2022-09-06 14:46:35
ጳጉሜ 1 ቀን 2014 ዓ.ም
"በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የደረሰብን ምት ፈፅሞ የምንቋቋመው አልሆነም ብዙዎች አጠገባችን ተደምስሰውብናል፣ አመራሮቻችንም ሞተዋል የተረፉትም ሸሽተዋል" ፦በሰቆጣ ግምባር እጃቸውን የሠጡ የህወሓት ታጣቂዎች
ወጣት ጉዕዲ ገ/ኪዳን ትባላለች በሠቆጣ ግምባር እጃቸውን ለመከለከያ ሠራዊታችን ከሰጡ የአሸባሪው ህወሓት ታጣቂዎች መካከል አንዷ ናት አማራን መደምሰስ አለብን የሚል ተልዕኮ እንደተሰጣቸውም ተናግራለች።
በትግራይ ክልል ውስጥ ከፍተኛ አፈና እና የመብት ጥሰት በአሸባሪው ታጣቂዎች እየተደረገ መሆኑን የገለጸችው ወጣት ጉዕዲ ምንም እንኳን የጦርነት ፍላጎት ባይኖራትም በቤተሰቦቿ ላይ የሚደርሰውን ወከባ እና እንግልት ላለማየት አሸባሪውን ቡድን መቀላቀሏን ገልፃለች።
ሌላኛው ምርኮኛ ኤልያስ ገ/ፃዲቅ የሶስት ወንድ እና የአንድ ሴት ልጅ አባት ሲሆን ከሚሰራበት ቦታ በሽብር ቡድኑ ታጣቂዎች ተገዶ ወደ ማሰልጠኛ እንደተወሰደ ተናግሯል።
በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የደረሰብን ምት ፈጽሞ የምንቋቋመው አልሆነም ብዙዎች አጠገባችን ተደምስሰውብናል፣ አመራሮቻችን ሞተዋል የተረፉትም ጥለውን ሸሽተዋል ሲሉ በዚሁ ግንባር እጃቸውን ለሠራዊታችን የሰጡት አለም ሙሉ እና ገ/እየሱስ ሃለፎም ተናግረዋል።
አብርሃም ዘውዱ
ፎቶግራፍ አብርሃም ወርቁ
===============
ተጨማሪ መረጃዎች ይኖራሉ፣ የቻናሌ ቤተሰብ በመሆን ተከታተሉ
http://t.me/ayuzehabesha http://t.me/ayuzehabesha
40.1K viewsAyu, 11:46