Get Mystery Box with random crypto!

ኢሳት(ትኩስ ትኩስ ዜናዎች)

የቴሌግራም ቻናል አርማ esatchannal — ኢሳት(ትኩስ ትኩስ ዜናዎች)
የቴሌግራም ቻናል አርማ esatchannal — ኢሳት(ትኩስ ትኩስ ዜናዎች)
የሰርጥ አድራሻ: @esatchannal
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 24.98K
የሰርጥ መግለጫ

አዳዲስ ወሬዎችን ዜናዎችን ማግኝት ከፈለጉ እኛን ይቀላቀሉ ለወዳጅ ዘመዶ #share

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2023-05-09 03:04:06
ኢንተርፖል በጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ አፈና ላይ እጁ እንደሌለበት አረጋገጠ። ኢንተር ፖል ከትሪፕል ኤ በቀረበለት ጥያቄ በሰጠው መልስ እንዳስታወቀው ጋዜጠኛ ጎበዜ በኢንተርፖል ዳታ ቋት ውስጥ እንደሌለ እና በአፈናው እንዳልተሳተፈ በደብዳቤ ገልጿል።

የብልፅግና መንግስት በውሸት አፈና መፈፀሙ ሳያንስ ኢትዮጵያ ውስጥ እያለ ያፈነውን ጋዜጠኛ ከሀገር ወጥቶ ነበር ብሎ ለህዝብ የገለፀበት ሂደት ፍፁም ውሸት አሳፋሪ እና ብልፅግናዊ መልክ ያለው ነው ተብሏል።

@esatchannal
6.2K viewsedited  00:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-03 22:30:45
< በትግራይ የምግብ እርዳታን ስርቆት የሚያጣራ ኮሚቴ ተቋቁሟል > - ጌታቸው ረዳ
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ በሚመሩት ክልል እየተፈፀመ ነው የተባለውን የእርዳታ ምግብ ስርቆት የሚያጣራ ኮሚቴ ማቋቋማቸውን ይፋ አድርገዋል።
ኮሚቴው በሌ/ጄነራል ፍሰሃ ኪዳኑ እንደሚመራም ጠቁሟል።

አሶሼትድ ፕሬስ ከሰሞኑ አራት የረድዔት ሰራተኞችን አነጋግሮ ባሰራጨው ዘገባ < የተ.መ.ድ. የዓለም ምግብ ፕሮግራም ስርቆቱን ተከትሎ ምርመራ ለማድረግ እርዳታ ማቋረጡን > አመልክቷል።

የክልሉ ፕሬዝዳንት ጌታቸው < የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የዓለም ምግብ ፕሮግራም ያሳለፈዉ ዉሳኔ በድጋሚ እንዲያጤነዉ እንፈልጋለን፤ ዉሳኔዉ በችግር ላይ ያለዉን ሰፊ ህዝብ የሚጎዳ ነዉ። › ሲሉ ተማፅነዋል።

የዜና ምንጩ በተመሳሳይ ባለፈው ወር ተመልክቼዋለሁ ያለውን ደብዳቤ መሠረት አድርጎ በሰራው ዘገባ ለ100 ሺህ ሰዎች የሚበቃ የእርዳታ ምግብ መሰረቁን ገልፆ ነበር።

ጌታቸው ‹ በህዝብ ላይ ተደራራቢ ችግር እየፈጠራችሁ ያላችሁ በመንግስት መዋቅር ይሁን ከዛ ዉጭ ያላችሁ አካላት ከድርጊታቹሁ እንድትቆጠቡ › ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

አክለውም ‹ በህዝብ ላይ ሞት ፈርደዉ ወንጀል እየፈፀሙ ያሉትን አካላት በህግ እንዲጠየቁ እፈልጋልሁ › ብለዋል።
ሚያዚያ 25/2015 ዓ.ም
=======≠========
ለተጨማሪ መረጃዎች ቻናላችንን join ያድርጉ፣መረጃ ለሚፈልጉ ለሌሎች ጋብዙ
1.2K viewsedited  19:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-03 22:30:45
መረጃ
የሸዋ ሰላም እና የልማት ማህበር(ሸዋሰማ) ፣የአማራ ተማሪዎች ማህበር ፣የአማራ ወጣቶች ማህበር እና የአማራ በጎ አድራጎትና ልማት ማህበር የባንክ አካውንታቸው እንዲመረመር የፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ ለሁሉም ባንኮች በፃፈው ደብዳቤ አዝዟል። እነዚህን የሲቪክ ማህበራት በፀረ-ሽብር ወንጀል ጠርጥሬያቸዋለሁ ብሏል።
ሚያዚያ 25/2015 ዓ.ም
=======≠========
ለተጨማሪ መረጃዎች ቻናላችንን join ያድርጉ፣መረጃ ለሚፈልጉ ለሌሎች ጋብዙ
http://t.me/ayuzehabeshaofficial
http://t.me/ayuzehabeshaofficial
1.2K views19:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-03 17:22:10 በሰሜን ሸዋ ዞን አንፆኪያ ገምዛ ወረዳ አምብውሃ በሚባል ቦታ ከፍተኛ የተኩስ ልውውጥ እየተደረገ ይገኛል። የከባድ መሳሪያ ድምፅ ጭምር ይሰማል።
@esatchannal
3.6K viewsedited  14:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-03 17:21:44 የተከበበው ምሬ ወዳጆ መጨረሻ
አራት ኪሎን ያተራመሰው የኢሳያስ ምላሽ
ወርቁ አይተነው ሸጠው



3.6K views14:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-03 15:09:19 ኢትዮጵያ በመገናኛ ብዙሃን ነፃነትን በመስጠት ከአለም ሀገራት የምትበልጪው 30ውን ብቻ ነው ተባለች፡፡

ዛሬ ይፋ በተደረገውና ድንበር የለሽ የጋዜጠኞች ቡድን ወይንም ሪፖርተርስ ዊዝ ሀውት ቦርደር በየዓመቱ ይፋ በሚያደርገው የመገናኛ ብዙሃን ነፃነት የአገራት ደረጃ ኢትዮጵያ ባለፈው ዓመት ከነበረችበት 114ኛ ወደ 130ኛ አሽቆልቁላለች፡፡አዲሱ የመገናኛ ብዙሃን አዋጅ በይዘቱ ለመገናኛ ብዙሃንና ጋዜጠኞች የተሻለ ነፃነትን የሚሰጥ ቢሆንም ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ማድረጉ ግን ፈተና እየገጠመው ነው ተብሏል፡፡

የቅድመ ክስ እስርና ሌላውም በአዋጁ የተከለከለ ቢሆንም ተግባራዊ እየተደረገ አይደለም ተብሏል፡፡በአሁኑ ሰዓት ቢያንስ 8 የመገናኛ ብዙሃን ሰራተኞች በተለያየ ወንጀል ተጠርጥረዋል ተብለው በእስር ላይ ስለመሆናቸውም ተነግሯል፡፡የተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት /ዩኔስኮ/ አማካኝነት ሜይ 3 ወይንም ሚያዚያ 25 ቀን የአለም የፕሬስ ነፃነት ቀን ተብሎ ይታሰባል፡፡

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ምክር ቤት እለቱን በማስመልከት ዛሬ በኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል ባሰናዳው ዝግጅት ላይ የፕሬስ ነፃነትን የተመለከቱ በርከት ያሉ ሀሳቦች ተነስቷል፡፡የዘንድሮ የፕሬስ ነፃነት ቀን በአለም ዙሪያ በጦርነትና የሕዝብ መፈናቀል ሰበብ የሰብአዊ መብቶች ጥበቃ ስጋት ላይ በወደቀበት ጊዜ የሚከበር ነው ተብሏል፡፡በኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት የተከሰቱ ጉልህ የሰብአዊ መብት ችግሮች በፀጥታ ሀይል እየተፈፀመ ያለ ፍርድ እስር ህገ-ወጥና የዘፈቀደ አፈናን በተመለከተ እንደ ሰብአዊ መብት ባሉ ተቋማት የሚወጡ ሪፖርቶችን መነሻ በማድረግ በዚህ ቀን በደንብ መነጋገር ይገባል ተብሏል፡፡

አዲሱ መገናኛ ብዙሃን አዋጅ በተመለከተ ሀሳብ ያነሱት የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ አማረ አረጋዊ አዲሱ አዋጅ ይዞ የመጣው ጠቀሜታ ብዙ ቢሆንም የዛን ያክል አዋጁን ተፈፃሚ ለማድረግ ችግር እየገጠመ ነው ብለዋል፡፡ሚዛናዊና እውነተኛ ዘገባ፣ የጋዜጠኛው ከስጋት ነፃ ሆኖ ስራውን መስራትና የህዝቡን እውነተኛ መረጃ የማግኘት መብትን በተመለከተ ሁሉንም አቻችሎ የመሄድ አስፈላጊነትን አንስተው በማብራሪያ አቅርበዋል፡፡

ዛሬም የሚዲያ ነፃነት ጉዳይ አደጋ ውስጥ ስለመሆኑ ማብራሪያ ያቀረቡት ደግሞ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽነሩ ዶ/ር ዳንኤል በቀለ ናቸው፡፡መሻሻል አሳይቶ የነበረው ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ መልሶ አደጋ ውስጥ ገብቷል ብለዋል፡፡አዲሱ የመገናኛ ብዙሃን አዋጅ በርከት ያሉ ሊጠቀሱ የሚችሉ በጎ ጎኖች ቢኖሩትም አሁንም ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ መሆን አልቻለም ብለዋል፡፡

አዋጁ የቅድመ ክስ እስርን የሚከለክል ቢሆንም አሁንም በቀጥታ ክስ ከማቅረብ ይልቅ የቅድመ ክስ እስር ተደጋግሞ እየታየ ነው ብለዋል፡፡በአሁኑ ሰዓትም በተለያየ ወንጀል ተጠርጥረዋል የተባሉ ቢያንስ 8 የሚዲያ ሰራተኞች በስር ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ዶ/ር ዳንኤል የመገናኛ ብዙሃን ነፃነትን የማንሳቱን ያክል መገናኛ ብዙሃኑ ያለባቸውን ግዴታ አብሮ ማንሳት ተገቢ ስለመሆኑ አብራርተዋል፡፡

የሚዲያ ነፃነት ገደብ የሌለው መብት አለመሆኑ ማወቅና መብትን ከግዴታ ጋር አቻችሎ መስራት ያስፈልጋል ሲሉ ተናግረዋል፡፡በፕሬስ ነፃነት ቀኑ ላይ ጋዜጠኞች መረጃ ለማግኘት እየገጠማቸው ስላለው ችግርና ሌሎች ሀሳቦች ተነስቷል፡፡ፍርሃትና ምን ይገጥመኝ ይሆን በሚል ስጋት ውስጥ ሆኖ መስራት የመገናኛ ብዙሃኑ እና የጋዜጠኞቹ ፈተና ነው ተብሏል፡፡

የአለም የፕሬስ ነፃነት ቀን የተባበሩት መንግስታት የትምህርት ፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት አማካኝነት ሁሌም ሚያዚያ 25 ቀን እንዲከበር የተወሰነው ከ31 ዓመት በፊት በናሚቢያ ዊንዶ ኦክ የተካሄደውን ጉባኤ ተከትሎ ነው፡፡የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ምክር ቤት እለቱን የተመከተውን ጉባኤ ከዩኔስኮ ካርድ ከተባለ ተቋምና ከሌሎችም ጋር በመሆን ያሰናዳው መሆኑን ተናግረዋል፡፡ዛሬ ይፋ በተደረገው የመገናኛ ብዙሃን ነፃነት የአለም አገራት ደረጃ ኢትዮጵያ ከ180 አገራት 130ኛ ደረጃ መያዟን ይፋ ተደርጓል፡፡

[Sheger FM]

@esatchannal
4.1K viewsedited  12:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-03 13:29:33
#Update

" ውይይቱ በአብዛኛው በአዎንታዊ መልኩ የተከናወነ ቢሆንም በአንዳንድ ጉዳዮች ላይ በዚህኛው የውይይት ስምምነት ላይ አልተደረሰም " - መንግሥት

በታንዛኒያ ሲካሄድ የቆየው የሰላም ውይይት የመጀመሪያ ምዕራፍ ዛሬ ተጠናቀቀ።

በኦሮሚያ ክልል ያለውን ግጭት በማስወገድ ሰላምን ለማምጣት ያለመውና በታንዛኒያ ሲካሄድ የቆየው የሰላም ውይይት የመጀመሪያ ምዕራፍ ዛሬ መጠናቀቁን መንግሥት አሳውቋል።

ውይይቱ በምን በምን ጉዳዮች ላይ እንደነበር በዝርዝር ያልገለፀው መንግሥት " ውይይቱ በአብዛኛው በአዎንታዊ መልኩ የተከናወነ ቢሆንም በአንዳንድ ጉዳዮች ላይ ግን በዚህኛው የውይይት ምዕራፍ ስምምነት ላይ ለመድረስ አልተቻለም " ብሏል፡፡

" መግባባት ላይ አልተደረሰባቸውም " የተባሉ ጉዳዮችንም መንግሥት በግልፅ አላሳወቀም።

ግጭቱን በዘላቂነትና ሰላማዊ በሆነ መንገድ ለማስቆም እንዲቻል ግን ሁለቱም አካላት የሰላም ውይይቱን መቀጠል አስፈላጊ መሆኑ ላይ ተግባብተዋል ተብሏል።

መንግሥት በኢትዮጵያ ሕገ መንግሥትና እስካሁን ሲመራባቸው በነበሩ መሠረታዊ መርሖች መሠረት ግጭቱን በሰላማዊ መልኩ ለመፍታት መንግስት የጸና አቋም እንዳለው አረጋግጧል።

መንግሥት " ኦነግ ሸኔ " እያለ የሚጠራው ታጣቂው የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት የሰላም ውይይቱን በተመለከተ የሚሰጠውን ማብራሪያ ተከታትለን እናሳውቃለን።

@esatchannal
4.2K viewsedited  10:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-03 13:25:15 በትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር የተሾሙት የወረዳ አስተዳዳሪዎችና ከንቲባዎች አዲስአበባ ውስጥ ተጠርተው ምክክር እያደረጉ ስልጠናም እየተሰጣቸው እንደሆነ ተሰምቷል
ከነዚህ ሹመኞች መካከል የወልቃይት ወረዳዎችን ሲያስተዳድሩ የነበሩ የቀድሞ የወያኔ አመራሮች መታየታቸው ተሰምቷል። ለአብነት ያህል ሀርመኒ ሆቴል አካባቢ መታየታቸውን የአዩዘሀበሻ
ምንጮች ገልፀዋል#አዩዘሀበሻ።
ሚያዝያ 25/2015 ዓ.ም
=======≠========
ለተጨማሪ መረጃዎች ቻናላችንን join ያድርጉ፣መረጃ ለሚፈልጉ ለሌሎች ጋብዙ
@esatchannal
3.9K viewsedited  10:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-03 12:51:54 ደብረሲና
በደብረሲና ከተማ ሾላሜዳ አካባቢ በከባድ መሳሪያ የታገዘ የተኩስ ልውውጥ እየተካሄደ ይገኛል#አዩዘሀበሻ።
ሚያዝያ 25/2015 ዓ.ም
=======≠========
ለተጨማሪ መረጃዎች ቻናላችንን join ያድርጉ፣መረጃ ለሚፈልጉ ለሌሎች ጋብዙ
@esatchannal
3.9K views09:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-03 12:51:54 የሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደር ያስተላለፈው መልዕክት
1ኛ.በከተማችን የሚገኘው የጸጥታ መዋቅር የሀገር መከላከያ ሰራዊት
በመሆኑ የከተማችን ህዝብ ተረጋግቶ መደበኛ ህይወቱን እንዲመራ እንጠይቃለን

2ኛ. የሸዋሮቢትና አካባቢውን ህዝብ ትጥቅ ለማስፈታት ታስቧል በሚል የሚወራው ወሬ መሰረተ ቢስ በመሆኑ ህብረተሰቡ እንዲረጋጋ ለህዝባችን ማሳሰብ እንፈልጋለን

3ኛ. የከተማችንን ሰላምና ደህንነት እንዲሁም የህዝቡን እንቅስቃሴ የሚያውክ ማንኛውንም እንቅስቃሴ ባለማድረግ ባለመተባበር ህዝባችንን
ከጥፋት እንከላከል ሲል የሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደር ጊዜያዊ ኮማንድ ፓስት መልእክቱን አስተላልፏል።
የሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደር
ሚያዝያ 25/2015 ዓ.ም
=======≠========
ለተጨማሪ መረጃዎች ቻናላችንን join ያድርጉ፣መረጃ ለሚፈልጉ ለሌሎች ጋብዙ
@esatchannal
3.9K views09:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ