Get Mystery Box with random crypto!

Ayu Zehabesha-Official (አዩ ዘሀበሻ)

የሰርጥ አድራሻ: @ayuzehabeshaofficial
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 181.36K
የሰርጥ መግለጫ

በዚህ ቻናል ወቅታዊ፣ታማኝ እና ፈጣን መረጃ ያገኛሉ❗
መረጃ ለማድረስ እና ማስታወቂያ ለማሰራት ከስር ባለው ሊንክ ይጻፉልን👉http://t.me/ayulaw

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 291

2022-10-07 15:38:05
Advertisement
ውድ የአዩ ዘሀበሻ ተከታዮቼ,  ያለንን እውቀት ማሳደግ የበለጠ በስራችን ውጤታማ ያደርገናል።
በመሆኑም አዳዲስ የሳይንስ እና የቴክኖሎጂ መረጃዎችን እና ትምህርቶችን እንደ አመጣጣቸው የሚያቀርብላችሁን አዲስ የቴክኖሎጂ ቻናል ከስር ባለው ሊንክ ተቀላቀሉ

https://t.me/gofere2tech
https://t.me/gofere2tech
https://t.me/gofere2tech
35.3K viewsAyu, 12:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-07 14:32:09 ነገ በደቡብ አፍሪካ ሊካሄድ የነበረው ድርድር ለጊዜው ተራዝሟል።
36.9K viewsAyu, 11:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-07 14:18:19
በተፈታኝ ተማሪዎች ላይ የትራፊክ አደጋ ደረሰ

የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችን ጭኖ ወደ ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሲጓጓዝ በነበረ የህዝብ ተሽከርካሪ ላይ የትራፊክ አደጋ ደረሰ፡፡

የትራፊክ አደጋው የደረሰው መስከረም 26 ቀን 2015 ዓ.ም በምዕራብ ጎጃም ዞን በሰሜን ሜጫ ወረዳ በአምቦ መስክ ቀበሌ ነው፡፡

መነሻውን ከባህርዳር ወደ ማርቆስ ሲጓዝ በነበረ የህዝብ ተሸከርካሪ እና ከምዕራብ ጎጃም ዞን ሰከላ ወረዳ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችን ጭኖ ወደ ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሲጓዝ በነበረ የህዝብ ተሸከርካሪ በመጋጨቱ ነው አደጋው የተከሰተው።
የሰሜን ሜጫ ወረዳ የመንግስት ኮሙኒኬሽን
ለፈጣን መረጃ የቻናሌ ቤተሰብ ይሁኑ
http://t.me/ayuzehabeshaofficial
37.5K viewsAyu, 11:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-07 09:39:09 የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችን ለመፈተን የተመደቡ የዩንቨርስቲ መምህራኖች ዩኒቨርሲቲው በቅድሚያ ገንዘብ ስላልሰጠን የመጓጓዣ ገንዘብ ስለተቸገርን ወደ ተመደብንበት ቦታ ለመሄድ አዳጋች ሁኔታ ፈጥሯል በገንዘብ እጥረት የቀሩም እንዳሉ ተናግረዋል። በዚህም ትምህርት ሚንስትር ተጠባባቂ ፈታኝ ካላዘጋጀ በፈተናው ላይ መስተጓጐል እንዳይፈጠር ካሁኑ መስራት አለበት።
አዩ ዘሀበሻ
ለፈጣን መረጃ የቻናሌ ቤተሰብ ይሁኑ
http://t.me/ayuzehabeshaofficial
12.8K viewsAyu, edited  06:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-07 09:33:56 ጥምር ጦሩ ሰለኽለኾ ገብቷል፣ ለአክሱም በቅርብ እርቀት ላይ ነው የሚገኘው።
አዩ ዘሀበሻ
ለፈጣን መረጃ የቻናሌ ቤተሰብ ይሁኑ
http://t.me/ayuzehabeshaofficial
13.5K viewsAyu, edited  06:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-07 09:15:53
የህወሓት ታጣቂዎች በቆቦና አካባቢው ከ100 በላይ ዜጎችን አግተው መውሰዳቸውን ነዋሪዎች ገለጹ

በህወሓት ቁጥጥር ስር የነበሩ አካባቢዎች ነጻ መውጣታቸውን ተከትሎ ህይወት ምን እንደሚመስል አል ዐይን አማርኛ የአካባቢዎቹን ነዋሪዎች አነጋግሯል።

በቆቦ ከተማ ፣ አርበት፣ ዞብል ተራራ እና ዙሪያው ባሉ ቀበሌዎች ውስጥ ይኖሩ ከ100 በላይ ሰዎች በህወሓት ታጣቂዎች ታፍነው እንደተወሰዱ ነዋሪዎቹ ተናግረዋል።

በህወሓት ታጣቂዎች ታፍነው የተወሰዱት ዜጎች ወጣቶች፣ የጦር መሳሪያ ይኖራቸዋል እና መረጃ ይሰጣሉ በሚል የጠረጠሯቸውን እንደሆነም ነዋሪው ጠቁመዋል።
AlAin
ለፈጣን መረጃ የቻናሌ ቤተሰብ ይሁኑ
http://t.me/ayuzehabeshaofficial
15.0K viewsAyu, edited  06:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-07 08:48:21 አሳዛኙ የራሕዋ ገብረዋሕድ ደብዳቤ
(ቆቦ፣ ደጋ በላጎ ከኪሷ ከተገኘ)

" ከታጋይ ራሕዋ( ሚጡ) ለመላ ቤተሰቤ፦

በመጀመሪያ ለተከበራችሁት ለምወዳችሁ ወላጆቼ ፣ ወንድም እኅቶቼና ቤተሰቦቸ ሆይ ! ይቺ ምትክ (አቻ) የማይገኝላት የእግዚአብሔር ፀጋ ለሆነዉ ጤናችሁ እንደምን አላችሁ? ለማለት እወዳለሁ። ደኅና እንደምትሆኑ ደግሞ ባለሙሉ ተስፋ ነኝ።
- እኔ ግን ናፍቆታችሁ እንደ ዉኃ ይጠማኛል፤ እንደ እንጀራ ይርበኛል፤ እንደሰማይ ርቆኝ መቻል አቅቶኛል። ግን እችለዋለሁ። የማይቻል የለም። ኹሉንም ለፈጣሪ ሰጥቼዋለሁ። ጸሎቴንም አላቋረጥኩም። ኹሉም የእግዚአብሔር ፈቃድ እስከሆነ ድረስ የሚበልጠዉ በተስፋ መኖር ነዉ ብዬ ነዉ እማምነዉ።
-በተለይ ያቺ ሩሕሩሕ ፣የዋህ የሆነቺዉና ነፍሴን አሳልፌ የምሰጣት፣ ከሌሎች እናቶች ጋር የማላወዳድራት እናቴ (ኣብረኸትዬ ) የኔ ማር የሆንሽዉ አንድ ቀን እንኳ እፎይ ሳትይ ከችግር ወደ ችግር የሆነዉ ህይወትሽ እንዴት ኾኖ ይኾን ? አብረኸትዬ ዘወትር ባንቺ የተነሳ ሳስብና ስጨነቅ እዉላለሁ። አላረፍኩም።
በተለይ የኔን እገዛ በሚያስፈልግሽ ጊዜ አላገዝኩሽም። ከሁሉም በላይ ደጋፊ የሌለዉን ቤታችንን በህመም ምክንያት ሳልነግርሽ ትቸሽ ሄድኩ። ምክንያቱም ከፊቴ ስታለቅሺ ማየት አልፈለኩም። ከወንድሜ ከገ/ሕይወት ይልቅ እኔ እዘምታለሁ ብዬ ወስኛለሁ። ምክንያቱም እኔ ከማግዛችሁ ይልቅ እሱ የሚያግዛችሁ ስለሚበልጥ ነዉ። አትቅየሙኝ። አብረኸትዬ በኔም የተነሳ አታስቢ (አትጨናነቂ)። ደኅና ነኝ። አሁን በህልሜም በእዉኔም እየመጣ ከአቅሜ በላይ ሆኖ የሚያስቸግረኝ ጉዳይ የመልከኛዉ፣ ምሑሩ እና ልባሙ ወንድሜ የሃለቃ በርሄ ጉዳይ ነዉ።
ከቀናት በፊት መጥፎ ህልም አይሉት ቅዠት አየሁ። እዉነትም መሰለኝ። ከወንድሜ በርሄ ጋር የተያያዘ መስሎኝ ከእንቅልፌ ብድርግ ብዬ ተነስቼ ማልቀስ ስጀምር ጓደኞቼ "ምን ሆነሽ ነዉ?" ብለዉ ጠየቁኝ። እኔም ያስጨነቀኝን ቅዠት ነገርኳቸዉ። እነሱም ህልሙ ጥሩ መሆኑን ነግረዉ አፅናኑኝ። እኔም ኹሉንም ለበጎ ያድርገዉ ብዬ ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማሪያም ነገርኳት።
በርሄ ወንድሜ ጤናህ እንዴት ነዉ ? እንደቀድሞዉ መለስ አላለልህም? ከቤተሰቦችህ ጋር ቤተክርስቲያን እያገለገልክ ነዉ? ከጓደኞችህ ጋር እየተጫወትክ እንደማገኝህ በጉጉት እጠብቃለሁ።
በርሄ ወንድሜ በዚህ እገዛ በሚያስፈልገኝ ጊዜ ትታኝ ሄደች ብለህ አደራ እንዳታዝንብኝ (እንዳትቀየመኝ) ! የኔ ማር ይቅርታ እየጠየኩህ ነዉ። ጊዜዉ ሲደርስ ደግሞ እክስሃለሁ። ሰላም ነዉ ያለኹት እንገናኛለን።
-ባባ (ገ/ዋሕድ ብርሃኔ) (ሣሙና) )፣ ወንድሜ ገ/ሕይወት ፣ እኅቴ ትርሓስ ፣ ማኅደር ፣ ዳናይት ፣ ዳንኤል (ፀጋዬ)፣ ወንድሜ አሉላ ፣ ወንድሜ ቢኒያም እስከምንገናኝ ኹላችሁንም ሰላም ሰላም ብያለሁ።
ለመገናኘት ደግሞ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም መልካም ፈቃድ ነዉና ስለኔ አትጨነቁ:: በተጨማሪም ለኹሉም ጎረቤት ሰላም በሉልኝ።
- ለእናቴ (አብሻይ)፣ አረጋዊ ፣ ጨርቆስ ፣ ማርቆስ ብቻ ኹሉንም ሰላም በሉልኝ።
- ያዬ (ብርሃነ ግደይ) ሥ ደኅና ነዉ? እያረጀ ነዉ እንዴ? ምግበይሥ እንደምን ነዉ ? ዳንኤል ገ/ሄርንም ሰላም በሉልኝ። የሹስ ተሻላት ወይ ? ሰላም በሉልኝ:: በተጨማሪም ለኹሉም ቤተሰብ ሰላም በሉልኝ። ቻዎ ፣ ቻዎ !!

[ከድብዳቤዉ ራስጌ ላይ ሰረዝ ደለዝ ተደርጎ የተጻፈው ደግሞ እንደሚከተለው ይላል።]
" አንድ ነገር የረሳኹት፣ ምጣዱን ነዉ:: ይኸዉም አዬር ቤት ዉስጥ ተከራይቼ ከነበርኩበት ቤት ነዉ ትቸዉ የመጣሁት ( ያለዉ) :: ቦታ እንዳይዝባቸዉ እስከዛዉ እነሳራ ይጠቀሙበት፤ ወይም ደግሞ ማርቆስ ቤት አድርግልኝ:: ብር ከጠየቁ ደግሞ መሸጫ ዋጋዉ 2,000.00 ብር ነዉ::"

ቤተሰቦቼ ከልብ የመነጨ ሰላምታዬ ይድረሳችሁ :: እና እኔ አኹን ያለሁበት ቦታ ራያ -ጨርጨር የሚባል ቦታ ኾኖ
አርሚ -44
ኮር -441(1)
ሬጅመንት (ሻለቃ)-3
ኃይል - 4
ደጀና ክፍለ ሠራዊት ነዉ !!
ትግራይ ትስዕር !!!"
*
ማስታወሻ፦ ራሕዋ ወንድሟን ተክታ ለትሕነግ ወታደር የነበረች ሴት ናት። ይህ ደብዳቤ የተገኘው ከኪሷ ነው። አስከሬኗም የተገኘው ቆቦ፣ በላጎ ነው። ደብዳቤው የትሕነግን እብደት፣ የትግራይ ልጆችን ያሉበትን ሁኔታ፣ የትግራይ እናቶችን ስቃይና ዋይታ ያሳያል በሚል ነው ተርጉሞ የቀረበው።( Wubshet Mulat)
ለፈጣን መረጃ የቻናሌ ቤተሰብ ይሁኑ
http://t.me/ayuzehabeshaofficial
17.6K viewsAyu, edited  05:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-07 08:48:13
17.5K viewsAyu, 05:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-06 19:57:52
በሽራሮ በኩል አዲሀገረይ በጥምር ጦሩ ቁጥጥር ስር መሆኗ ተረጋግጧል።
========================
በውሸት አካውንት እንዳትሸወዱ ትክክለኛው የቻናሌ ሊንክ ከስር ያለው ብቻ ነው
http://t.me/ayuzehabeshaofficial
http://t.me/ayuzehabeshaofficial
27.5K viewsAyu, 16:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-06 19:56:03
#የኡጋንዳ ፕሬዝዳት ልጅ ጀነራል ሙሁዚ ኬኒሩጋባ ለአዲሷ የጣሊያን ጠ/ሚኒሰትር የጋብቻ ጥያቄ አቀረቡ
100 ከብቶችን ጥሎሽ እሰጣለሁ ያሉት ጄነራሉ፤ ጥያቄው ተቀባይነት ካላገኘ “ጣሊያንን እወራለሁ” ብለዋል። ጀነራል ሙሁዚ ኬኒሩጋባ በትዊተር ገጻቸው ከሚያጋሩት መልእክት ጋር በተያያዘ ከኃላፊነታቸው ተነስተዋል።
27.7K viewsAyu, 16:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ