2023-02-08 19:28:59
ባለቤታቸው ያልታወቁ አደገኛ መልእክቶች፣ በግድግዳ፣ በፖል፣ በአጥር...ተለጥፈው በዚሁ ሶሻል ሚዲያ ላይ ሲይዘዋወሩ ተመልክቻለሁ። የመልእክቶቹ ይዘት በአጭሩ ብሔር ከብሔር፣ ሃይማኖትን ከሃይማኖት የሚጋጩ ሆነው አግቻቸዋለሁ። በተለይ ደግሞ ቅድስት ቤተክርስትያን ይዛ የተነሳችውን፣ ህጋዊና ሰላማዊ ትግል ጥላሸት የሚቀባ ነው። የደንበር አጥር፣ የዘር፣ የቀለም፣ የብሔር ገደብ፣ የፖለቲካዊ ርዕዮተ ዓለም ልዩነት የሌላትን የቅድስት ቤተክርስቲያንን ምዕመን ለመከፋፈል ያለመም ነው።
ስለሆነም የኦርቶዶክስ ልጆች ከላይ የገለጽኳቸውን ይዘት ያላቸውን መልዕክቶች በአካል የሚለጥፉ ሰዎችን ካያችሁ በእርግጠኝነት ለጠፊዎቹ ከኦርቶዶክሳዊያን ወገን አይደሉምና ለሚመለከተው የህግ አካል አሳልፎ መስጠት ይጠበቃል ብዬ አምናለሁ።
በሶሻል ሚዲያም ከኦርቶዶክሳዊነት አስተምሮ ያፈነገጡና ኦሮቶዶክሳዊያንን የሚከፋፍሉ መልእክቶችን የሚያስተላልፉትን ቢቻል መክሮ ማስተካከል፣ ካልተቻለ ደግሞ አደገኛ መልእክታቸው እንዳይስፋፋ ማድረግ ይጠበቅብናል ባይነኝ። ቢያንስ ሼር፣ ላይክ፣ ኮሜንት፣ ፎሎ ባለማድርግ የድርሻችን ልንወጣ ይገባል። በአጠቃላይ ከቅዱስ ሲኖዶስ እውቅና ውጭ የሆኑ መልእክቶችን ባለመቀበልና ባለማስተላለፍ የድርሻችን እንወጣ እላለሁ።
፩ ቅድስት ቤተክርስቲያን
፩ ቅዱስ ሲኖዶስ
፩ መንበረ-ፓትርያሪክ
1.9K viewsedited 16:28