Get Mystery Box with random crypto!

ኢሳት(ትኩስ ትኩስ ዜናዎች)

የቴሌግራም ቻናል አርማ esatchannal — ኢሳት(ትኩስ ትኩስ ዜናዎች)
የቴሌግራም ቻናል አርማ esatchannal — ኢሳት(ትኩስ ትኩስ ዜናዎች)
የሰርጥ አድራሻ: @esatchannal
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 24.98K
የሰርጥ መግለጫ

አዳዲስ ወሬዎችን ዜናዎችን ማግኝት ከፈለጉ እኛን ይቀላቀሉ ለወዳጅ ዘመዶ #share

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2023-06-12 20:19:55
ህወሃት በሚል ስያሜ ሌላ ፓርቲ ለመመስረት ለምርጫ ቦርድ ጥያቄ ያቀረቡ ሰዎች መኖራቸው ታወቀ
በዚህም ምርጫ ቦርድ ከቀድሞው የህወሓት ፓርቲ ጋር ተመሳሳይ ስም በመሆኑ እና መራጮችን ስለሚያደናግር ፈቃድ ከመስጠት ውድቅ አድርጌዋለሁ ብሏል።
Join now
@esatchannal
3.0K viewsedited  17:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 15:29:58 ሰበር-ጎጃም ሲዋጋ አደረ መከላከያ አፀፋ ገጠመው ድብቁ ስምምነት ፈነዳ












4.5K viewsedited  12:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 13:51:57
ጌታቸው ረዳ ባህርዳር ተገኝቶ ከህዝብ ጋር ባደረገው ቆይታ በፕሮፓጋንዳ በሰራሁት ነገር ልጠየቅ ይገባል አለ
"ህዝባችንን ለዚህ  ችግር የዳረግነው እኛ ፓለቲከኞች ነን። ህዝቡማ ተጋብቶና ተዋልዶ አብሮ ይኖራል። እኔ በሚዲያ ለሰራሁት የፕሮፖጋንዳ ስራ ልጠየቅ ይገባል። ይቅርታም እጠይቃለሁ።" ጌታቸው ረዳ።

በእውነት ማገዶ የፈጀ ቢሆንም ለህዝቡ ሲባል ይሄ አንድ እርምጃ ወደፊት የሚያስኬድ ነው። በፖለቲከኞቹ ስህተት የሆነው ሁሉ ሆኗል። ብዙ ህይወት ጠፍቷል፣ ብዙ ሰው አልቅሷል፣ ብዙ ውድመት ደርሷል።
በተለይ እነ ጌታቸው የሰሜን እዝን በመምታት በይፋ በጀመሩት ጦርነት የትግራይ ህዝብ ተጎድቷል። ሂሳብ እናወራርዳለን በማለት ወደ አማራ ክልል ገብተው ብዙ መከራ አድርሰዋል፣ ደርሶባቸዋል።
ሁሉ ከሆነ በኋላ ወደ ሰላም መመለስ መልካም ነው። የሰላም ፍላጎቱ ግን በቅንነት ላይ የተመሰረተ ሊሆን ይገባል።
4.8K viewsedited  10:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 11:07:40 "ልዩ ሀይሉን ይቅርታ ጠይቀን በአንድ ቀን እንሰበስበዋለን" የአማራ አመራሮች
ጌታቸው ረዳ፣የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሀመር፣የአማራ ክልል ተወካዮች እና የፌደራል ባለስልጣናት ላለፉት ሶስት ቀናት በአዲስ አበባ በነበረው ስብሰባ ላይ የተነሱ ጉዳዮችን እንደሚከተለው ቀርቧል።
ተፈናቃዮች በሚቀጥሉት ሶስት ቀናት ውስጥ እንዲመለሱ ጌታቸው ረዳ ያነሳ ሲሆን የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሀመር ተፈናቃዮቹን ለማቋቋም አሜሪካ እንደምትረዳ ተናግረዋል። ጌታቸው ረዳ ከተፈናቃዮች በተጨማሪ የፀጥታ ሀይል እና አስተዳደር መግባት አለበት ያለ ቢሆንም የአማራ ተወካዮች ይሄን እንዳልተቀበሉት እና ተፈናቃዮች ብቻ መግባት እንዳለባቸው ተነጋግረዋል። የፀጥታ ሀይል እና የራሳችንን አስተዳደር እናስገባለን የምትሉ ከሆነ አካባቢውን ለዳግም ጦርነት የሚዳርግ ነው ብለዋል።
ይሄን የምትሉት የልዩ ሀይሉን መፍረስ እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም ከሆነ እኛ ልዩ ሀይሉን ይቅርታ ጠይቀን በአንድ ቀን እንሰበስበዋለን" እስከማለት የደረሰ ንግግር በአማራ ተወካዮች በኩል ተሰምቷል።
ሁለቱም አካላት ተፈናቃዮችን በተመለከተ የሚቆጣጠር የጋራ  ግብረ ሀይል እንዲቋቋም ተስማምተዋል።
ማይክ ሀመር በዚህ ስብሰባ ላይ ወደ አንድ ወገን ያደላ ንግግር ታይቶባቸዋል።
ከሰሞኑ በራያ እየታየ ያለው የትግራይ ታጣቂዎች እንቅስቃሴ ከተፈናቃዮች ጋር አብረው በመግባት እና አካባቢውን ለመቆጣጠር እንደሆነ ለማወቅ ችያለሁ። ሆኖም አሁን ላይ በውይይቱ ምክንያት በአሉበት እንዲቆሙ ተደርገዋል።

@esatchannal
5.0K viewsedited  08:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 11:03:53 ዝዋይ
ዝዋይ ከተማ ለሊት ከ5:30 እስከ 6:30 ጤና ጣቢያው አካባቢ ከፍተኛ የተኩስ ድምጽ እንደነበር ነዋሪዎቹ ገልፀዋል። የተጎዱ የፖሊስ አባላት አሉ።
በዚሁ አካባቢ በዝዋይ መስመር እንዲሁም በቢሾፍቱ  ኦነግ ሸኔ በተደጋጋሚ ተኩስ በመክፈት እስረኞችን ማስለቀቁ ይታወሳል።

@esatchannal
4.8K viewsedited  08:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 09:53:15 ዶር ይልቃል ቁርጥ ነጥሮ ወጣ ብራቮ ፡ የአለም ሚዲያ አብይ ላይ ተነሳ ፤ ተረጋገጠ ፡ ህጻኑ ፋኖ ታፈነ












5.0K viewsedited  06:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-11 21:35:43 ከራያ
የትግራይ ታጣቂዎች መከላከያን ወደጎን በመተዉ  በማይ ማዕዶ(ገረብ ቆላ)አካባቢ ጥራሬ (ፅራረ)ወደሚባለዉ አቅጣጫ በመንቀሳቀስ ራያን ሰርክል ለማድረግ እየተንቀሳቀሱ ነዉ።

@esatchannal
5.6K viewsedited  18:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-11 21:35:43
ሮማኒያ አፍሪካዊያንንዝንጆሮብሎ የጠራ አምባሳደሯን ከኬንያ ወደ ሀገሯ እንዲመጣ ጠራች
በኬንያ የሮማንያ አምባሳደር የሆኑት ድራጎስ ቲጋው ባሳለፍነው ሚያዚያ ላይ ዘረኛ አስተያየት መስጠታቸውን ተከትሎ የሀገሪቱ መንግስት በይፋ ኬንያዊያንን እና ጥቁሮችን ይቅርታ ጠይቋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም የሮማንያ መንግስት አምባሳደሩን ወደ ሀገሩ እንዲመጣ መጥራቷን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

አምባሳደሩ በናይሮቢ ባለ የተመድ ቢሮ ውስጥ ሆነው በመስኮት ዝንጆሮዎችን ሲያዩ “አፍሪካዊያንም ተቀላቅለውናል” ሲሉ ተናግረዋል ተብሏል፡፡

የሮማንያ ሚዲያዎች ዲፕሎማቱን በመተቸት ሰፊ ሽፋን ሰጥተዋል የተባለ ሲሆን የሮማኒያ ዲፕሎማቶች የሀገራቸውን ሰም ከማጉደፍ እንዲታቀቡ ማሳሰባቸውም ተገልጿል፡፡

በፈረንጆቹ 2014 ላይ በአርመኒያ የሮማኒያ አምባሳደር በአይሁዶች ላይ ያልተገባ ቀልድ ቀልደው ትችቶችን አስተናግደዋል የተባለ ሲሆን የሀገሪቱ መንግስትም በወቅቱ በይፋ ይቅርታ ጠይቆም ነበር።

@esatchannal
5.5K viewsedited  18:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-11 21:35:43 #Update #ባህርዳር

" ልዩነቶች ቢኖሩ እንኳን ልዩነቶቹ ከአማራ እና ትግራይ ሕዝብ በታች ናቸው " - አቶ ጌታቸው ረዳ

" ልዩነቶችን በሕግ፣ በሠላም እና በመነጋገር መፍታት የአማራ ሕዝብ ፍላጎት አለው " - ዶ/ር ይልቃል ከፋለ

ባህር ዳር የሚገኙት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ እና ልዑካቸው ከአማራ ክልል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ይልቃል ከፋለ ጋር እንዲሁም ከህብረተሰቡ ከተውጣጡ ተወካዮች ጋር ውይይት አድርገዋል።

በዚህ ውይይት ላይ አቶ ጌታቸው ረዳ " ዋጋ የማይጠይቅ የሠላም አማራጭ ሳለ በፖለቲከኞች የጠብ ርሃብ ምክንያት በርካታ ጉዳቶች ተከስተዋል " ብለዋል፡፡

" ልዩነቶች ቢኖሩ እንኳን ልዩነቶቹ ከአማራ እና ትግራይ ሕዝብ በታች ናቸው " ያሉ ሲሆን " አሁን የጦርነትን ምዕራፍ ዘግተን የሠላም አማራጮችን የምናይበት ጊዜ ነው " ብለዋል፡፡

" የሁከት እና ግርግር አጀንዳዎች የሚታያቸው ይኖራሉ፤ ነገር ግን ለሕዝብ ካሰብን እና ከሠራን ከሠላም ውጭ የተሻለ አማራጭ የለንም " ሲሉ ተናግረዋል።

የአማራ ክልል ፕሬዜዳንት ዶ/ር ይልቃል ከፋለ በበኩላቸው ፤ " ልዩነቶች ይኖራሉ  ያሉትን ልዩነቶችን ግን በሕግ፣ በሠላም እና በመነጋገር መፍታት የአማራ ሕዝብ ፍላጎት ነው ብለዋል።

" የአማራ ክልል ሕዝብ እና መንግሥት ለሠላም አማራጮች ዝግጁ ነው " ሲሉም ተደምጠዋል።

" የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነቱ ወደ ቀደመው ሁኔታው መመለስ አለበት፣ ትራንስፖርት እና የንግድ እንቅስቃሴ መጀመር ይኖርበታል " ያሉት ዶ/ር ይልቃል " ተከባብረን እና ተደማምጠን ልዩነቶቻችን ለመፍታት መሥራት ይጠበቅብናል " ብለዋል።

የፖለቲካ አመራሩ የጀመረውን የሠላም ግንኙነት የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች በተለይ ደግሞ አዋሳኝ አካባቢ ያሉ የሁለቱም ክልል ሕዝቦች አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል።
@esatchannal
5.4K viewsedited  18:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-11 14:02:37
Update

አቶ ጌታቸው ረዳ ዛሬ ረፋድ ባህርዳር ከተማ ገብተዋል።በዶ/ር ይልቃል አቀባበል ተደርጎላቸዋል ሲል አሚኮ ዘግቧል።

@esatchannal
6.2K views11:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ