Get Mystery Box with random crypto!

Amde Ezra

የቴሌግራም ቻናል አርማ amde123 — Amde Ezra A
የቴሌግራም ቻናል አርማ amde123 — Amde Ezra
የሰርጥ አድራሻ: @amde123
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 10.51K
የሰርጥ መግለጫ

የመረጃ መስመር

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-06-29 19:47:14 አተኳኮስ ትጣለህ!!

እናተዬ ዘርሮ ነው የጣለው እኮ። አዲስ አበባ ልደታ አካባቢ የጀበና ቡና ለመጠጣት ከናቱ ማህጸን እንደወጣ እንደ መጨረቅ እንቦሳ ከሚያረገርግ እግረ-ተከል የፕላስቲክ ወንበር ላይ ተቀምጫለሁ።

ፊት...ለፊቴ ደግሞ ወጣቶች ከበዋል። ወጣቶቹ በወሪያቸው እንደ ተረዳሁት የተለያየ የብሔር ማንነት ያላቸው ናቸው። ከመካከላቸውም ህሉፍ የሚባል የትግራይ ብሔር ተወላጅ ነበረ።

የህሉፍን ሥምም ሆነ የብሔር ማንነቱን ማወቅ የቻልኩት ከበው ካሉት ወጣቶች መካከል አንዱ ስሙን ጠርቶ ግብረመልስ ሲሰጠው ነው። ህሉፍ በክርክሩ እምብዛም ተናጋሪ አልነበረም። በአብዛኛው አድማጭ ነበር።

የመከራከሪያም በሉት የመወያያ ርዕሳቸው ደግሞ ስፖርታዊ ነው። ስፖርታዊ ርስዕሱ ከአገር ውስጥ እስከ ውጪ አገራት ያሉትን ክለቦች ያዳረሰ ነበር። ከአገር ውስጥ እነቡና፣ እነቅዱስ ጊዮርጊስ፣ እነፋሲል...ከውጪ ደግሞ እነማንችስተር ዩናይትድ፣ እነአርሴናል፣ እነማንችስተር ሲቲ...የመሳሰሉት የእግርኳስ ክለቦች መነጋገሪያ ነበሩ። በተለይ በተጫዋቾች የዝውር ገቢያው ላይ ለሚደግፏቸው ክለቦች ከፔፕ ጋርዲዮላ፣ ከሚካኤል አርቴታ፣ ከእሪክ ቲህናግ...በላይ ሆነው "ምን አለ እከሌ የሚባለውን ተጫዋች ብንገዛው? እሱን እማ መግዛት ይኖርብናል!! አንዴ መልስ የሌለው ጥያቄ፣ ሌላ ጊዜ ደግሞ ፓውንድ መዥላጭና ወሳኝ ሆነው ይደመድማሉ። ለእየሚደግፉት ክለባቸው ይስማማል የሚሏቸውን ተጫዋቾች እያነሱ "በምኞት አይከለከል።" ብሂል ይብከነከናሉ።

እንግዲህ በዚህ ክርክር መሃል ላይ ነው ሚሳኤሉ የተወነጨፈው። ተኩሱ የፈነዳው። ምን አለ ህሉፍ እስከመጨረሻው አድማጭ ሆኖ ቢቀጥል ኖሮ ያስብላል። ህሉፍ ምላሱን ሲበለዋ፣ ሲያቅለበልበው...

"እውነት ለመናገር ዲክላር ራስ ግን 105 ሚሊዬን ፓውንድ የሚያወጣ ተጫዋች ሆኖ ነው አርሴናል ሊገዛው የተስማማው?" ብሎ በጥያቄ ጀምሮ የሚካኤል አርቴታን ቀሽምነት ለማብራራት አፉን እያሾለ ሳለ...

አንዱ የአርሴናል ደጋፊ የሆነ ወጣት:- የህሉፍን ንግግር ከምላሱ ላይ አፈፍ አድርጎ
"ማነህ? ህሉፉ ቆይ...ቆይ...አንድ ጊዜ ቆዬኝ እማ? እየውልህ ህሉፉ አንተ #ስለፓራ #ኦሎፒክ ማውራት ስንጀምር ያ...ኔ በደንብ ማብራሪያ ትሰጣለህ።" ብሎት እርፍ።

ከዚህ በላይ የምላስ ተኩስ አለ እንዴ? የእውነት አተኳኮስ ትጠላለህ
2.8K viewsedited  16:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-25 22:11:48 ትንቢታችን ደረሰና የጥሞና ጊዚያችን ጥሰን መጣን። ግማሽ ደርዘን የሚሆኑ የኢዜማ ከፍተኛ አመራሮች ከኢዜማ መልቀቃቸውን ነገሩን። ግን ከዛሬ አራት ዓመታት ከመንፈቅ በፊት የፌስቡክ ሊኩን በመጫን "ማን ያርዳ የቀበረ፤ ማን ይነገር የነበረ።" እንዲል ከናሁ ቴሌቪዥን ጋር በነበረን ምን ብለን ነበር? ከስር ያለውን የፌስቡክ ሊንክ በመጫን የሰጣናቸውን ምስክርነት በቪዲዮ ያዳምጡ...

https://fb.watch/kLqG3AmbSk/?mibextid=Nif5oz
3.2K viewsedited  19:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-30 16:51:37 የምናባዊው የ"ስኳድ" ሰነድ ደራሲዎች...


እዳ እኮ ነው ጎበዝ። ደግሞ በሽታቸው አገርሽቷል። ተነስቶባቸዋል። አየር ላይ ወይም ምንብ ላይ የፈጠሩትን "በበሬ ወለደ" ትርክት መሬት ላይ ለማወረድ እየተጋጋጡ ነው። ጥቁሩን በረጅም ምላሳቸው ፍቀው ነጭ ለማድረግ እየተጉ ነው።

የምናባዊው የ"ስኳድ" ሰነድ ደራሲዎች የፖለቲካ ኃይል አሰላለፉ መልኩን በቀየረበት በዚህ ወቅት የሰነዱን አቧራ አራግፈው ከተፍ ብለዋል። የተቀናጄ ዘመቻ ጀምረዋል።

እንዳልኩት የፖለቲካዊ ኃይል አሰላለፉ በተቀያየረበት ወቅት ምናባዊ ድርሰታቸውን ለምን ሰሞኑን እንደ አዲስ ይዘውት ከች አሉ? ለምን እንደ አዲስ እንድን አካባቢ ታርጌት አድርገው የተቀናጀ ዘመቻ ጀመሩ? የአሁኑ ዘመቻ ዓላማውና ግቡ ምንድን ነው?

ወዳጄ "ጠርጥር ከገንፎ አይጠፋም ስንጥር" እንዲል የሰነዱ ደራሲዎች ያውም በዚህ ወቅት የጀመሩትን የተቀናጀ ዘመቻ፣ በቅጥፈት ዘመቻው ታርጌት የተደረክ የአንድ የአካባቢ ተወላጅ ሁሉ መርምር። ከተሳለብህ ሰይፍ የምትተርፍበትን ብልሃት ቀምር።

መልዕክቴ ይሄው ነው።
422 viewsedited  13:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-29 17:13:45
1.4K views14:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-29 17:13:37 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ውጤት ካጣ በሆላ ከአሰልጣኝ ውበቱ አባተ ጋር Mulualem G. Medhin በ ያደረገረኩት አጠር ያለ ቆይታ ይህን ይመስላል፦

ሙሉዓለም፦ ወንድማለም ይሄው አንተ የአሰልጣኝነቱን ኃላፊነት ከተቀበልክ ጊዜ ጀምሮ ብሔራዊ ቡድኑ ከአገኘው ጋር እየተላተመ አያሌ ቀይ ካርድ እና ቢጫ ካርድ እየተሰጠው ነው ምንድን ነው ችግሩ?

አሰልጣኝ ውበቱ፦ ትክክል ነህ ሙሌ፣ ብዙ ችግር ነበረብን። ከካርድ በተጨማሪ በርካታ የቅጣት ምቶችም ተሰጠውብን ብዙ ተጎድተናል። ይችን ሦስት ቀን ግን ምንም ካርድ አላየንም፤ ቅጣት ምትም አልተመታብንም። ሰው ግን በዚች ሦስት ቀን ውስጥ ምን ያህል ቡድናችን ሰላም እንደሆነ አልተረዳልንም።

ሙሉዓለም፦ ይሄ ሰላም ከየት ነው የመጣው?

አሰልጣኝ ውብቱ፦ በርግጥ በዚች ሦስት ቀን ውስጥ ምንም ጨዋታ ስላልነበረን ነው።

ሙሉዓለም፦ እሺ ቡድኑ ከእፍሪካ ዋንጫ ውጪ እንዲሆን በማድረግህስ ከኃላፊነትህ አትለቅም ወይ

አሰልጣኝ ውበቱ፦ ለምንድን ነው የምለቀው? ጥያቄው መሆን የነበረበት 'ሁሉም የቡድኑ አባላት መልቀቅ አለባቸው፤ እነሱ ብቻ ሳይሆኑ ኢሳያስ ጅራም መልቀቅ አለባት። የአትሌትክስ አሰልጣኝዋ ደራርቱ ቱሉም መልቀቅ አለባት፣ እሷም ብትሆን የሯጮች አለቃ ናት፤ ስፖርት ከተባለ ደግሞ ሁሉም ስፖርት ነው። ስለዚህም የቦክስ ፌድሬሽን አለቃም፣ የቼዝ ፌድሬሽን አለቃም መልቀቅ አለባቸው። ኃላፊነቱ የሁሉም ነው።

ነገር ዓለሙ ሁሉ 'ግንጊልቻ'

Mulualem G. Medhin
1.4K views14:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-29 14:11:40
1.7K views11:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-29 14:11:36 አቶ ለጥ!! ሰጥ ይበሉ
1.7K views11:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-27 19:32:57 ኢትዮጵያ ማለት እንዲህ ናት...

የማየት አቅሙ ያላችሁ ህጻኗን ተመልከቷት። እኔ ቪዲዮውን በእንባ ነው የጨረስኩት። በጸጸት ነው የቋጨሁት። ሙሉውን ከፈለጋችሁ ከEBS ቴሌቪዥን ዩቱዩብ ገጽ ታገኙታላችሁ...

አባቷ ወታደር ነበር። "አገር ለማዳን" በሚል በጦርነቱ ተሰውቷል። በመጨረሻም የዳነው ሌላ ነው። "አገር ማዳን" የሚለው ያሁሉ ፕሮፖጋንዳ ማን እንደዳነ አውቀነዋል። እንኳን እንደ ዝች ምስኪን ህጻን አባት ደፋ ብለን አልቀረን። ተመስገን።

እንዳልኩት የህጻኗ አባት በጦር ሜዳ ተሰውቷል። የህጻኗ ወላጅ እናት ደግሞ በባሏ ሃዘን ጠዋት ማታ እየተወዘወዘች... እህህ... እያለች ባሏን ተከተለች። አርፋለች። የሞተችው ግን የዘጠኝ ዓመቷን ህጻን እና የሁለት ዓመት ጫቅላ ህጻኗን ትታ ነው። ያማል። ከዚህ በኋላ የዘጠኝ ዓመቷ ህጻን የሁለት ዓመት ወንድሟን ለመሳደግ ወደ ልምና ወጣች። የእናቷ እህትም አለች። እየለመነች በምታገኛት ገንዘብ በተደፋባቸው የቀን ጥላ ስር ይኖራሉ።

ኢትዮጵያ ግን የማናት? ለማነች? የአገር ባለውለታ ልጆች እንዲህ ሆነዋል። ሌላው ደግሞ ጠግቦ ሲተፋ ያድራል። "አገር ለማዳን ተነሱ" ያሉት ባለስልጣናት ናጥጠዋል። በእርግጥ ይች ህጻን እድለኛ ሆና በካሜራ ዕይታ ወስጥ ገባች እንጂ በዚህ ጦርነት የስንቱ የሞቀ ቤት ፈርሷል መሰላችሁ። ስንት ህጻናት ተበትነዋል መሰለችሁ። ኢትዮጵያ ማለት እንዲህ ናት። የሸጣት የሚዘባነንባት፣ የሞተላት ደግሞ ዳግም የሚሞትባት።

ይችን ህጻን ለማገዝ የምትፈልጉ ካላችሁ አድራሻዋን ከEBS ቴሌቭዥን ልታገኙ ትችላላችሁ...
1.9K views16:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-27 17:44:58
1.8K views14:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-27 17:44:38 የልማት አርበኛው ገዳም "ማን እንደ አባአቡነ ያሳይ" አንድነት ገዳም

በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ምዕራብ ደምቢያ ወረዳ የምትገኘው ጎርጎራ የጣና ሐይቅ ወደብ ከመሆኗ ባሻገር በደሴቶቿና በዳርቻዋ በርካታ ገዳማትን አቅፋ የያዘች ናት።

ለአብነትም ደብረ ሲና ማርያም፣ ማን እንዳባ መድኃኔ ዓለም፣ ብርጊዳ ማርያም፣ ገሊላ ኢየሱስ፣ አንጋራ ተክለ ሃይማኖት፣ እጅ በራ ማርያም እና ሌሎችም ገዳማቶች ከበዋት ይገኛሉ፡፡

"ማን እንደ አባ አቡነ ያሳይ" አንድነት ገዳም በርካታ መነኮሳቶች ያሉት ሲሆን በእንስሳት እርባታ፣ በንብ ማነብ እና በግብርና ስራዎች የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል።

ኢትዮጵያ አቅፋ የያዘቻቸው፣ ጠብቃ ያኖረቻቸው አያሌ ሚስጥራት አሏት፡፡ እነዚያ ሚስጥራትም የዓለም ሚስጥር መፍቻ ቁልፎች ናቸው፡፡ ኢትዮጵያ ግን ሚስጥር ናት፡፡ ገዳሙን ይዩት፤ ይጎብኙት፣ ይረኩበታል፤ መልካም ነገርም ያገኙበታል::

በመሆኑም ዓመታዊ የንግስ በዓሉ የፊታችን መጋቢት 27/2015 በደመቀ ሁኔታ ስለሚከበር የበዓሉ ተሳታፊ በመሆን በረከትን ያግኙ፡፡

መረጃው የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ኮሙዩኒኬሽን ነው።
2.0K views14:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ