድ ፎቶግራፍ፣
3ኛ. አንሶላ፣ የትራስ ጨርቅና የስፖርት ትጥቅ ይዛችሁ መምጣት ይጠበቅባችኋል፡፡
#ማሳሰቢያ፡ከተጠቀሰው ቀን ቀድመውም ሆነ ዘግይተው የሚመጡ ተማሪዎችን የማናስተናግድ መሆኑን እንገልፃለን፡፡ ለበለጠ መረጃ የዩኒቨርሲቲውን ድረ-ገፅ WWW.gmu.edu.et ወይም የዩኒቨርሲቲውን ረጅስትራር ፌስቡክ GMU Registrar and Alumni Directorate ይጎብኙ፡፡
የጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ ሬጅስትራርና አልሙናይ ዳይሬክቶሬት
SUBSCRIBE ON YOUTUBE
https://www.youtube.com/c/Ethiopia24
https://www.youtube.com/c/Ethiopia24
አስተያየት ለመስጠት @Ethnewbot
➹share &Join Us
@ethiopia_24 @ethiopia_24
@ethiopia_24 @ethiopia_24
2.5K viewsedited 12:46