Get Mystery Box with random crypto!

ኢሳት(ትኩስ ትኩስ ዜናዎች)

የቴሌግራም ቻናል አርማ esatchannal — ኢሳት(ትኩስ ትኩስ ዜናዎች)
የቴሌግራም ቻናል አርማ esatchannal — ኢሳት(ትኩስ ትኩስ ዜናዎች)
የሰርጥ አድራሻ: @esatchannal
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 24.98K
የሰርጥ መግለጫ

አዳዲስ ወሬዎችን ዜናዎችን ማግኝት ከፈለጉ እኛን ይቀላቀሉ ለወዳጅ ዘመዶ #share

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 140

2022-07-16 09:54:54 በ18ኛው የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የመጀመሪያ ቀን ማጣሪያ ውድድሮች ሁሉም ተሳታፊ ኢትዮጵያዊያን ለቀጣይ ዙር አለፉ

በኦሬገኑ 18ኛው የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የመጀመሪያ ቀን ማጣሪያ ውድድሮች ሁሉም ኢትዮጵያዊያን ተሳታፊዎች አመርቂ ውጤት በማስመዝገብ ለቀጣይ ዙር አልፈዋል

አትሌቶቹ ወደቀጣይ ዙር ያለፉባቸው ዘርፎች በወንዶች በ3 ሜትር መሠናል እና በሴቶች የ1500 ሜትር ውድድሮች የተሳፉ 6ቱ አትሌቶች ናቸው።

በዚሁ መሰረት
በ3ሺ መሠናክል ወንዶች

ጌትነት ዋለ 8:17.49
ለሜቻ ግርማ 8:19.64
ኃ/ማርያም አማረ 8:18.34

በ1,500 ሜትር ሴቶች
ሂሩት መሸሻ 4:07.05
ፍሬወይኒ ኃይሉ 4:04.85
ጉዳፍ ፀጋይ 4:02.68 በማስመዝገብ ለቀጣይ ዙር አልፈዋል፡፡

@Esatchannal
663 viewsedited  06:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-16 03:34:00 7-12 ኛ ክፍል ላላችሁ ተማሪዎች በሙሉ የክረምት የኦላይን ትምህርት በክፍያ መልኩ መማር ማጥናት የምትፈልጉ ተመዝግባችሁ መማር የምትችሉ መሆኑን እናሳዉቃለን
ለመመዝገብ ስም ክፍል አድራሻ ስልክ ቁጥር በመፃፍ @sms1850 በመጫን መላክ ይኖርባችሆል።
@sms1850

@sms1850
የሚሰጡ ትምህርቶች
maths physics chemistry

ለበለጠ መረጃ 0932661848
1.0K views00:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-15 14:43:30 በም/ቤቱ እራሳቸውን የተከላከሉት ዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱ !

" እኔ መጀመሪያ ማንሳት የምፈልገው ፤ መጀመሪያ ከግል ስብእናዬ መነሳት ፈልጋለሁ እኔ እስከማስበው ድረስ ምስኪኑ ህዝብ ቆጥቦ ቤት እንዲያገኝ ነው ፍላጎቴ ፤ ይሄ ከነበረኝ ስብእና እንፃር ሙስና የሚለው የሚገልፀኝ አይደለም።

ነገር ግን ድርጊቱ ተደርጎ ከሆነ እኔም አዝኛለሁ፤ ይሄም ጥልቅ የሆነ ምርመራ ተደርጎ ነገ ሁላችንም የምናየው ይሆናል።

ወደ ዋናው ሀሳቤ ስሄድ የአመራር ሚና ምድነው እኔ የቢሮ ኃላፊነ ነኝ፣ በተለይ የቢሮ ኃላፊ ስሆን አጠቃላይ strategic የሆነ direction ነው የምሰጠው።

እነዚህ የ routine የሆኑ ስራዎች ላይ ስራዎችን አልሰጥም። ነገር ግን በዚህ ሂደት ማየት የሚገባኝን የአመራር ክፍተቶችን እወስዳለሁ። እሱን የምክደው አይደለም።

እኔ በ Presentation ላይ በኢንሳ ተረጋገጠ አላልኩም። የቪድዮ ቅጂ ስላለ እሱን ማየት ይቻላል። ነገር ግን እንዴት ነበር የሚለውን ለዚህ ምክር ቤት ለታሪክ መቅረት ስላለበት ማቅረብ ይገባኛል።

መጀመሪያ ለዕጣው ዝግጁ ስናደርገው ከ9 ወር በፊት ነው ይሄ ስራ ያተጀመረው ይሄ ስራ ከተጀመረ በኃላ መጀመሪያ የተደረገው ለኢኖቬሽን ... እ "

የምክር ቤቱ አፈጉባኤ ወ/ሮ ሱፌና አልከድር ፦

" የተከበሩ ዶ/ር ሙልቀን ... በሂደቱ ላይ ሳይሆን "

ዶ/ር ሙሉቀን ፦

" አይደለም ሀሳቤን ... "

የም/ቤቱ አፈጉባኤ፦

" በቀረበው ላይ ብቻ አስተያየት ይስጡ "

ዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱ ፦

" ገብቶኛል ክብርት አፈጉባኤ ... "

የም/ቤቱ አፈ ጉባኤ ፦

" እሱን ፍርድ ቤት የማያጣራው ጉዳይ ይሆናል "

ዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱ ፦

" አይደለም፤ ይሄ ም/ቤትም... ለመደመጥም እንትን ልሁን ምክንያቱም ይሄ ምክር ቤትም ማወቅ የሚገባውን አካሄዱን ማወቅ ስለሚገባው ስላለበት ነው መናገር ያለብኝ ።

ስለዚህ በሂደቱ አስተያየት መስጠት ያለብኝ በዚህ መልክ ነው።

ሎተሪው ዕጣ ከመውጣቱ በፊት 2 ደብዳቤ በህዳር 17 /2014 በአብርሃም ተፈርሞ ለኢኖቬሽን ሚኒስቴር እና ለኢንሳ የሞያዊ ድጋፍ ኣስፈላጊድን እንድታደርጉ ብለን ፅፈናል።

የኢኖቬሽን ሚኒስቴር በታህሳስ 26/2014 በደብዳቤ ምክረ ሀሳብ ሰጥቶናል። ከዛ በምክረ ሀሳቡ መሰረት የሚስተካከለውን አስተካክለናል። ኢንሳን በተመለከተ ግን ምንም አይነት ነጥብ አልሰጠንም personally እንደውም ዶ/ር ሹመቴን አግኝቼ ለማውራት እባክህን...ክብርት ያስሚንም ስላለች ክብርት ያስሚንም ደውላለት እንደውም ፍቃደኛ ያልሆነበት ሁኔታ ነበር የነበረው። ዕጣው ከመውጣቱ በፊት የነበረው ሂደት ይሄው ነው።

ሰኔ 21 ቀን 2014 በአቶ ሽመልስ የተፃፈ ደብዳቤ ተወካይ ይመደብልን በተባለው ሰዓት ..."

የም/ቤቱ አፈጉባኤ፦

" በጣም ያሳጥሩልን "

ዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱ ፦

" አሳጥራለሁ ግን ካልተሰማሁ at least ይሄ ምክር ቤት ይስማኝ ካዛ በኃላ ችግር የለውም ሌላውን ነገር ..."

የም/ቤቱ አፈጉባኤ፦

" ማለት ይሄ የተከበረው ምክር ቤት ይሄንን ከማጣራት ስልጣን የለውም፤ የማጣራት ስልጣን ያለው ፍትህ ሚኒስቴር ነው "

ዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱ ፦

" ለታሪክ መቀመጥ ስላለበት እኔ ከግል ስብእናዬ ከከፈልኩት የፖለቲካ ዋጋ ካለኝ ነገር ይሄ ምክር ቤት understand አድርጎ ለታሪክ መቀመጥ ስላለበት ነው። ይሄን መናገር የፈለኩት።

ከይቅርታ ጋር ክብርት አፈጉባኤ ባያቋርጡኝ ብቀጥል። አጭር አጭር አድርጌ ልግለፅ።

ስለዚህ ሰኔ 21 ቀን በአቶ ሽመልስ በተፃፈው ደብዳቤ የዘርፉ ምክትል ኃላፊ ለሆኑት ለአቶ አብርሃም ደርሷቸዋል። "

የም/ቤቱ አፈጉባኤ፦

" አሁንም ላስቆሞት ነው። አልፈቅድም። ሁሉንም ዝርዝር እንዳያቀርቡልን አልፈቅድም "

ዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱ ፦

" አጭር ነው ፤ ሀሳቤን ወይም ደቂቃ ይስጡኝና... "

የም/ቤቱ አፈ ጉባኤ፦

" ሀሳቡን አጭር አድርገው፣ የሚቃወሙትን ነገር ላይ ብቻ "

ዶ/ር ሙሉቀን ሀፍታ፦

" ክብርት አፈ ጉባኤ የምቃወመው ይሄን ሀሳቤን ገለፅኩኝ በኃላ ነው "

የም/ቤቱ አፈ ጉባኤ፦

" ለማስቆም እየተገደድኩ ነው "

ዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱ፦

" እሺ በምን ልናገር ታዲያ ? "

የም/ቤቱ አፈጉባኤ፦

" በጣም በማሳጠር "

ዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱ ፦

" እሺ፣ ችግር የለውም ! በጣም አሳጥራለሁ። የምክር ቤት አባላትን በጣም ይቅርታ ጠይቃለሁ። ማወቅ ስላለባችሁ ነው።

ሰኔ 21 ቀን በአቶ ሽመልስ የተፃፈው ደብዳቤ እኔ ሰኔ 21 ምናልባት በጊዜው አልነበርኩም በባለቤቴ ወሊድ ምክንያት በዚህ ሰዓት ዳታ ሲቀበሉ፣ እንዲህ ያለውን ደብዳቤ ሲፃፃፉም በጊዜው አልነበርኩም።

የኔ ምክትል የነበረው ግን ይሄንን ዳብዳቤ ተቀብሎ ባለሞያ ወክልሉልን ባለን መሰረት ለሶፍትዌር ዳይሬክተር ባለሞያ እንዲወክል ፅፏል።

ከዛም በድጋሚ አቶ ሽመልስ ሰኔ 21 የቤት መረጃ ለቢሯቹ የላክን መሆኑን ይላል። እዚህ ጋር አቶ ሽመልስ አጠቃላይ የቤት ምዝገባ ያተደረጉበትን፣ ዕጣ የሚወጣባቸውን አቶ ሽመልስ ልኳል።

እኔ በዛ ሰዓት ስላልነበርኩ ምክትሌ አቶ አብርሃም አሁንም ይሄንን ለሶፍትዌር ዳይሬክተሮች መርቶ ወደባለሞያው የገባበት ሁኔታ አለ።

ለምን ይሄን አነሳሁኝ ለሚለው ሁለት ነገር ነው።

አንደኛው ዕጣ ከመውጣቱ በፊት ክብርት ያስሚንም እንደውም እኔ አልነበርኩም ክብርት ያስሚን የእኔ ምክትል ቢሮ ኃላፊዎች ይዛ ቢሯችን መጥታ እዛ ስላልነበርኩኝ ያለውን ነገር ውይይት አድርጋ ሲስተሙ እንዴት ነበር ተብሎ display ተደርጎ ነበር እሱ በማየት ደረጃ እሳቸውም ስላሉ ይገልፁታል።

ሌላው ከ4 በላይ ሙከራ ተደርጓል የተባለው ምናልባት ክብርት ከንቲባ ባሉበት ሙከራ አድርገናል። ከዛም በኃላ ይሄ ኮምፒዩተር እኛ አዲስ ብለን ነው የሰጠነው። እንግዲህ ይሄ too በጣም technical እኔ የተማርኩት በሰላምና ደህንነት more of social science ነው። እኔ strategically በሆነ way ነው እንጂ መሥጠት ያለብኝ ምን አይነት algorithm ተጠቅሟል፣ behind የሰራውን ምን አይነት ሶፍትዌር ይጫን የሚልውን ነገር እኔ አላውቀውም።

ነገር ግን ይሄ ኮምፒዩተር አዲስ ነው። ከግዢ የሰጠነው ነው። ሰጠን ባለሞያው ይጠቀምበት ይሄን ያድርግበት እኔ እንደ አመራርነቴ ወርጄ የማየት role አለኝ ብዬ አላስብም።

ዕጣው ከመውጣቱ ለፊት ማታ ታሸገ፣ ከታሸገ በኃላ ታዛቢ ባለበት ታሸገ፣ ምንም ዳታ እንደሌለው ታይቶ ታሸገ። እኔ ኮምፒዩተሩ ጋርም ቀርቤ አላውቅም። ከዛ በነገታው መጡ ክብርት ያስሚን ባለችበት ሌላም ታዛቢ ባለበት በሩ ተከፍቶ ተገባ ካዛ ኮምፒዩተሩ ታየ ከዛም ክብርት ከንቲባ ባለችበት ያሬድ የሚባል ባለሞያ በቴክኖሎጂ የታወቀ ነው እሱ ይየው ተብሎ መጣ ያሬድ የሚባለው ሰውዬ ክሊክ አድርጎ ያለውን ነገር ጠቅላላ አየ መሄድ ይችላል ብሎ እዛው confirmation ሰጠን ምክንያቱም ክብርት ያስሚንም ስላሉ በዚህ መሰረት ወደ እጣው መጣ።

ወደ ዕጣው ሢመጣ presentation ተዘጋጀ፣ ከዛም ለቢሮው ይመጥናል አንተ ብታቀርበው ተብዬ እንዳቀርብ ተደረገ፤ ከዛ ውጭ Presentation ላይ ያቀረብኩት ደግሞ አንዱ ነገር ጠቅላላ የተሰጠኝን ሀሳብ ነው።

ለምሳሌ ከታች ባለሞያ አለ ከባለሞያው በላይ ዳይሬክተር አለ፣ ከዳይሬክተር በኃላ..."

ዶ/ር ሙሉቀን ይህንን እየተናገሩ እያሉ በቀጥታ በአዲስ ቴሌቪዥን ለህዝብ ሲሰራጭ የነበረው ንግግር ተቋርጧል። በኃላም ያለመከሰስ ማብታቸው ተነስቷል።

@esatchannal
1.8K viewsedited  11:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-15 14:43:30
1.5K viewsedited  11:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-15 14:43:30 #የጋራ_መኖሪያ_ቤቶች #ፍትህሚኒስቴር

ፍትህ ሚኒስቴር ለአዲስ አበባ ምክር ቤት በፃፈው ደብዳቤ ላይ (ከዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱ ያለመከሰስ መብት መነሳት ጋር የተያያዘ) ፦

" ... ዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱ ምሩፅ ለከተማ አስተዳደሩ አመራሮች ቀርበው በሰጡት መግላጫ እንዲሁም በእጣ አወጣጥ ስነስርዓቱ ላይ ለህዝብ በይፋ በሰጡት ማብራሪያ ቢሮው በአዋጅ በተሰጠው ኃላፊነት መሰረት ቴክኖሎጂውን አልምቶ የጨረሰ በመሆኑ ቴክኖሎጂው ከሰው ንክኪ ነፃ በመሆኑና በኢንሳ በኩል ተፈትሾ ማረጋገጫ ያገኘ እንዲሁም ለዕጣው አወጣጥ ከባንክ የተላከው ዳታ በአግባቡ የተጫነ መሆኑ ማረጋገጫ ሰጥተው ነበር።

መስተዳደሩም የኃላፊውን ማረጋገጫ በመቀበል እና በማመን ዕጣው ሐምሌ 1 በህዝብ ፊት እንዲወጣ አድርጎ የነበረ ቢሆንም ከተሰጠው ማረጋገጫ በተቃራኒ ከፍተኛ ከፍተኛ የሆነ የዳታ ማጭበርበር ተግባር የተፈፀመ መሆኑ አመላካች መረጃ በማግኘት ኦዲት እንዲደረግ አቅጣጫ ተሰጥቶ እንዲፈተሽ ተደርጓል።

በዚህ መሰረት ከኢንሳ ፣ ከብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት እና ከኢኖቬሽን ሚኒስቴር በተዋቀረው የባለሞያ ቡድን በተደረገው ማጣራት ፦

1ኛ. ሲስተሙ አዲስ እና የገባው ዳታ በማንም ያልታየ ለመሆኑ ለከተማው አመራር ጭምር በኃላፊው ማረጋገጫ የተሰጠ ቢሆንም ዕጣው ከመውጣቱ በፊት ወደ ኮምፒዩተሩ የገባውን ዳታ ለአምስት ጊዜ የተመለከቱ መሆኑ፤

2ኛ. ለዕጣ ብቁ ናቸው ተብሎ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከተላከው 79 ሺህ ተመዝጋቢዎች በላይ ለዕጣው ብቁ ያልሆኑ 73 ሺህ ሰዎችን በድብቅ ወደ ኮምፒዩተሩ በመጫን የተጠቃሚዎችን ቁጥር ወደ 172 ሺህ እንዲያድግ ያደረጉ መሆኑ፤

3ኛ. ኃላፊው ከቤቶች ልማት የተላከውን የተወዳዳሪዎችን መረጃ ለሚያስገባ ባለሞያ ሚስጢራዊነቱን ጠብቆ እንዲሰራ ማድረግ ሲገባቸው በቀጥታ ለአልሚው በመስጠት የዳታ ማጭበርበሩ እንዲፈፀም ያስደረጉ መሆኑ፤

4ኛ. ሲስተሙ የማልማት ተግባሩ አለም አቀፍ ስታንዳርዱን ያልጠበቀና የሚና መደበላለቅ የታየበት በተለይም ሶስቱን አካላት አልሚውን፣ የተጠቃሚውን እና አረጋጋጩን አካላት የሚና ክፍፍል የሌለበት እና ሁሉም በአንድ ሰው ማለትም በአልሚው ብቻ የተሰራ በመሆኑ አሁን ለተከሰተው ማጭበርበር በር እንዲከፍት ያደረገ መሆኑ፤

5ኛ. ዳታው የተጫነበት ኮምፒዩተር አዲስ እና የዳታ አጠቃቀሙን ከእጅ ንክኪ ነፃ እንዲሆን የሚፈልግ የነበረ ቢሆንም ነገር ግን ኮምፒዩተሩ ለስራው የማይፈለግ ባዕድ ሶፍትዌር ጭምር የተጫነበት ከመሆኑ በላይ የዕጣ አወጣጥ ሂደቱን በኦንላይን ጭምር እንዲከታተሉ የሚያስችል የነበረ መሆኑ ፤

6ኛ. ስለደህንነቱ ምንም አይነት ፍተሻ ባልተደረገበት ቴክኖሎጂ በኢንሳ ተፈትሾ ችግር እንደሌለበት ማረጋገጫ የተሰጠበት ነው በሚል የተሳሳተ መረጃ በማቅረብ የከተማ አስታዳደር አመራሩን በማሳሳት ዕጣ እንዲወጣ ያስደረጉ መሆናቸውን ማረጋገጥ ተችሏል።

በአጠቃላይ ዕጣውን ለማውጣት ጥቅም ላይ የዋለው ቴክኖሎጂ ወይም ሲስተም የአሰራር ስርዓቱን ያልተከተለ፣ አግባብ ባለው ተቋም ያልታየና ምንም አይነት የደህንነት ማረጋገጫ ያልተሰጠበት፣ ለማጭበርበር የሚረዳ ባዕድ ሶፍትዌር የተጫነበት ፣ ለዕጣው ብቁ ናቸው ተብሎ ከሚመለከተው አካል ተረጋግጦ ከተላከው ዳታ ውጭ ሌላ ዳታ ማስገባት መረጃ መጨመር፣ ማጥፋት እንዲሁም ማስተካከል የሚያስችል እድል ለአልሚው በድብቅ የሚሰጥ ስለመሆኑ ማረጋገጥ ተችሏል።

ድርጊቱ በቢሮው ኃላፊ እና በስሩ የተሳተፉት ሌሎች ግለሰቦች የተፈፀመ መሆኑ ተረጋግጦ አብዛኛዎቹ በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን የወንጀል ምርመራ እየተደረገ ይገኛል። "

@esatchannal
1.5K viewsedited  11:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-15 12:24:40
ከምዕራብ ወለጋ ቶሌ አካባቢ የተፈናቀሉ ዜጎች ወደ ቀያቸው መመለሳቸው ተሰማ!

በምዕራብ ወለጋ ዞን ጊምቢ ወረዳ ቶሌ ቀበሌ ሰኔ 11/2014 ዓ.ም በነበረው የጸጥታ ችግር ተፈናቅለው ወደ አርጆ ጉዳቱ ከተማ የሸሹ ዜጎች ወደ ቀድሞ ቀያአቸው መመለሳቸውን የዞኑ አስተዳደር አስታወቀ። የኦሮሚያ «ቡሳ ጎኖፋ» ምዕራብ ወለጋ ቅርንጫፍ ( በቀድሞ ስሙ የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ጽ/ቤት) ኃላፊ ወ/ሮ ነጻነት ዓለማየሁ በወቅቱ ተፈናቅለው በአርጆ ጉደቱ ተጠልለው የነበሩ ሁሉም ሰዎች ወደ ቀያአቸው መመለሳቸውን ገልጸዋል፡፡መኖሪያ ቤታቸው ለተቃጠለባቸው 96 ነዋሪዎችም ለጊዜያዊ መጠለያ የሚሆን ሸራዎች መዳረሱንም ጠቁሟል፡፡በቶሌ ቀበሌ የሚገኙ ዶይቸ ቨለ ያነጋገራቸው ነዋሪዎችም ሰብአዊ ድጋፍ እንደ ደረሳቸው ገልጸው በአካባቢው አሁንም የጸጥታ ስጋት መኖሩን ተናግረዋል። በርካታ ሰዎች ደግሞ በጸጥታ ችግሩ ስጋት ወደ ወሎ ሀርቡ የሚባል ስፍራ መሄዳቸውንም ገልጸዋል።

ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ: https://p.dw.com/p/4E7eb

@esatchannal
1.5K viewsedited  09:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-15 12:22:15
1.4K viewsedited  09:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-15 12:22:15
1.4K viewsedited  09:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-15 12:22:15
1.5K viewsedited  09:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-14 17:52:11
በካሚላት መህዲ ላይ አሲድ የደፋው ግለሰብ ከ30 በላይ ሴቶችን በማጭበርበር ተጠርጥሮ በቁጥጥር ስር ዋለ!

ከ13 ዓመታት በፊት በካሚላት መህዲ ላይ አሲድ ደፍቶ የግድያ ሙከራ ወንጀል በመፈፀም የሞት ፍርድ ተፈርዶበት በማረሚያ ለ12 ዓመታት ቆይቶ በምህረት የተፈታው ደምሰው ዘሪሁን የማነ፤ አሁን ደግሞ ከ30 በላይ ሴቶችን ገንዘብ በማጭበርበር ወንጀል ተከሶ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውሏል።

ከ13 ዓመታት በፊት በፍቅረኛው ካሚላት መህዲ ላይ አሲድ በመድፋቱ በጥር 21 ቀን 2000 ዓ.ም በተከሰሰበት የግድያ ሙከራ ወንጀል በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሞት ቅጣት የተላለፈበት ደምሰው ዘሪሁን የማነ የተባለው ወይም ራሱን ሳምሶን እያለ የሚጠራው ተጠርጣሪ በወቅቱ ቅጣቱ ወደ የዕድሜልክ እስራት ተሻሽሎለት ማረሚያ ቤት ቢወርድም 12 ዓመት ከ7 ወራት እንደታሰረ እስራቱን ሳይጨርስ በይቅርታ ተለቋል።

ተጠርጣሪው ውሎ ሳያድር በተለያዩ ወንጀሎች ተከሶ ድጋሚ ታስሮ ስለመለቀቁም የፌደራል ፖሊስ ምርመራ ያመለክታል።

ከዚያ በኋላም ተጠርጣሪው ከ30 በላይ ሴቶችን ገንዘብ በማጭበርበር ወንጀል ተከሶ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውሏል፤ ለአብነትም ነዋሪነቷን በሀገረ ጀርመን አድርጋ ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት በኮንስትራክሽን ዘርፍ በኢንቨስትመንት በተሰማራችው መሐሪት ክፍሌ ላይ ከባድ የማታለል ወንጀል ስለመፈፀሙ ነው ፖሊስ ያስረዳው።

Via EBC
@esatchannal
2.0K viewsedited  14:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ