2023-02-06 18:58:59
እኛ ከበረታን...
በብሔር፣ በዘር፣ በቋንቋ ለያዩን። በሀሰት ትርክት አባሉን። ግን አንዲት ጥላ ቀርታን ነበር። ጨርሰን እንዳንጠፋ አጋምዳና አንድ አድርጋ የያዘችን። ንጽሂት ቅድስት ቤተክርስትያን የመትባል ተስፋ ቀርታን ነበር።
በብሔር፣ በቋንቋ፣ በዘር፣ በፖለቲካ ልዩነት የሚባሉ ወገኖች በኦርቶዶክሳዊነታቸው ግን ጨርሰው እንዳይጠፋፉ ሆኑ። ኦሮሞ፣ አማራ፣ ትግሬ፣ ከባታ፣ ሃድያ፣ ጉራጌ፣ ጋሞ...ወዘተ ብሔሩ የሆነና በብሔር ተለያይቶ በኦርቶዶክሳዊነቱ ግን አንድ ሆነ። ከጨርሶ መጠፋፋት ዳነ።
ብልጽግና፣ ኢዜማ፣ አብን፣ ህወሃት...ወዘተ የሚባሉ ፓርቲዎች አባል የሆኑ በፖለቲካዊ ርዕዮተ-ዓለም የተለያዩ አንዳንዴም ለመጠፋፋት የሚተዳደኑ በኦርቶዶክሳዊነታቸው ግን አንድ ሆኑ። በኦርቶዶክሳዊነታቸው በቅጽሯ ግቢ ተገናኙ።
ታዲያሳ? ታዲያማ:-
በሁሉም ከፋፈለውን የቀረችን አንዲት ጥላ ናት። እሷም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ትባላለች። ነገር ግን በሀሰት ትርክት የአንድነታችንን ገመዶች ሁሉ የበጡሱ አሁን ደገሞ በቀረቸው መጥተዋል። አንዲት መሰባሰቢያ እንኳን እንዳትኖረን ሊንዷት ተነስተዋል።
እኛ ማወቅ ያለብን፣ ከሰነፍን ይሳካላቸዋል። ከበረታን ግን አይደለም የቀረችውን መሰባሰቢያችንን ሊንዷትና ሊበጥሷት ነውና ከዚህ ቀደም የበጣጠሷቸውን መልሰን እንቀጥላቸዋለን። መልሰን እንገነባቸዋለን። የቀረችውን የማሰባሰቢያ ጥላችን ለመታደግም ሆነ፣ የሀሰት ትርክቱን ንደን የተበጠሱትን የአንድነቶቻችን ገመዶች መልሰን ለመቀጠል እንደ ከዚህ ቀደሙ በብሔር፣ በዘር፣ በቋንቋ...መፈራረጁን፣ እጣት መጠቋቆሙን፣ መጠላላቱን፣ መባላቱን...እንተወው። ከሁላችንም ወገን ነውረኛ አለ። በነውረኞች ሁሉንም እየጀመልን ለዛሬው ውድቀታችን በቅተናል። በጠላቶቻችን ወጥመድ ዘው ብለን ስንገባ ኑረናል። ይሰመርበት። እኛ ስንባላ፣ ሁላችንንም ጨርሶ የሚሰለቅጥ የመጣ መሆኑንን ልብ ማለት ያስፈልጋል።
2.4K viewsedited 15:58