Get Mystery Box with random crypto!

EBC (Ethiopian Broadcasting Corporation)

የቴሌግራም ቻናል አርማ ebcnewsnow — EBC (Ethiopian Broadcasting Corporation) E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ebcnewsnow — EBC (Ethiopian Broadcasting Corporation)
የሰርጥ አድራሻ: @ebcnewsnow
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 123.21K
የሰርጥ መግለጫ

Ethiopian Broadcasting Corporation (EBC)

Ratings & Reviews

1.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2024-04-09 23:04:08
ሙሉቀን መለሰ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ
*****************************
የቀድሞ ድምፃዊ ሙሉቀን መለሰ ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱን የድምፃዊው የቅርብ ምንጮች ለኢቢሲ ሳይበር አረጋግጠዋል።
ሙለቀን መለሰ በሚኖርበት ሀገረ አሜሪካ ነው ሕይወቱ ያለፈው::
ገና የ13 ታዳጊ ሳለ ሙዚቃን የጀመረው ድምፃዊው በ1958ዓ.ም በፈጣን ኦርኬስትራ ውስጥ ተቀላቅሎ በመግባት ለሁለት ዓመታት ያህል መስራት ችሏል።
ከእዚያ በማስከተል በ1960 ዓ.ም ወደ ፖሊስ ኦርኬስትራ ክፍል በመግባት ይበልጥ በሙዚቃ ስራው ዝናን ማትረፍ ችሎ ነበር።
በ1972 ዓ.ም ላይ ደግሞ ከዳህላክ ባንድ ጋር ተቀላቅሎ ሰርቷል፡፡ እስከ 1980ዎቹ ድረስ በነበሩት ዓመታት እጅግ ተወዳጅ የሙዚቃ ስራዎችንም መስራት ችሏል።
የአንጋፋዋ ሁለገብ ከያኒት የአለምፀሐይ ወዳጆ እና የተስፋዬ ለሜሳን ግጥምና ዜማዎች አቀንቅኗል።
ሙዚቃ በቃኝ ብሎ ራሱን ከሙዚቃው ዓለም እስካገለለበት ጊዜ ድረስ በርካታ የሙዚቃ ስራዎችን ለትውልድ አበርክቷል።
ከ1980ዎቹ በኃላ ፊቱን ወደ መንፈሳዊ ስራዎች በማዞር የመዝሙር ስራዎችን ሲሰራ ቆይቷል።
እስከ ህልፈተ ሕይወቱ ድረስ በሀገረ አሜሪካ ኑሮውን አድርጎ በእዚያው ቆይቷል።
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽንም በአንጋፋው ድምጻዊ ሙሉቀን መለሰ ህልፈት የተሰማውን ሀዘን እየገለጸ፤ ለቤተሰቦቹና ለአድናቂዎቹ መጽናናትን ይመኛል።
12.6K views20:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-08 23:23:27
የፀሐይ ግርዶሹ በርካታ የአሜሪካ ከተሞችን በእኩለ ቀን አጨልሟቸዋል
****************************

የፀሐይ ግርዶሹ በርካታ የአሜሪካ ከተሞችን በእኩለ ቀን ሙሉ በሙሉ እንዳጨለማቸው ተገልጿል፡፡

ሙሉ የጸሐይ ግርዶሹ ማዛትላን የተባለችውን የሜክሲኮ ከተማ ጨለማ አልብሷት ካለፈ በኃላ ወደ ዳላስ፣ ቴክሳስ እና ሌሎች የአሜሪካ ግዛቶች ተሸጋግሯል፡፡

በአንዳንድ የአሜሪካ ግዛቶች የጸሐይ ግርዶሹ እስከ 4 ደቂቃ መቆየቱም ተመላክቷል፡፡

የጸሐይ ግርዶሹ በሚቀጥሉት ሰዓታት ወደ ሰሜን አሜሪካ ሰሜናዊ እና ምስራቃዊ ክፍሎች እንደሚዞርም ተጠቁሟል፡፡

በሰሜን አሜሪካ ክስተቱን ለማየት በ10 ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች አደባባይ መውጣታቸውን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

ክስተቱን በልዩ ሁኔታ እየተከታተለ የሚገኘው የአሜሪካ የጠፈር ምርምር ተቋም (ናሳ) ያለ ጸሐይ መነጽር ግርዶሹን ለማየት መሞከር የዓይን ብርሃንን እስከማሳጣት የሚያደርስ የጤና ችግር ሊያስከትል እንደሚችል በማስገንዘብ ላይ ነው፡፡
12.9K views20:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-22 21:51:20
ኢትዮጵያ 6ኛውን እና 7ኛውን  ወርቅ በ5 ሺህ ሜትር እና በ1 ሺህ 500ሜትር ሴቶች ሩጫ ውድድር አገኘች
*****
በጋና እየተካሄድ ባለው 13ኛው የመላ አፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ በ5 ሺህ ሜትር ወንዶች እና በ1 ሺህ 500 ሜትር ሴቶች ሩጫ 6ኛውን እና 7ኛውን ወርቅ አግኝታለች፡፡
ለኢትዮጵያ በ5 ሺህ ሜትር ወንዶች ፍፃሜ በሚያስደምም የአጨራረስ ብቃት ወርቅ ያመጣው አትሌት ሀጎስ ገ/ሕይወት ነው።
አትሌት ሂሩት መሸሻ በ1 ሺህ 500ሜትር ሴቶች ሩጫ ውድድር የወርቅ ሜዳለያ ያስገኘች ሌላኛዋ ጀግና አትሌት ናት፡፡
አትሌት ሀዊ አበራም  የብር ሜዳሊያ በማስገኝት የአገሯን ክብር ከፍ አስደርጋለች፡፡
በ1500 ሜትር ወንዶች ፍፃሜም ሌላኛው ባለድል ኤርሚያስ ግርማ   የብር ሜዳልያ ለአገሩ አስገኝቷል፡፡https://www.facebook.com/share/p/L64tzNa5JTcbHNLn/?mibextid=qi2Omg
13.4K views18:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-11-22 19:37:50 ባለፉት 3 ወራት ዲኘሎማሲውን ወደ ከፍታ መመለስ ያስቻሉ ስራዎች መሰራታቸው ተገለፀ
**************

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የ2016 ዓ.ም የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የስራ አፈፃፀም ሪፓርት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነት እና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በዛሬው እለት ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል።

በሪፖርቱ ግንኙነትን በማጠናከር፣ የኢትዮጵያን ተሰሚነት በማሳደግ እና ሚዛናዊ አቋም እንዲያዝ በማድረግ፣ የኢንቨስትመንት ፍሰትን በማሳደግና በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ያሉ ዜጎችን ከውጭ በመመለስ ዲፕሎማሲው ውጤታማ እንደነበር ተነስቷል።

ባለፉት ሶስት ወራት በጎረቤት ሃገራት ከ11 በላይ ጉብኝቶችን በማድረግ ግንኙነትን የማጠናከር ስራዎች ተሰርተዋል ነው የተባለው።

https://ebc.et/newsdetails.aspx?newsid=4267
12.9K views16:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-11-22 14:21:08
የሚኒስትሮች ምክር ቤት የ100 ቀናት ግምገማ ሁለተኛ ቀን (በምስል)
14.1K views11:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-11-22 12:49:45 ከሳይበር ጥቃት ፈፃሚዎች ተጠንቀቁ - የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አስተዳደር
**************************

WinSCP (Windows Secure Copy) የተሰኘ የፋይል ማስተላለፊያ ፕሮቶኮልን በመጠቀም ተጠቃሚዎችን ዒላማ ያደረጉ አሳሳች እና ተንኮል አዘል ሶፍትዌሮችን በጉግል ማስታወቂያዎች ላይ በማጣበቅ ወደ ኮምፒውተራችን/ስልካችን እንድንጭናቸው ከሚያደርጉን አጭበርባሪዎች እንጠንቀቅ ሲል ‘ዘሃከር ኒውስ’ በድረ ገጹ አስነብቧል።

የሳይበር ጥቃት ፈፃሚዎቹ እንደ WinSCP ያሉ ሕጋዊ ሶፍትዌሮችን ለማውረድ የሚፈልጉ ተጠቃሚዎችን ተመሳስሎ የተሠራ ማልዌር እንዲጭኑ በማድረግ የተጭበረበሩ የፍለጋ ውጤቶችን እና ሐሰተኛ የጉግል ማስታወቂያዎችን እየጠቀሙ እንደሆነ ዘገባው አመላክቷል።

አጥቂዎቹ በተንኮል አዘል ማስታወቂያ አማካኝነት ተጠቃሚውን ወደ ተንኮል አዘል የዎርድፕረስ ድረ-ገጽ gameeweb[.]com ይመራዋል፣ ይህም ተጠቃሚውን በአጥቂው ቁጥጥር ስር ወዳለው የማስገሪያ (phising) ጣቢያ በመምራት መረጃዎችን ይዘርፉታል።

ተጨማሪ ለማንበብ ... https://www.facebook.com/permalink.php?story_fbid=pfbid02KUibb2tnK5Zm2LftW7A7hVpJ3ubXD5xdBdh1TfntJHEkE7Mizc7WLuuFCJwaJLS4l&id=61550945701729
13.5K views09:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-11-14 13:23:16
12.7K viewsBetty Sam, 10:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-11-13 21:29:09

13.0K viewsBetty Sam, 18:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-11-13 15:31:07
አትሌት ትዕግሥት አሰፋ በዓመቱ ምርጥ አትሌት ምርጫ የመጨረሻዎቹ 5 ውስጥ ተካተተች
*****************

በሴቶች ማራቶን የሪከርድ ባለቤት የሆነችው አትሌት ትዕግሥት አሰፋ በዓመቱ ምርጥ አትሌት ምርጫ የመጨረሻዎቹ 5 ውስጥ ተካትታለች።

አትሌት ትዕግሥት አሰፋ የዘንድሮውን የበርሊን ማራቶን 2:11:53. ሰዓት በመግባት በሴቶች ማራቶን ተይዞ የነበረውን ክብረ ወሰን በእጇ ማስገባቷ ይታወሳል።

ከአትሌቷ ጋር ኔዘርላንዳዊቷ አትሌት ፌምኬ ቦል፣ ጃማይካዊቷ አትሌት ሼሪካ ጃክሰን፣ ኬንያዊቷ አትሌት ፋይዝ ኪፕዬጎን እና ቬኒዙዌላዊቷ አትሌት ዩሊማር ሮያስ የመጨረሻዎቹ 5 ውስጥ የገቡ አትሌቶች ናቸው።
14.6K viewsYona, 12:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-11-13 14:17:05
ዴቪድ ካሜሮን የእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው ተሾሙ
**********************

የቀድሞው የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስትር ዴቪድ ካሜሮን የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው በዛሬው ዕለት ተሹመዋል።

የወቅቱ የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሪሺ ሱናክ የካቢኔ ሽግሽግ ማድረጋቸው ታውቋል።

በዚህም ዴቪድ ካሜሮንን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትራቸው አድርገው መሾማቸውን ሮይተርስ ዘግቧል።

የ57 ዓመቱ ዴቪድ ካሜሮን እኤአ ከ2010 እስከ 2016 እንግሊዝን በጠቅላይ ሚኒስትርነት መርተዋታል።
12.9K viewsNesru Jemal, edited  11:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ