የሰርጥ አድራሻ:
ምድቦች:
ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች:
6.83K
የሰርጥ መግለጫ
አለም አቀፋዊ መረጃዎች ምልከታዎችና ታሪካዊ ክስተቶች ይቀርቡበታል
Ratings & Reviews
Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.
5 stars
1
4 stars
0
3 stars
1
2 stars
1
1 stars
0
የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች
2022-09-01 20:01:31
የህወሀት ጦር በመከላከያ ሀይላችን አይቀጡ ቅጣት ሲቀጣና ፍፁም ባላሰበው አጭር ጊዜ ውስጡ ጦሩ ሲረግፍ የኢትዮጵያ ጦር ብቻውን አሸነፈኝ ላለማለት የኤርትራ ጦር አብሮ እየወጋኝ ነው በማለት እያለቃቀሰ ነው ።
ህወሀት ይህን የሚያደርገው ለሁለት ምክንያት ነው ።
1 እየተሸነፍን ያለነው በመከላከያ ሰራዊት ብቻ በኤርትራም ጭምር ታግዞ ነው በሚል ህዝቡን ለመደለል
2 የምእሬባዊያን ሜእቀብ ሰለባ የሆነቻዋን ኤርትራን ወደ ጦርነቱ ለመሳብና ምእራባውያን የበለጠ ጫና በኢትዮጵያ ላይ እንዲፈጥሩ ለማድረግ እንድሁም ወጊያውን ቀጠናዊ ለማድረግ ነው ።
አሜሪካና የአውሮፓ ህብረት ከኢትዮጵያ ጋር ያላቸውን ግንኙነት ለማሻሻል ካቀረቧቸው ቅድመመስፈርቶች አንዱ የኤርትራ ጦር ከትግራይ ይውጣ የሚል ልቦለድ ነው ። እናም ህወሀት ኤርትራ ኤርትራ የሚለው ለላኪዎቹ ሌላ የፕሮፓጋንዳ ግብአት ለማቅረብ ነው ።
ያም አለ ይህ አሁን ህወሀት እየደረሰበት ያለው ምት ከእስካሁኑ የከፋበት ሆኗል ። መከላከያ ሀይላችን ህወሃትን 360 ዲግሪ አቦ ያጠቃል ። ባንዳዎቹ እንኳንስ ማሸነፍ ማምለጫም የላቸው !
#Seid_Mohammed_Alhabeshiy
ቴሌግራም
t.me/Seidsocial
981 views17:01
2022-08-31 22:49:44
ፓኪስታን በታሪኳ አይታው የማታውቀው የጎርፍ መጥለቅለቅ አጋጥሟታል ። የጎርፉ አደጋ አብዛኛውን የሀገሪቱ ክፍል ያካለለ ሲሆን በሚሊዮን የሚቆጠሩ ህዝቦችን መውጫ መግቢያ አሳጥቶ የበርካቶችን ህይወት እየቀጠፈ ነው ።
እስካሁን ከ 1,100 በላይ ፓኪስታናዊያን ህይወታቸው አልፏል ። ከ ግማሽ ሚሊዮን ህዝብ በላይ ተፈናቅሏል ። በርካታ ከተሞች ከነ ህንፃዎቻቼው በጎርፉ ሰጥመዋል ።
ይህ ከባድ ዝናብ ያስከተለው ጎርፍ በፓኪስታን 100 ኪሎሜትር ሀይቅ መፍጠር ችሏል ። ጎርፉን ለማምለጥ ወላጆች ህፃናት ልጆቻቼውን ልጆች አዛውንት ወላጆቻቼውን ይዘው ሲታገሉ ሲታይ በጣም ያሳዝናል ።
ለህዝቧ በአደጋ ጊዜ በፍጥነት መድረስ የሚያስችል አቅም ያልገነባችው ፓኪስታን ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ የእርዳታ ጥሪ አቅርባለች ።
የፓኪስታን ወንድሞቻችንን አላህ ከዚህ መከራ በቃችሁ ይበላቸው !
#Seid_Mohammed_Alhabeshiy
ቴሌግራም
t.me/Seidsocial
665 views19:49
2022-08-31 19:59:48
እስካሁን የመከላከያ ሰራዊታችን የማጥቃት ትእዛዝ አልተሰጠውም የተሰጠው የመከላከል ትእዛዝ ብቻ ነው ።
ማጥቃት ሲጀምር ግን የሚጀምረው ከወሎ ወይንም ከጎንደር እንዳይመስላችሁ ። ነገሩ ወዲያ ነው !
መከላከያችን ከኤርትራ በኩል ቆርጦ ወራሪውን ሀይል እየጠረገ ከስሩ ሊመነግል ዝግጅቱን ጨርሷል ። አቅጣጫና እቅዱን አጠናቋል ።
ይህንን ህወሃቶችም ተረድተው ብርድ ብርድ እያላቸው ፍርሀት እያንዘፈዘፋቸው ነው ። ዛሬ የትግራይ ጦር አዛዥ ጀኔራል ታደሰ ወረደ በዚህ ጉዳይ ላይ መግለጫ ሲሰጥ መናገር እስኪያቅተው ድረስ ይርበተበት ነበር ። " እኛ እንደዚህ ይሆናል ብለን በፍፁም አልጠበቅንም ነበር " ብሏል ባን*ዳው ጀኔራል ።
የመከላከያ ሰራዊታችን እቅድ ዝግጅት እጅግ እጅግ የሚገርም ነው ። መንግስታችን በአስር ሺህ የሚቆጠር በርካታ ክፍለጦር ወደ ኤርትራ አስገብቶ በተጠንቀቅ ማቆሙን ህወሀት የተረዳው ከረፈደ በመሆኑ አስደንግጧቸዋል ።
ነገሩ አይጥ ስትጠግብ የድመት አፍንጫ ታሸታለች ነውና የህወሀት ጉሮሮ የሚበ*ጠስበት ጊዜ ሩቅ የሚሆን አይመስልም !
ኢትዮጵያ ግን ታሸንፋለች !!!!
#Seid_Mohammed_Alhabeshiy
ቴሌግራም
t.me/Seidsocial
1.3K views16:59
2022-08-30 18:12:58
ወራሪን ማራኪዎቹ !!
እውነተኛ አርበኝነት ያለቺው ወሎ ነው !
እውነተኛ ሀገር ወዳድነት መነሻዋም መድረሻዋም ወሎ ነው !!
የአርሶአደሩ ጀኔራል ሀሰን ከረሙ ጦር ወሎን ሊወር ሊያዋርድ የመጣውን ወራሪ በርካታ ሀይል እየማረኩ ይገኛሉ ። የኔ አርበኞች እነዚህ ናቸው ! ተራራ ናቸው ! ጠላትን እንደት ማስተናገድ እንዳለባቸውም ያውቁበታል !!!
በነገራችን ላይ በአለም ላይ አርሶ አደር ጀኔራልን ያበቀለች ወሎ ብቻ ናት !
ሁሉም ወሎየ እንደነ ጀኔራል ሀሰን ከረሙ አርበኞች መሆን አለበት ። ያ ከሆነ ወራሪውን መስበር አያቅትም ።
ወሎየነት ደግነት ብቻ ሳይሆን ጀግንነትም ነው !!!
#Seid_Mohammed_Alhabeshiy
ቴሌግራም
t.me/Seidsocial
1.3K views15:12
2022-08-30 16:38:41
በምንም አይነት መልኩ ቢሆን መሰደድ መፍትሄ አይደለም ። ከስደት በሗላ ያለው የውርደት ህይወት ሞትን የሚያስመኝ ስብራት ነው ። ይህንን እነረደ ህዝብ አይተናል ።
በባለፈው የህወሀት ወረራ ወቅት የበለጠ ስቃይና መከራ ያዩት እዚያው ከወረራው ውስጥ ካሉት ይልቅ የተሰደዱት ናቸው ።
ጀግኖቻችን እየተዋደቁ ነው ። እነርሱ ከፊት እየተዋደቁ ለህይወታ ሳይሳስሱ እየተጋደሉ ከሗላ ደጀን ሆኖ ጋሻና መከታ መሆን ሲገባ መሸሽ በታሪክም የሚያስወቅስ ስህተት ነውና ከመሸሽ መታገል አልያም ባሉበት ታግሶ መቀመጥ !!!
ድል ለጥምር ጦራችን !
#Seid_Mohammed_Alhabeshiy
ቴሌግራም
t.me/Seidsocial
1.4K views13:38
2022-08-29 20:13:30
አልጀሪያ የ 1.5 ሚሊዮን ሰማእታት ሀገር ነች ። ሀገር ካለደምና አጥንት አይሰራምና አልጀሪያ ነፃነቷን ያስከበሩላት ወራሪና ባንዳዎቿን የቀበሩላት በርካታ ሚሊዮናት ጀግኖችን የታደለች ሀገር ናት ። በዚህም ከኢትዮጵያ ጋር ያመሳስላታል ።
ታዲያ መሪያችን ዶክተር አብይ አህመድ ለነዚያ ሰማእታት መታሰቢያ የአበባ ጉንጉን ማስቀመጣቸው አጋጣሚውም ትርጉሙም ትልቅ ነው ።
አልጀሪያ ሚሊዮን ጀግኖቿን ስትገብር የተዋጋቺው ከወራሪዋ ፈረንሳይ ጋር ብቻ አልነበረም ይልቁንስ ከማህፀኗ ከወጡ ተላላኪ ባን*ዳዎችም ጋር ጭምር እንጅ ። እናም ዞሮ ዞሮ አልጀሪያ ስታሸነፍ ስለርሷ የሞቱላት ስለርሷም የኖሩላት ዘልአለም በክብር ሲወሱ ይኖራሉ ።
እነዚያ ጥቅመኛ ባንዳ*ዎቿ ግን እንኳንስ አልጀሪያ ላኪያቸው ፈረንሳይ እንኳ ተፀይፋቸው የውርደት ሞትን ሞተዋል ።
ድሮስ ለባን*ዳ ከውርደት ያለፈ ምን ክብር ኖሮት ያውቅና !!
#Seid_Mohammed_Alhabeshiy
ቴሌግራም
t.me/Seidsocial
1.9K views17:13
2022-08-28 23:11:00
ወሎ የደግነት ሀገር ብቻ አይደለም የጀግንነት ሀገርም ጭምር እንጅ !!
ወሎ የገራገርነት ሀገር ብቻ አይደለም የቆራጥነት ሀገርም እንጅ !!
ወሎየነት ለሀገር ፍፁም ታማኝነት ነው !
ወሎየነት ለሀገር መስዋእትነት የመሆን አርማ ነው !
በሀገራችን ታሪክ ለዚህች ሀገር የወሎን ህዝብ ያክል ለኢትዮጵያ የተዋደቀ መስዋእትነትን የገበረ የለም ።
ይናገር አድዋ - ከ 70,000 በላይ ወሎየዎችን በደምና በአጥንት ላስቀመጠው !
ይመስክር ጣሊያን በወሎየዎች በላይ ዘለቀና መሰሎቹ የአርበኞችን ቅጣት የቀመሰው !
ወሎ የሀገር አድባር የሀገር አርማ !!
#Seid_Mohammed_Alhabeshiy
ቴሌግራም
t.me/Seidsocial
2.0K views20:11
2022-08-28 21:40:59
አንዳንድ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት የመከላከያ ሀይላችን ዋነኛ አላማ ወራሪውን ሀይል ራያ ላይ መቁረጥ አይደለም ። ከዚያ ይልቅ መከላከያ ሀይላችን ወራሪውን ሀይል ከኤርትራ በኩል ቆርጦ አጠቃላይ ትግራይን ከህወሀት ለማፅዳት የተራቀቀ እቅድ ይዞ እየተንቀሳቀሰ ነው ተብሏል ።
ከዚህ በተጨማሪ ጀግናው የመከላከያ ሰራዊታችን ከሁመራ አቅጣጫ ከማይጠብሪ አቅጣጫ ወደ ማጥቃት እንደሚገባና የወራሪውን አማተር ሰራዊት ሳንዱች ለማድረግ እየተጣደፈ ይገኛል ።
ህወሀት ከወሎ ብቻ ሳይሆን ከትግራይም የሚፀዳበት ጊዜ በጣም የተቃረበ ይመስላል ። በዚህ ዘመቻ መከላከያ ሀይላችን ከመቀሌ ያነሰ ኢላማ የለውም ።
ኢትዮጵያ ታሸንፋለች !
#Seid_Mohammed_Alhabeshiy
ቴሌግራም
t.me/Seidsocial
2.0K views18:40
2022-08-27 20:46:21
በባለፈው ጦርነት የወሎን ህዝብ ያክል መስዋዕትነት የከፈለ መከራና ስቃይ ያየ የለም ። በዚህኛውም ጦርነት የጦርነቱ አውድማ እንዲሆን የተመረጠው ወሎ ነው ። ወሎ የኢትዮጵያን መከራ እንዲሸከም የተፈጠረ እስኪመስል ድረስ እየተነባበረ ህዝባችንን እያመሰቃቀለው ነው ።
የአማራ ክልል መንግስት እንደሆነ ለወሎ ብዙም ደንታ እንደሌለው ትላንትም አይተነዋል ዛሬም እያየነው ነው ።
መሆን ያለበት የወሎ ህዝብ ማንንም ሳይጠብቅ ከመከላከያ ሀይላችን ጎን ተሰልፎ ደጀንና ጋሻ ሆኖ ወራሪውን ሀይል እስከመጨረሻ መታገል ነው ። ህዝባችን ከባለፈው ስብራት ሳያገግም ዛሬም እንደገና ሌላ ስብራት መጥቶበታል ። በመሆኑም ሳንሰበር እንታገል ።
ስንታገል ከምንከፍለው መስዋዕትነት በላይ ሳንታገል የምንከለው ዋጋ በእጅጉ ይከፋልና አሁንም ከሰራዊታችን ጎን ሆኑን እንታገል !
#Seid_Mohammed_Alhabeshiy
ቴሌግራም
t.me/Seidsocial
2.3K views17:46
2022-08-27 19:45:48
ሀገሬ ስታሸንፍ ብቻ ሳይሆን ስትሸነፍም ከጎኗ እቆማለሁ !
በድል ወቅት ሳይሆን በፈተና ወቅት ከመንግስቴ ጎን የበለጠ እሰለፋለሁ !
ደግሞም አልጠራጠርም ኢትዮጵያየ ታሸንፋለች !!!
አሸናፊነት እንጅ ሌላ ነገር የሚመጥናት ሀገር አይደለችምና !!
አንድ ሰው ስለሀገሩና ክብሩ ቢሰዋ ክብሩ ነው ቢኖርም ክብሩ ነው !
ባ*ንዳ ግን ሁሌም ወራዳ ነው ! ቢሞትም ተዋርዶ ነው ! ቢኖርም ተዋርዶ ነው ! የሀገሬ ባንዳዎችም ከዚህ የዘለለ ገጥሟቸው አያውቁም !
ሁልቀን ድል ላይገኝ ይችላል ግና የመጨረሻው ድል የኛ ይሆናል ! ደግሞም እያሸነፍን ነው !
ጠላት በሬሳየ ልረማመድና ወደ ፊት ልገስግስ ብሎ ቢመጣም ጀግኖች ልጆቻችን ከሬሳው ውስጥ ሰጥሞ እንዲቀር እያደረጉት ነው !
ኢትዮጵያ ታሸንፋለች !!!!
#Seid_Mohammed_Alhabeshiy
ቴሌግራም
t.me/Seidsocial
2.1K views16:45