2022-09-05 10:55:36
ሰቆጣ
በአሁኑ ሰዓት ሰቆጣና አካባቢዋ ምንም አይነት ጦርነት የለም።
ትላንት በነበረው ጦርነት በርካታ የህወሃት ሀይሎች ሞተዋል።
የተረፉትም የህወሓት ታጣቂዎች ጥራሪ ወንዝን ተሻግረው ሄደዋል።
ወለህ እና ቲያ ቀበሌ ላይ በርካታ የህወሓት ታጣቂዎችን አስኬረን የአካባቢው ማህበረሰብ አፈር ሲያለብስ አርፍዷል።
በአሁኑ ስዓት ሰቆጣ ሱቆችም ተከፍተዋል፤ የትራንስፖርት አገልግሎትም ስራ ጀምረዋል፤ መብራትም ማታ ማታ ይለቀቅልናል፤ የሰላሙ ሁኔታ እጅግ አስተማማኝ ነው።
በዚህ ግንባር የነበሩ የመከላከያ አባላት የዋግን ህዝብ ደጀንነት በቃል ለመግለጽ በሚከብድ መልኩ አመስግነዋል። ደጀንነት ዋግኽምራ ህዝብ
=======
በራያ ግንባር በወርቄ በኩል የሀራን መስመር ለመያዝ የተረፈውን ሀይሉን አሰባስቦ ዛሬ ማለዳ ላይ ድጋሚ ተኩስ ከፍቷል።
ትላንት በ29/12/2014 ከአራዶም እና ሮቢት ተንቀሳቅሶ በአራፋ ጊወርጊስ በማቅናት በቀይ አፈርና ተኩለሽ መካከል ዘሎ በመግባት ጥምር ሃይሉን በመቁረጥ ለሁለት ሊከፍል የነበረው ብዛት ያለው የህውሃት ታጣቂ እንደቅጠል እረግፏል፤የተወሰኑት እጅ ሰጥተው ህይዎታቸውን መታደግ ችለዋል።
በአላውሃ በኩል ያፈገፈጉ ይመስላል፣ የከባድ መሳሪያ ድምፅ አልፎ አልፎ ነው የሚሰማን የሚል መረጃ ከአካባቢው ነዋሪዎች አግኝቻለሁ።
================
በአዳርቃይ ግንባር ህወሃት ያልጠበቀው ምት ነው የደረሰበት፣ በርካታ የህወሓት ታጣቂዎች እጅ ሰጥተዋል። ከባድ መሳሪያቸውን ጭምር ይዞ ለመሄድ ጊዜ አላገኙም። አድዐርቃይ ሙሉ ለሙሉ ነፃ ወጥታለች።
ዛሬ የዘገየሁት አንዳንድ ቦታ ስልክ አልሰራ ብሎኝ ነው።
አዩ ዘሀበሻ
ነሃሴ 30/2014 ዓ.ም
ከረፋዱ- 4:55
ተጨማሪ መረጃዎች ይኖራሉ፣ የቻናሌ ቤተሰብ በመሆን ተከታተሉ
http://t.me/ayuzehabesha http://t.me/ayuzehabesha
17.1K viewsAyu, edited 07:55