Get Mystery Box with random crypto!

Ayu zehabesha

የቴሌግራም ቻናል አርማ ayuzehabesha — Ayu zehabesha A
የቴሌግራም ቻናል አርማ ayuzehabesha — Ayu zehabesha
የሰርጥ አድራሻ: @ayuzehabesha
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 139
የሰርጥ መግለጫ

@abretp

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2022-09-03 20:57:31 መረጃ
ጁንታው ከ ሰቆጣ 10ኪሎሜትር ከምትገኘው ወለህ የሚባለው ወረዳ ገብቷል። አንዳይመቱም እዛው ከምትገኘው የስደተኞች ካምፕ ገብተው ከህዝቡ ጋር ተቀላቅለዋል።
የየሰቆጣ ህዝብ ተረጋጉ አዲስ ነገር ይኖራል። ጥምር ጦሩን ደግፉ።
አዩ ዘሀበሻ
23.4K viewsAyu, edited  17:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-03 20:46:15 ከሰቆጣ ወደ ላሊበላ መስመር ወለህ በሚባል አካባቢ ትኩረት ያስፈልጋል ሲሉ የአካባቢው ነዋሪዎች ገልፀዋል።
አዩ ዘሀበሻ
25.0K viewsAyu, edited  17:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-03 20:20:37 ወርቄ
የወርቄ ህዝብ እገዛ ይሻል የቂም በትር ማረፊያ ሁኗል። ህወሃት ሙሉ አቅሙን ተጠቅሞ ወርቄን እያወደመ ነው። እናቶች አዛውንቶች ጫካ ነው ያሉት። ባለሽስጣሞቹ አሁንም ድረስ እየታገሉ ነው፣ ቤተሰቦቻችን ተራቡብን እነሱን አግዙልን ብለዋል።
ወሎ ህብረት እና ወሎ ቤተአምሃራ ህብረት እርዳታ አድርሱላቸው።
አዩ ዘሀበሻ
27.5K viewsAyu, edited  17:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-03 20:08:46 ማይፀብሪ
ጥምር ሃይሉ በማይፀብሪ በኩል ለሽሬ 13/14 ኪ/ሜ ገደማ ነው የቀረው።
ሽሬን ተቆጣጥሯል የተባለው ለጊዜው ስህተት ነው።
አዩ ዘሀበሻ
28.4K viewsAyu, 17:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-03 17:57:22 ከወልድያ ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ምክር ቤት የተላለፈ ውሳኔ
የከተማውን አሁናዊ ሁኔታ መነሻ ከተማ በማድረግ የከተማ አስተዳደሩ የሰዓት እላፊ ገደብ ማውጣቱ የሚታወቅ ሲሆን ከዚህ በተጨማሪ ሌሎች ክልከላዎችን ማስቀመጥ በማስፈለጉ የከተማ አስተዳደሩ የጸጥታ ምክር ቤት የሚከተሉትን ውሳኔዎችን አስተላልፏል።

1. ከፀጥታ መዋቅሩ ውጭ በከተማችን በየትኛውም ቦታ የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ በፍጹም የተከለከለ ነው፡፡

2. ከተፈቀደላቸው የመንግስት የፀጥታ አባላት ውጭ የሰራዊቱን አልባሳትን መልበስ የተከለከለ ነው፡፡

3. ሀሰተኛ ወሬ በመልቀቅ የከተማውን ማህበረሰብ የሚያውኩ አሉባልታዎችን በሚዲያዎችና በአገልግሎት መስጫ ተቋማት በማሰራጨት ህዝቡን ማዋከብ በጥብቅ የተከለከለ ነው፡፡

4. በከተማችን የሚገኙ የራያና ቆቦ ከተማ ተፈናቃዮች ውጭ ሌላው አካል ወደ መጣበት አካባቢ እንዲመለስ በጥብቅ እናሳስባለን

5. በከተማችን የህዝብ አገልግሎት የሚሰጡ ባንክ ቤት፣ ሱቆች፣ ሆቴሎች፣ ካፌና ሬስቶራንቶች፣ የንግድ ተቋማት እና የመሳሰሉትን መዝጋት ፍጹም የተከለከለ ነው፡፡

6. ማንኛውም የግል ተሸከርካሪ ለፀጥታ ስራ ትብብር ሲጠየቅ የመተባበር ግዴታ አለበት። ነገር ግን ተሸከርካሪን የሚሸሽግ፣ የሚያሸሽ፣ ሆን ብሎ ተበላሸ በሚል ላለመተባበር ጥረት የሚያደርግ ግለሰብ እና ድርጅት ተጠያቂ ይሆናል።

7. የመኖሪያ ቤትና የመኝታ አልጋ የሚያከራይ ግለሰብ የተከራዮቻችሁን ማንነት የመለየትና የታደሰ መታወቂያ ስለመያዛቸው የማረጋገጥ ግዴታ ሲኖርባችሁ አጠራጣሪ ጉዳይ ሲኖር ለጸጥታ አካል ሪፖርት የማድረግ ሃላፊነታችሁን እንድትወጡ በግልፅ እናሳስባለን

8. ፀጉረ ልውጥ ሰው የሚያገኝ ግለሰብ በቅርቡ ለሚገኝ የፀጥታ አካል የመጠቆምና የማቅረብ ኃላፊነት ይኖርበታል

9. ከነሀሴ 29/2014 ዓ.ም ጀምሮ የቀበሌ መታወቂያ መስጠት የተከለከለ መሆኑን እናሳውቃለን።

10. ማንኛውም የመንግስት እና የግል ታጣቂ አካባቢውን በብሎክ አደረጃጀት ውስጥ በመካተት በየደረጃው ያለ የፀጥታ አካላት በሚሰጠው ስምሪት አካባቢውን የመጠበቅ ኃላፊነትና ግዴታ አለበት

11. አግባብነት የሌለው የዋጋ ንረት መፍጠር፣ በሸቀጦችና በግብርና ምርቶች ላይ ተገቢ ያልሆነ ዋጋ ጨምሮ ህዝቡን ማስቃየት፣ በማንኛውም ህገ-ወጥ እንቅስቃሴ ውስጥ መገኘት በህግ ያስጠይቃል፡፡

ከላይ የተዘረዘሩትን ውሳኔዎች ማንኛውም አካል የማክበርና ኃላፊነቱን የመወጣት ግዴታ ያለበት መሆኑንና ይህን ውሳኔ የማያከበር ግለሰብም ሆነ ድርጅት ላይ የፀጥታ መዋቅሩ አስፈላጊውን የእርምት እርምጃ እንደሚወስድ በአጽእኖት እናሳውቃለን፡፡
ነሐሴ 28/2014 ዓ.ም.
ወልድያ
34.9K viewsAyu, 14:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-03 17:53:34 መረጃ
ከአላማጣ መረዋ አበቃት ወደ ጋዝጊብላ ወረዳ አስከተማ ሄደው የነበሩት የወራሪው ኃይል አባላት ወደ ሰቆጣ የሚሄደውንጰ ዋና መስመር ለ2 ሰዓታት ዘግተው ነበር ከ2 ሰዓታት ቆይታ በኋላ ከጥምር ጦሩ ጋር መንገድ በዘጉበት ዛሮታ ቀበሌ በተደረገው ውጊያ ትላንት  በርካታ የሰው ሀይል እንደ ቅጠል ረግፎባቸው መስመሩን ለቀው ወደ ጉብራቅ አቅጣጫ እና ወደ አሏቅ እንዲሁም በሀሙሲት የነበረው ሀይል ለዛሬ ሊነጋ አዳሩንም እና አስከዚ ስአት ድረስ በጀግኖቹ መከላከያ ሰራዊታችን እና ጥምር ጦሩ እርምጃ ሲወሰድበት አድሮና ውሉ የተረፎት ደግሞ በአየር ሀይል የተዳሰስ ሲሆን አሁን ላይ ቀሪው ሀይሉ በደነብሱ ወደ ቴያ አካባቢ ወረዱ ተሰባስቦ ይገኛል።
ከቦታው በስልክ
አዩ ዘሀበሻ
====================
ስለጦርነቱ ፈጣን መረጃ ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሌን ይቀላቀሉ
http://t.me/ayuzehabesha    http://t.me/ayuzehabesha
http://t.me/ayuzehabesha   http://t.me/ayuzehabesha
በውሸት አካውንት እንዳትሸወዱ
33.6K viewsAyu, edited  14:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-03 16:35:36 በዛሬው እለት የወርቄ ጀግኖች ከ31 በላይ ክላሽንኮቭ መሳሪያ ማርከዋል።
ህወሃት በዚህ ግንባር ወርቄን መያዝ 4ኪሎን መያዝ ነው በሚል በርካታ ሃይል እያመጣ ከፍተኛ ውጊያ አድርጓል። አሁንም እንደቀጠለ ነው። ይሄን የሚያደርገው በዞብል ጋቲራ በኩል ወደ ወርቄ ዘልቆ በመግባት ነው፣ ግን እንዳሰበው አልሆነም።
በዚህ ግንባር አብዛኞቹ ያለቁት ሴቶች እና አዛውንቶች ናቸው(ሀሰን ከረሙ)።
አዩ ዘሀበሻ
35.6K viewsAyu, edited  13:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-03 15:25:26 ሳምረን የተቆጣጠረው የጄኔራል ሃይሉ ከበደ ጦር
(ጄኔራል ሃይሉ ከበደ ክ/ጦር)
እስከ ትናንት ጠዋት ድረስ ኒሯቅ (ያብርገሌ ወረዳ ዋና ከተማ) በጠላት የሞት የሽረት ትግል እየተደረገባት ነበር። ትናንት ግን ጸሃይ ሳይወጣ ለማይቀርላት የወገን ጦር እጇን ሰጥታለች።

በዚህም ከጻታ፣ ሻኩራና ቀዳሚት ዙሪያ ምሽጉን ጥሎ የሮጠው የወያኔና ባንዳው የሸንጎ ታጣቂ እንደገና ለመደራጀት ተሰብስቦ ባለበት የጄኔራል ሃይሉ ከበደ ልጆች እምሽክ አድርገውታል፤ የቀረውም ሳምረን ጥሎ የተለመደው የተከዜ ሸለቆ ገብቷል።

ባሁኑ ሰአት ሳምረ በወገን ቁጥጥር ስር የምትገኝ ሲሆን መቀሌን በከባድ መሣሪያ ሬንጅ ውስጥ (በ40ኪሜ) እንድትገባ አድርጓታል። ይህ በዚህ መስመር የሚገኘው ጦር ለመቀሌ መቅረቡ ብቻ ሳይሆን ኮሽ ባለ ቁጥር እንደ ነብሰጡር ጥንቸል ዘለው የሚደበቁበት ዋሻ (ከ3ኪሜ በላይ ውስጥ ለውስጥ መንገድ ያለው) መገኛ በመሆኑ ይሄንን ዋሻ ቀድሞ እንዲይዝ የሚጠበቅ ነው።

በሌላ በኩል ትናንት ማታ ጀምሮ በላይ በመረዋ-ሀሙሲት አደርጎ ግማሹ በጉብራቅ አደርጎ ዛሮታ፣ ግማሹ በግሸና በር አድርጎ አሏቅ ወንዝ የገባው የተበታተነ ሃይል ከትናንት ጀምሮ በእሳት እያናገሩት ይገኛል። ዛሬ ጠዋት ላይም ይዟቸው ከነበሩ አከባቢዎች ወደኋላ የፈረጠጠ ሲሆን ተበታትኖ በየጥሻውና በየገበሬ ቤቱ እየተልከሰከሰ ይገኛል። ያከባቢው ገበሬም ያገኘኸውን እየቀነጠስክ መሳሪያ እንድትማርክ ተጋብዘሃል። ዋግ ገብቶ የሚወጣ አይኖርም፣ በጦርም በፍቅርም የሚመጡትን በየቋንቋቸው እናስቀራለን።

የጄኔራል ሃይሉ ከበደ ክፍለ ጦር
በዚህ በሚካሄደው ትግል ጥምር ጦሩና ደጀኑ ዋጋ እየከፈለ ወደፊት እየገሰገሰ ይገኛል።
ነገር ግን በተለየ የጻታን፣ የቀዳሚት ዙሪያን የዛምራን የአለት ምሽጎችን በመደርመስ በኩል ከፊት የሚገኘው የራስ ሃይሉ ክፍለ ጦር ያንበሳውን ድርሻ ይወስዳል።
የአገር መከላከያ 104ኛ ኮር 36ኛ ክፍለጦርን በጄኔራል ሃይሉ ከበደ መሠየሙ ይታወቃል።
( ያብወይ ከግንባር)
ተጨማሪ መረጃ አለኝ ጠብቁኝ.....Join our channel.
36.8K viewsAyu, edited  12:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-03 15:13:28 ራያ ቆቦ ከተማ ውስጥ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጁን ጁንታው ለህክምና መስጫ፣የራያ ግንባር ህክምና ቁሳቁስ ማከማቻ እንዲሁም የመካከለኛ አመራር መሰባሰቢያ አድርጎት የነበረ ሲሆን አየር ሃይል ትናንት ማታ እርምጃ ወስዷል። ከዚህ በተጨማሪ በርካታ ታንኮች ከጥቅም ውጪ ተደርገዋል።
አዩ ዘሀበሻ
35.6K viewsAyu, edited  12:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-03 14:48:25 ኮምቦልቻ
ኮምቦልቻ ከተማ እስከ አሁኗ ሰአት ድረስ ከ100 በላይ የህወሀት ሰርጎ ገብና አስተኳሾች በቁጥጥር ስር ውለዋል።
በኬላ እየተደረገ ካለው ቁጥጥር በተጨማሪ ሁሉም የከተማዋ ማህበረሰብ ፀጉረ ልውጦችን ሲያይ ለሚመለከተው አካል እንዲያሳውቅ ጥሪ ቀርቧል።
36.0K viewsAyu, 11:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ