2022-07-14 20:50:36
#በጋምቤላ የሰዓት ገደብ ተጣለ
በጋምቤላ ከተማ ካለው ወቅታዊ ሁኔታ ጋር በተያያዘ ሕገወጥ እንቅስቃሴን ለመቆጣጠር የሰዓት እላፊ ገደብ መጣሉን የክልሉ መንግስት አስታውቋል።
ከዚህ ቀደም በጋምቤላ ከተማ ተከስቶ በነበረው የፀጥታ መደፍረስ ምክንያት የሰዓት እላፊ ተጥሎ እንደነበር ይታወሳል።
ይሁን እንጂ ለማህበረሰቡ ደህንነት ታስቦ የተጣለው የሰዓት እላፊ ገደብ ተግባራዊ ከማድረግ አንፃር ክፍተት መታየቱን ተገልጿል።
በዙህም በከተማው የሰዎች እና የተሽከርካሪዎች እንቅስቃሴን በመለየት ከምሽቱ 2 ሰዓት እስከ ንጋቱ 11፡30 ድረስ የተጣለው ገደብ ተግባራዊ ሊደረግ ይገባል ተብሏል።
ከአንቡላንስና ከፀጥታ ሀይል ተሽከርካሪ በስተቀር ማንኛውም ተሽከርካሪና ሰዎች መንቀሳቀስ የሚችሉት ከንጋቱ 11፡30 እስከ ምሽቱ 2 ሰዓት መሆኑ ማሳሰቢያ ተላልፏል።
በአሁኑ ወቅት በጋምቤላ ከተማ ሰላማዊ ሁኔታ መኖሩ የተገለፀ ሲሆን በየደረጃው የሚገኙ የጸጥታ ሃይሎች የተጠናከረ ጥበቃ እያደረጉ ነው ተብሏል።
ህብረተሰቡ በየአካባቢው ተደራጅቶ መረጃ በመስጠት እገዛ እንዲያደርግ ጥሪ ቀርቧል።
======================
ማሳሰቢያ
የውሸት አካውንት የከፈቱ ስላሉ እንዳትሸወዱ፣ትክክለኛ የቴሌግራም ቻናላችን ሊንክ ይሄ ብቻ ነው t.me/ayuzehabesha
"መረጃ ህይወት ነው"
9.6K viewsAyu, edited 17:50