2022-09-03 11:19:04
አሜሪካ ለታይዋን ከ1 ቢሊዮን ዶላር በላይ የዋጋ ግምት ያላቸውን የጦር መሳሪያዎች ልትሸጥላት ነው፡፡
የጦር መሳሪያ ሽያጩ እቅዱ በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ተቀባይነት ማግኘቱን ፕሬንሳ ላቲና ፅፏል፡፡
ውሳኔው ቻይናን በእጅጉ ማስቆጣቱ ተሰምቷል፡፡
ለታይዋን የሚሰጡት ዘመን አፈራሽ ፀረ መርከብ ሚሳየሎች እና ራዳሮችን እንደሚጨምር ታውቋል፡፡
ቻይና ለዚህ አፀፋ ይኖረኛል ማለቷ በዘገባው ተጠቅሷል፡፡
ታይዋን ራሴን የቻልኩ አገር ነኝ ብትልም ቻይና ታይዋንን እንዳፈነገጠች ግዛቷ ነው የምታያት፡፡
ቻይና በቅርቡ የአሜሪካ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ናንሲ ፔሎሲ ታይዋንን መጎብኘታቸውን ተከትሎ በደሴቲቱ ዙሪያ ገባ በታሪኳ ታላቅ ነው የተባለ የጦር ልምምድ ማድረጓን ዘገባው አስታውሷል፡፡
ለዩቱብ ተጠቃሚዎች
በዩቱብ ቻናላችን በቅርብ ቀን ፈጣን፤እውነተኛ እና ሚዛናዊ መረጃዎችን በምርጥ አቀራረብ እንጀምራለን፤ሰብስክራይብ እያደረጉ ይጠብቁን፡፡
አዩ ዘ ሀበሻ
በዚች ሊንክ ሰብስክራይብ ያድረጉን https://www.youtube.com/channel/UCU7EgWx5JV0TO81iqGVKPeQ
10.2K viewsAyu, edited 08:19