Get Mystery Box with random crypto!

Ayu zehabesha

የቴሌግራም ቻናል አርማ ayuzehabesha — Ayu zehabesha A
የቴሌግራም ቻናል አርማ ayuzehabesha — Ayu zehabesha
የሰርጥ አድራሻ: @ayuzehabesha
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 139
የሰርጥ መግለጫ

@abretp

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 10

2022-09-02 19:37:35 ሸዋሮቢት በዚህ ሰዓት የተኩስ ድምፅ እየተሰማ ይገኛል።
መስተካከል ያለባቸው ነገሮች አሉ፣በዚህ ሰዓት ዋናው ጠላት ላይ ብናተኩር የተሻለ ነው።
ችግሩን በውይይት ለመፍታት ብንሞክር የተሻለ ነው።
አዩ ዘሀበሻ
40.1K viewsAyu, edited  16:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 19:19:39 መረጃወች
ጥምር ጦሩ ከትላንት ጀምሮ በራያ ግንባር ጎብየን ተቆጣጥሮ ሮቢትን ለማስለቀቅ ጥሩ የሚባል ተጋድሎ እያደረገ ሲሆን በሮቢት አሚድ ውሀ በምትባል መሿለክያ ላይ ተከማችቶ በነበረ በአስር ሽዎች የሚቆጠር የጁንታው ሰራዊት በድሮን ዶግ አመድ ሁኗል። ነገ ወይም ከነገ ወድያ ሮቢት በወገን ጦር ቁጥጥር ስር ትሆናለች።
አሁንም ድረስ በወርቄ  ዞብል እና ቆቦ ጥጋጥግ ላይ ጦርነት አለ ሽንፈት የቀመሰው የጁንታው ሰራዊት በራያ ቆቦ ወረዳዎች በጣም ብዙ ቁጥር ያላቸውን ንፁሀንን ገሏል። አልገዛም ያለው የራያ ቆቦ ህዝብ በቡድንም በግልም በመሆን ቆቦ ለጁንታው የእግር እሳት እንድትሆንበት እያደረገ ነው።

በሰቆጣ ግንባር ለወራት በጁንታው ቁጥጥር ስር የነበረችው አበርገሌ ነፃ መውጣት ችላለች። ነገር ግን አሁንም ለሰቆጣ በቅርብ ርቀት ሀሙሲት እና ጥራሪ
ከተማ ላይ ተቆርጦ የቀረ የጁንታው ሀይል በከፈተው ጥቃት በመረምረም ላይ ይገኛል። በምእራብ ትግራይ በሚደረግ ጦርነት ለአመት በጁንታው ቁጥጥር ስር የነበረችውን አድርቃይን ነፃ ለማውጣት የተቃረብን ሲሆን ብዙ የጁንታው ሀይሎች ተደምስሰዋል።
ትክክለኛ የቻናሌ ሊንክ ይሄ ብቻ ነው፣በውሸት አካውንት አትሸወዱ http://t.me/ayuzehabesha
40.0K viewsAyu, edited  16:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 19:19:05
ሸዋ ቱሪዝም ልማት
ሸዋ-ደብረብርሃን የቱሪዝም ልማት ጥሪ
የልዕለ ኃያላንና አገር መሥራቾች መውጫ በር፣ የንዑዳን ቀዬ፣ የብርቅዬ ተፈጥሮና መልክዓ-ምድር መገኛና የታሪክ ማኅደር  የሆነችው ሁለተኛዋ የሸዋ መናገሻ ፣ የንጉሥ ዘርዓ ያዕቆብ ማህተመ-ሥሪት ደብረብረሃን ከሰሜን ሸዋ ዞንና ከአጋር አካላት ጋር በመሆን   በከተማውና አካባቢው የሚገኙ ታላላቅ ታሪካዊ፣ ተፈትሯዊና ሠው-ሰራሽ መስህቦችን፣ ቦታዎችንና ቅርሶችን  ለማልማት፣ ለመንከባከብና የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ የሚያስችል የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ-ግብር የክብር የንጉሥ እራት ደግሳለች።
በዚህም ታሪካዊ የቱሪዝም ልማትና ማስፋፊያ ፕሮግራም ዳግማዊ ዐጤ ምኒልክ ኃይለመለኮት ከየካቲት 1870 ዓ.ም እስከ ታሕሳስ 1878 ዓ.ም በነበረው የንግሥና ዘመናቸው የመሰረቱት የመጀመሪያው የልቼ ቤተ መንግሥት እና አንጎለላ በመፈራረስ ላይ የሚገኘው የንጉሥ ሣሕለሥላሴ ወሰንሰገድ አብያተ መንግስታት ይገኙበታል፡፡

እነሆ ጳጉሜ 3 ቀን 2014 ዓ.ም  በአዲስ ዓመት ዋዜማ  በደብረብርሃን ከተማ ጌትቫ ሆቴል ከቀኑ 10 ሰዓት ጀምሮ በተዘጋጀው የክብር እራት ላይ በመገኘት ባለሃብቱ፣ ተወላጁ፣ ሀገርና ታሪክ ወዳድ ሁሉ ርብርብ እንዲያደርግ አለማቀፋዊ ጥሪ ተደርጓል።
ይምጡ!
የከበረ የንጉሥ እልፍኝ ታዳሚ ይሁኑ!
በተከበረ የንጉሥ እራት ኪነ ጥበባዊ መሰናዶ ደምቀን ተጋግዘን የአባቶቻችንን ታሪክ ዳግም ለትውልድ እናኑር!

የክብር እራት መግቢያውን ከአስተባባሪዎች ያግኙ፡፡
ለተጨማሪ መረጃ ከታች ባሉት ቁጥሮች ይደውሉ
09 10 54 49 20
0973 04 56 55
09 91 91 91 64
09 10 11 94 11
09 11 94 87 77
38.5K viewsAyu, 16:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 13:15:33 ደደቢት
በደደቢት መስመር ያለው የጠላት ሃይል በጥይት አቅርቦት እጥረት ምክንያት እርስ በእርስ መተሳሰር እንዳልቻለ እየተገለጸ የሚገኝ ሲሆን የጥይት አቅርቦት የማግኘት እድሉ አነስተኛ በመሆኑ በአካባቢው የሚገኝ ታጣቂ በጥንቃቄ ለወገን ሃይል እጅ ለመስጠት እንደሚፈልግ የሚገልጽ መልእክት በአርሶ አደሮች አማካኝነት ለወገን እየላከ እንደሚገኝ እይተገለጸ ነው።
=================
ስለጦርነቱ ቶሎ ቶሎ መረጃ ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ
http://t.me/ayuzehabesha http://t.me/ayuzehabesha
http://t.me/ayuzehabesha http://t.me/ayuzehabesha
"በውሸት አካውንት እንዳትሸወዱ
14.6K viewsAyu, 10:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 12:40:19 ኦነግ ሸኔ በኢሉባቡር ዶረኒ ወረዳ ወረቦ ቀበሌ ገብቶ ጥምባ በምትባል አካባቢ ተኩስ ከፍቶ እንደነበር መዘገቤ ይታወሳል።
አሁን ወደ ቦታው የፀጥታ ሀይል የተንቀሳቀሰ ሲሆን አሁንም ወረቦ ላይ ኦነግ ሸኔ ሱቆችን እየዘረፈ ነው ሲሉ የአካባቢው ነዋሪዎች ገልፀውልኛል።
ሼኔዎቹም አሁንም ሐይል ጨምረው ከአልጌ እየመጡ ነው።
=================
ስለጦርነቱ ቶሎ ቶሎ መረጃ ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ
http://t.me/ayuzehabesha    http://t.me/ayuzehabesha
http://t.me/ayuzehabesha   http://t.me/ayuzehabesha
"በውሸት አካውንት እንዳትሸወዱ
19.1K viewsAyu, edited  09:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 12:34:00 ከበረከት ሁመራ ግንባር የሸሸው የህወሃት ታጣቂ ወደ ሱዳን በመሻገር አሻባ በሚባለዉ የስደተኞች ካምፕ ዉስጥ አስጠልሉኝ በሚል  ልመና ውስጥ ገብቷል። ሱዳኖች ግን በመጣቹበት እግራችሁ ተመለሱ እያሉ ሲሆን ታጣቂውን ለኢትዮጵያ መንግስት አሳልፈው ለመስጠት በአንድ ቦታ ላይ እያሰባሰቡት መሆኑን ከወደ ሱዳን የተገኙ መረጃዎች ይጠቁማሉ። በዚህ ግንባር ከ5 ምሽጎች ውስጥ 4ቱ ተደርምሰዋል።
=================
ስለጦርነቱ ቶሎ ቶሎ መረጃ ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ
http://t.me/ayuzehabesha    http://t.me/ayuzehabesha
http://t.me/ayuzehabesha   http://t.me/ayuzehabesha
"በውሸት አካውንት እንዳትሸወዱ
19.7K viewsAyu, edited  09:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 12:09:32 በጎንደር ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ምክር ቤት የተላለፈ ውሳኔ
ለመላው የጎንደር ህዝብ ለሶስተኛ ዙር አገራችን ለማፈራረስ ወራሪዉ ሃይል ጦርነት ለኩሷል ፡፡
ስለሆነም አሁን ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ ግምት ውስጥ በማስገባት የጎንደር ከተማ የፀጥታ ምክር ቤት የሚከተሉትን ውሳኔዎች አስተላልፏል፡፡
ጥምር ጦራችን በሁሉም ግንባር በሙሉ ብቃትና ወኔ ጠላትን እየመከተ እየደመሰሰ ይገኛል፡፡ ስለሆነም የጎንደር ከተማ አስተዳደርና የፀጥታ ምክር ቤት ማህበረሰባችን ራሱን ማዘጋጀትና የከተማችን ሰላምና ደህንነት ለመጠበቅ ሲባል
የሚከተሉትን ውሳኔዎች አስተላልፏል፡፡
1. ከፀጥታ መዋቅሩ ውጭ፣ በከተማችን በብሎክ አደረጃጀት አካባቢን እንዲጠብቅ በተሰጠው ተራው ከተሰማራው ውጭ በየትኛውም ቦታ የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ የተከለከለ ነው፡፡
2. ከተፈቀደላቸው የፀጥታ አካላት ውጭ የተለያዩ የፀጥታ አካላት አልባሳትን መልበስ የተከለከለ ነው፡፡
3. ማህበረሰቡን የሚያውኩ አሉባልታዎች ወይም የሃሰት መረጃዎችን በተለያዩ ሚዲያዎች፣ በመጠጥ ቤቶች ወዘተ ማሰራጨት ህዝቡን ማወዛገብ ማሰጨነቅ በጥብቅ የተከለከለ ነው፡፡
4. በከተማችን የሚገኙ ተፈናቃዮች ከተሰጣቸው መጠለያ ካምፕ ውጭ መንቀሳቀስ የተከለከለ ሲሆን ለገበያ፣ ለህክምና፣ ለአንገብጋቢ ጉዳዮች፣ ለተለያዩ ስራዎች ከመጠለያው መውጣት ያለበት ተፈናቃይ በሚመለከታቸው የካምፕ አስተባባሪዎችና በክ/ከተማው የፀጥታ መዋቅር እውቅና እና የመውጫና የመግቢያ ፈቃድ መለያ ካርድ ይዞ ተመዝግቦ ተፈቅዶለት የሚንቀሳቀስ ይሆናል፡፡
5. በተለያዩ አሉባልታ ወሬዎችና ስበብ በመፈለግ ለህዝብ አገልግሎት የሚሰጡ እንደ ባንክ ቤት፣ ሱቆችና ሆቴሎች፣ የገበያ ማዕከሎች እና የመሳሰሉትን መዝጋት የተከለከለ ነው፡፡
6. ማንኛውም የግል ሆነ የመንግስት ተሸከርካሪ ለፀጥታ ስራ ሆነ ለዘመቻ የሠው ሃይል ለማንቀሳቀስ በሚመለከታቸው የዘመቻ ማምሪያ ኮማንድ ፖስት ትብብር ሲጠየቅ የመተባበር ግዴታ አለበት ላለመተባበር ተሸከርካሪን የሚሸሽግ፣ የሚያሸሽ ሆን ብሎ ተበላሸ በሚል ላለመተባበር ጥረት የሚያደርግ ተጠያቂና የጥፋት ኃይሎች ተባባሪ ተደርጎ ስለሚቆጠር ከዚህ አይነት ጥፋት በመቆጠብ ኃላፊነትን መወጣት ይገባል፡፡
7. ማንኛውም የቤት አከራይ ወይም አልጋ የሚያከራይ፣ ሆቴሎች፣ ፔንሲዮኖች ተከራዮቻቸውን እና ተጠቃሚዎቻቸውን የመለየትና ማንነታቸውን የመለየት፣ የታደሰ ህጋዊ መታወቂያ ስለመኖራቸው የማረጋገጥ ግዴታ እና አስፈላጊውን መረጃ ይዞ ለጸጥታ አካል ሪፖርት የማድረግ ኃላፊነትና ግዴታ አለበት
8. ማንኛውም ሰው ፀጉረ ልውጥ ሰው ሲያጋጥመው በቅርብ ለሚገኝ የፀጥታ አካል የመጠቆም ኃላፊነት አለበት
9. ከነሀሴ 27/2014 ዓ.ም ጀምሮ የቀበሌ መታወቂያ መስጠት የተከለከለ ሲሆን አስቸኳይ የሆነ ጉዳይ የገጠመው ለምሳሌ ለህክምና መታወቂያ ቢያስፈልግ፣ ወደ ዩኒቨርስቲ ለመሄድ ቢያስፈልግ፣ ወደ ውጭ አገር የሚያስፈልግ ጉዞ የመሳሰሉት አስቸኳይ ጉዳዮች ከገጠሙና መታወቂያ መስጠት ካስፈለገ የክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚና የክ/ከተማው ሰላምና ደህንነት በጋራ በማየት መታወቂያ የመስጠት ፈቃድ ሊሰጡ ይችላሉ
10. ማንኛውም የመንግስት የግል ታጣቂ አካባቢውን በብሎክ አደረጃጀት ውስጥ በመካተት በየደረጃው ያለ የፀጥታ አካላት በሚሰጠው ስምሪት አካባቢውን የመጠበቅ ኃላፊነት ግዴታ አለበት
11. አግባብነት የሌለው የዋጋ ንረት የሚፈጥሩ በሸቀጦች በግብርና ምርቶች ላይ ተገቢ ያልሆነ ዋጋ ጨምሮ ህዝቡን ማስቃየት በጥብቅ የተከለከለ ነው፡፡
12. ከከተማ ውጭ ወደ ከተማው ለጸጥታ ስራ፣ ሆነ የጦር ,መሳሪያ ይዞ ወደ ከተማው መግባት አስፈላጊ ለሆኑ ስራዎች የሚንቀሳቀስ ማንኛውም አካል ለስራ ከተላከበት አካባቢ ከሚመለከተው የፀጥታ አካል የይለፍ ደብዳቤና መታወቂያ መያዝ ግዴታ አለበት
13. ወቅታዊ ሁኔታውን እንደምቹ ሁኔታ ተጠቅሞ በህገ ወጥ ስራዎች፣ በህገ ወጥ ግንባታ መሰማራት ከወራሪው ኃይል ያልተለየ ጥፋት ተደርጎ የሚወሰድ መሆኑን በመገንዘብ ከዚህ አይነት ጥፋት ማንኛውም ሰው መቆጠብ አለበት
14. በጫት ቤቶች ተሰብስቦ በመቃም አሉባልታና ሽብር መንዛት የተከለከለ ነው
15. ተገቢ ያልሆነ ምክኒያት የሌለዉ የቤት ኪራይ ጭማሪ ማድረግ በህዝቡ ላይ ሌላ ጫና መፍጠር በመሆኑ ክዚሀ ብፊተ የከተማዉ ምክር ቤት የወሰነዉ ዉሳኔ በቤት ኪራይ ዋጋ መጨመር ክልከላዉ እንደተጠበቀ የሚቀጥል ይሆናል
በአጠቃላይ የጎንደር ህዝብ ወራሪ ኃይሉን ለመመከትና ለመደምሰስ በሚደረገው ዘመቻ ከመቸውም ጊዜ በላይ አንድ በመሆን በግንባር በመዝመት፣ አካባቢን በመጠበቅ በሎጀስቲክ በማሰባሰብ ህዝባችን እንዲሳተፍ የፀጥታ ም/ቤቱ ጥሪ እያቀረበ ከላይ የተዘረዘሩትን ውሳኔዎች ማንኛውም አካል የማክበርና ኃላፊነቱን የመወጣት ግዴታ ያለበት መሆኑንና ይህን ውሳኔ የማያከበር የፀጥታ መዋቅሩ አስፈላጊውን የእርምት እርምጃ ሊወስድ እንደሚችል በአጽእኖት ያሳውቃል፡፡
የጎንደር ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ምክር ቤት
ነሀሴ 27/2014 ዓ.ም
ጎንደር፣
==================
ስለጦርነቱ ቶሎ ቶሎ መረጃ ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ
http://t.me/ayuzehabesha http://t.me/ayuzehabesha
http://t.me/ayuzehabesha http://t.me/ayuzehabesha
"በውሸት አካውንት እንዳትሸወዱ
21.5K viewsAyu, edited  09:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 12:02:48
ትዘርፋላችሁ ተብለው እናቶች ጭምር መጥተዋል። ትህነግ አማራ ጠላታችሁ ነው ብሎ የሚያስተምረው ጥላቻ አልበቃ ብሎት በአደንዛዥ ዕፅ አጡዞ ያመጣቸው የህዝባዊ መአበል የሚለው ስልት ተሳታፊ ናቸው። ህወሃት በዚህ መልኩ ነው የትግራይን ህዘብ ከሁሉም አጎራባች ክልሎች ጋር ደም እያቃባ ያለው።
==================
ስለጦርነቱ ቶሎ ቶሎ መረጃ ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ
http://t.me/ayuzehabesha http://t.me/ayuzehabesha
http://t.me/ayuzehabesha http://t.me/ayuzehabesha
"በውሸት አካውንት እንዳትሸወዱ
21.5K viewsAyu, edited  09:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 11:52:23 በጎብዬ ሸማኔ ቀበሌ ላይ ስበሰባ ላይ በነበሩ የህወሓት ታጣቂዎች ላይ ድሮን ጥቃት ፈፅሟል።
በዚህም በርካታ ታጣቂዎች ሞተዋል።
ዛሬም በወርቄ አቅጣጫ ከፍተኛ ውጊያ እየተካሄደ ነው። አዩ ዘሀበሻ
==================
ስለጦርነቱ ቶሎ ቶሎ መረጃ ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ
http://t.me/ayuzehabesha http://t.me/ayuzehabesha
http://t.me/ayuzehabesha http://t.me/ayuzehabesha
"በውሸት አካውንት እንዳትሸወዱ
22.4K viewsAyu, edited  08:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 11:38:32 በወልቃይት በረከት እና ሉግዲ መሃከል በህወሓት ከሰራው 5 ግዙፍ ምሽጎች መካከል ከትናንት በስቲያ፣ትናንትና ዛሬ 4 መሰበሩ ታውቋል።
አዩ ዘሀበሻ
==================
ስለጦርነቱ ቶሎ ቶሎ መረጃ ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ
http://t.me/ayuzehabesha http://t.me/ayuzehabesha
http://t.me/ayuzehabesha http://t.me/ayuzehabesha
"በውሸት አካውንት እንዳትሸወዱ
23.7K viewsAyu, edited  08:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ