Get Mystery Box with random crypto!

ኢሳት(ትኩስ ትኩስ ዜናዎች)

የቴሌግራም ቻናል አርማ esatchannal — ኢሳት(ትኩስ ትኩስ ዜናዎች)
የቴሌግራም ቻናል አርማ esatchannal — ኢሳት(ትኩስ ትኩስ ዜናዎች)
የሰርጥ አድራሻ: @esatchannal
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 25.06K
የሰርጥ መግለጫ

አዳዲስ ወሬዎችን ዜናዎችን ማግኝት ከፈለጉ እኛን ይቀላቀሉ ለወዳጅ ዘመዶ #share

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2024-03-27 12:55:57ህወሓት የፕሪቶርያውን ስምምነት በግልፅ በመጣስ ራያ ላይ ጦርነት ከፍቷል ” - የአላማጣና አካባቢው አመራር
የትግራይ እና አማራ ክልሎች የይገባኛል ጥያቄ ከሚያነሱበት አንዱ በሆነው ራያ አላማጣ አካባቢ ትላንትና " ህወሓት " ተኩስ መክፈቱን፣ በዚህም በሰው ሕይወት ላይ ሞትና የአካል ጉዳት ሙድረሱን አካባቢውን ከሚያስተዳድሩ አመራሮች (ባለስልጣን) አንደኛው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

አንድ የአካባቢው አመራር (ባለስልጣን) ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ “ ራያ ላይ  አዲስ ነገር አለ። ህወሓት የፕሪቶሪያውን ስምምነት በግልፅ በመጣስ ራያ ላይ ጦርነት ከፍቷል ” ብለዋል።

“ ቀን ላይ አንድ ሰው ሕይወቱ አልፏል። ሁለት ቆስለው ወደ ደሴ ሪፈር ተብለዋል። ደንበሩን በማለፍ የራያ አላማጣ ወረዳ አዳዲስ ቀበሌዎች ተቆጣጥሯል ” ሲሉ አክለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጦርነቱ የተከፈተው በምን ሰዓት ነው ? በዬት በኩል ነው የተከፈተው ? አሁን ተኩስ አለ ? በቁጥጥር ስር የሆኑት ቀበሌዎች እነማን ናቸው ? ከሰሞኑን ለጦርነት አመላካች ጉዳዮች ነበሩ ? ሲል ለአመራሩ ጥየቄ አቅርቧል።

አመራሩም ፣ “ ጦርነቱን የጀመሩት ሰኞ ሌሊት 6:00 አከባቢ ሲሆን፣ እስከ ቀን 6:30 ድረስ ነበር። መከላከያ ለራያ ምሊሻ ‘ወደ ኋላ ተመለሱ እነርሱም ይመለሳሉ’ በማለቱ ምክንያት ጦርነቱ ቁሞ የራያ ምሊሻ ወደ ኋላ ቢልም TDF መልሶ ቦታውን ተቆጣጥሮታል ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

ተኩሱ የተጀመረበትን ልዩ ቦታ በተመለተ በሰጡት ምላሽም ፣ “ የተጀመረበት ቦታው ‘ጮጓራ’ ይባላል። የራያ አላማጣ ቦታ ነው። አሁንም እሱን በማለፍ ወደ ‘ኮስም’ የሚባል አከባቢ እየተጠጉ ነው። ተጨማሪ ኃይልም እያስጠጉ ይገኛሉ ” ብለዋል።

የአካባቢው አመራር የተኩሱን መነሻ በገለጹበት አውድ ፣ “ የዚህ ዋናው መንስኤ አማራ ክልል #ወልቃይት እና #ራያ በስርዓተ ትምህርቱ ካርታ ላይ ተካተዋል በሚል በወጣው መግለጫ ነው ” ሲሉ አስረድተዋል።

“ የራያ ህዝብ የዘመናት ትግሉ በህጋዊ መንገድ ፍትህ ማግኘት እንጂ ጦርነት አይፈልግም። እነሱ እየተከተሉ ደጋግመው እያቆሰሉት ነው ” ሲሉም አክለዋል።

በህወሓት ተከፈተ ስለተባለው ተኩስ በትግራይ ክልል በኩል እስካሁን በይፋ የተባለ ነገር የለም።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በትግራይ ያሉ አስታዳዳሪዎችን አግኝቶ የነበረ ሲሆን ስብሰባ ላይ እንደሆኑና ወደ በኃላ ማብራሪያ እንደሚሰጡን ገልጸዋል።

የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ካቢኔ ሰሞኑን በሰጠው መግለጫ፣ “ የአማራ ክልል የትግራይ መሬት በካርታው በማስፈር የትምህርቱ ሰርዓቱ አካል በማድረግ እያስተማረበት ይገኛል " ማለቱ አይዘነጋም።

አስተዳደሩ ፤ በአማራ ክልል መንግሥት በኩል በትግራይ ህዝብ ላይ ግፍ እና በደል ሲፈፀም እንደቆየ አሁንም እንደቀጠለ ገልጾ ክልሉ የሰላም ስምምነቱን የሚያናጋ ጠብ አጫሪ ተግባራትን እየፈፀመ እንደሆነ ከሶ ነበር።

የፌደራል መንግስት በካርታው ላይ ምንም አይነት እርማት እንዳልሰጠ ፣ የአማራ ሕዝብም ሆነ ሌለው የኢትዮጵያ ህዝብ ከጊዚያዊ አስተዳደሩ ጎን እንዲቆሙ ይህ ሳይሆን ቀርቶ ለሚከተለው ነገር ሁሉ ግን የአማራ ክልል ሙሉውን ኃላፊነት ይወስዳል " ሲል አስጠንቅቆ ነበር።

@esatchannal
12.6K viewsedited  09:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-20 17:28:21 #ለጥንቃቄ
" ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዋናው መስሪያ ቤት ነው " እየተባለ ወደ ተለያዩ የባንኩ ደንበኞች ስልክ እየተደወለ የግል መረጃ መውሰድና የኦንላይን ዝርፊያ እየተሞከረ ይገኛል።
ቀደም ብሎ አንድ #አጭበርባሪ ግለሰብ (ጾታ - ወንድ) ሳያውቀው ለባንክ ሰራተኛ ደውሎ ያጋጠመውን ክስተት አጋርተናል።

የዜጎችን ሀቅና ገንዘብ አታለው ለመዝረፍ ስልክ ከሚደውሉት መካከል #ሴቶችም ስለሚገኙበት ጥንቃቄ አድርጉ።

ከላይ ባለው የድምፅ ቅጂ የምትሰሟት አጭበርባሪ ግለሰብ (ጾታ-ሴት) ከንግድ ባንክ ዋና መ/ቤት እንደደወለች በማስመሰል ፦ ደንበኞች የሞባይል ባንኪንግ ሲጠቀሙ ኔትዎርኩ please try again ፣ connection problem ፣ error ፣ service not available " የሚል ችግር እየገጠማቸው እንደሆነ ትገልጸለች።

በዚህ ምክንያት ባንኩ ከብዙ ደንበኞቹ ቅሬታ በመምጣቱ ፤ " ችግሩን በዋናው የንግድ ባንክ መ/ ቤት #ሲስተም ላይ ለማስተከል ነው " በማለት የደንበኛውን የግል መረጃዎች በመቀበልና በማታለል ዝርፊያ ለመፈፀም ሞክራለች።

አሁን ላይ እንዲህ ያሉት አጭበርባሪዎች ተበራክተዋል ተጠንቀቁ።
የመጀመሪያው የድምፅ ቅጂ በአጋጣሚ የባንኩ ሰራተኛ ጋር ነበር የተወደለው፣ውርደቱን ተከናንቦ ሄዷል
ለማንኛውም #ለማታውቁት ስልክ የባንክ መረጃችሁን እንዳትሰጡ።
ቲክቫህ
13.0K views14:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-07 07:03:23 ስለ ጌታቸው አዲስ መረጃ ታመዋል
ሚኒስትሩ“የአብይ ተላላኪ ባንዳ አይደልሁም”
10 ሰዓት ሙሉ የዘለቀው የወሎ ዉጊያ




12.7K views04:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-29 22:12:07 ተቆርጦ የቀረው የአብይ ንግግር፤ “እመኑኝ ወልቃይትን አሳልፌ አልሰጣቸውም




13.7K viewsedited  19:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-23 21:24:21
በምስሉ የሚታዮት ከ3 ቀን በፊት በሸዋ #ሰላድንጋይ ብልፅግና በድሮን የጨፈጨፋቸው ንፁሀን አማራዎች ናቸው::

በ11/06/2016 የክርስትና ስረአት አድርገው ሲመለሱ የነበሩ የአንድ ቤተሰብ አባላትን ጨምሮ ከ70 በላይ ህፃናትና አዛውንት በአንድ አይሱዙ ተጭነው ሲጏዙ የተጨፈጨፉ ሲሆን ከሞት የተረፉት ክርስትናው የነበረው ህፃኑና አቅፈውት የነበሩት አያቱ ብቻ ናቸው
13.3K viewsedited  18:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-19 20:11:48
ትናንት ጠዋት በአማራ ክልል ከአጣዬ ወደ ይምሎ በባጃጅ ሲመጡ የነበሩ ሰዎችን ሰንበቴ አቅራቢያ በዚህ መልኩ ነው inhuman በሆነ መልኩ አርደው የጣሏቸው።
የባጃጅ ሹፌሩን በዚህ መልኩ ነው የገደሉት
ምን አይነት የጭካኔ ጥግ ላይ ደረስን ግን
በዚህ አካባቢ ሰሞኑን በርካታ ህይወት እየጠፋ ነው። መፍትሔ ይሻል።
በርካታ ተጨማሪ መረጃዎች አሉ፣ይህን የቴሌግራም ቻናል ከስር ባለው ሊንክ join በማደረግ እና ለሌሎች በመጋበዝ ይከታተላሉ
@esatchannal
13.3K viewsedited  17:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-07 13:34:53

12.6K views10:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-01-24 13:56:17
ሰበር መረጃ
ሶማሊያ ለድርድር ዝግጁ ነኝ አለች
ሰሞኑን የጦርነት ጉሰማ እና የተለያዩ ሀገራትን ድጋፍ በማሰባሰብ ማስፈራሪያ ስታሰማ የነበረችው ሶማሊያ ከአዲስ አበባ ጋር ለድርድር ዝግጁ ነኝ ስትል ፕሬዚዳንቱ ተናግረዋል። የሶማሊያው ፕሬዚዳንት ትናንት ኳታር የገቡ ሲሆን ከኳታሩ አልጀዚራ ጋር ቆይታ አድርገዋል። በዚህም ኢትዮጵያ የባህርበር እንዲረኖራት እንፈልጋለን በዚህ ላይ ምንም ጥያቄ የለንም ያሉ ሲሆን ነገር ግን መሬታችንን በጉልበት በመውሰድ ሳይሆን በድርድር መሆን ይኖርበታል፣ ለዚህም ዝግጁ ነን ሲሉ ተደምጠዋል። ፕሬዝዳንቱ ከጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ ጋር በቅርቡ ጅቡቲ በተገኒኝንበት ወቅት ከሱማሊላንድ ጋር የወደብ ስምምነት እንደሚያደርጉ አልነገረኝም ሲሉ ወቀሳ አቀርበዋል።
ፕሬዝዳንቱ፣ ችግሩ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ስላልደረሰ የግብጽ ጦር ወደ ሱማሊያ እንዲገባ ሰሞኑን ወደ ካይሮ ባቀኑበት ወቅት ከፕሬዝዳንት አል ሲሲ ጋር እንዳልመከሩ ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ ጋር የፈፀመችውን የወደብ ስምምነት ወደ ትግበራ እንዳታስገባ አሳስበዋል
12.6K viewsedited  10:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-01-14 15:25:20
ሶማሊያ ከሰሞኑ የምትይዘውን የምትጨብጠውን አሳጥቷታል።በኢትዮጵያ ላይ በይፋ ጦርነት ወደማወጅ እየተንደረደረች ይመስላል...

የአለም ሀገራት ጀርባቸውን የሰጧቸው የሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሸህ መሀመድ "ሶማሊያዊ ለማይቀረው ጦርነት ይዘጋጅ የሶማሊያ የግዛት አንድነትና ሉዓላዊነት አደጋ ተጋርጦበታል" በማለት የጦርነት ቅስቀሳ እያካሄዱ እንዳለ ተሰምቷል።

ፕሬዝደንቱ ትናንትም ወጣቶችን ሲቀሰቅሱ እንደዋሉ ከመገናኛ ብዙሃናቸው ዘገባዎች መረዳት ተችሏል።በቅስቀሳቸው ኢትዮጵያ አንድ እርምጃ ወደ ሶማሊያ ከገባች እኛ ደግሞ ሁለት እርምጃ ወደ ኢትዮጵያ ድንበር እናልፈለን አለም እኛን መውቀስ አይችልም ማለታቸው ሶና የሶማሊያ ቴሌቪዥን ዘግበዋል።ወጣቶችን መሳሪያ እያሸከሙ ፎቶ በማንሳት ለጦርነት ማነሳሳቱን ተያይዘውታል።
=========================
@esatchannal
13.3K viewsedited  12:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-12-26 16:20:47 የጨጓራ ህመም ለሚስቸግረዉ




12.7K viewsedited  13:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ