Get Mystery Box with random crypto!

የህይወት ቃል / Word of life

የቴሌግራም ቻናል አርማ dailywordoflife — የህይወት ቃል / Word of life
የቴሌግራም ቻናል አርማ dailywordoflife — የህይወት ቃል / Word of life
የሰርጥ አድራሻ: @dailywordoflife
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.80K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የቴሌግራም ቻናል በየእለቱ ህይወት ከሆነው ከእግዚአብሔር ቃል አጠር ያለ መልእክት የሚቀርብበት ነው። ይህንን ቻናል በመቀላቀልና አብረን ይህንን የህይወት ቃል እንድንመረምር እናድማችኋለን። ጥያቄ ወይም አስተያየት ቢኖራችሁ በዚህ አድራሻ ጻፉልን። @melakalex ወይም 254724416340

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-09-01 21:57:11 ቀን 5
አይኖቼን ክፈት
ከ2014 ወደ 2015 በጸሎት ለመሻገር እየተሳተፍን በምንገኝበት በዚህ መርሃ ግብር፣ የዛሬው የጸሎት ርእሳችን የሚያተኩረው በአይናችን ላይ ሲሆን “ዐይኖቼን ክፈት” በማለት ወደ ጸጋው ዙፋን እንቀርባለን።
ይህ ጸሎት እጅግ ወሳኝ እንደሆነ ለመረዳት ጌታችን ኢየሱስ ስለ ዐይን ሲናገር እንዲህ ያለውን ማስታውስ ተገቢ ነው ፦
“ዐይን የሰውነት መብራት ነው፤ ስለዚህ ዐይንህ ጤናማ ከሆነ መላው ሰውነትህ በብርሃን የተሞላ ይሆናል። ዐይንህ ታማሚ ከሆነ ግን መላው ሰውነትህ በጨለማ የተሞላ ይሆናል።” ማቴ 6:22
በተለይም ደግሞ የልቦናችን ዐይን ካልበራና የአምላካችንን መገኘትና የእርሱንም ሃሳብ ካላስተዋልን ሕይወት በጨለማ እንደመዳከር ይሆንብናል።
ይህንን የተረዳው ጳውሎስ ለኤፌሶን ሰዎች ሲጸልይ እንዲህ በማለት ነበር የጻፈው ፦
“እንዲሁም በእርሱ የተጠራችሁለት ተስፋ፣ ይህም በቅዱሳኑ ዘንድ ያለውን ክቡር የሆነውን የርስቱን ባለጠግነት ምን እንደሆነ ታውቁ ዘንድ የልባችሁ ዐይኖች እንዲበሩ ለእኛ ለምናምነውም ከሁሉ በላይ ታላቅ የሆነውን ኀይሉን እንድታውቁ እጸልያለሁ። ” ኤፌ 1:18፣ 19
“ዐይኖቼን ክፈት” በማለት ስንጸልይ ክቡር የሆነውን የርስቱን ባለጠግነት ምን እንደሆነ እንድናስተውል ሊሆን ይገባል።
በእርግጥም ዐይናችን ሲከፈት የተጠራንለትን ተስፋ እናስተውላለን። ይህ ተስፋ ደግሞ ታላቅ የሆነው የእግዚአብሔር ኀይል በእምነት በተቀበሉት ህይወት ውስጥ እንደሚሰራ ዋስትና የሚያስጨብጠን ተስፋ ነው።
ዛሬ ምልናባት የእግዚአብሔርን ቃል በዘልማድ የምናነብና ቃሉም ከእኛ ከሰሚዎቹ ጋር በእምነት ተዋህዶ እየጠቀመን ካልሆነ፣ ጌታ ዐይናችንን እንዲያበራልንና በቃሉ ውስጥ የተገለጠውን ተአምራት አድራጊውን የእርሱን ድንቅ ኀይል ለማየት እንጸልይ።
ጌታችን ኢየሱስ ከተሰቀለ በኋላ በኤማኡስ መንገድ ላይ እየጠወለጉ የሚሄዱ ደቀመዛምርት ነበሩ። “በቃ! ተስፋ ያደረገነው ከዳን! ተስፋችን ሞተ!” እያሉ ያዝኑ ነበር። ይሁን እንጂ፣ ጌታችን ሞትን ድል አድርጎ ተነስቶ ድንገት ከእነርሱ ጋር አብሮአቸው መጓዝ ጀመረ። በጉዟቸው መጨረሻም ዐይናቸው ተከፈተና ተስፋቸው መና እንዳልቀረ ይልቁንም ህያው እንደሆነ ተረዱ።
ዐይናቸው በተከፈተ ጊዜ ኀይላቸው ደግሞ ታደሰ። ህይወታቸው ተለወጠ።
አባት ሆይ፣ እኛም የልባችን ዐይኖች እንዲበሩልንና የአንተን ማንነትና ለእኛም የተሰንጠን ከሁሉ በላይ ታላቅ የሆነውን ኀይልን እንድናስተውል ዐይናችንን ክፈትልን። አሜን።
48 views18:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 21:57:04
47 views18:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 22:27:03 ቀን 4
“መልሰን፣ አድሰን”
ባለፉት ቀናት ስለ ኃጢአትችን ምህረትን ለመቀበል ወደ ጸጋው ዙፋን ቀርበልና። ዛሬ ደግሞ ያለፈ የበደል ዕዳችን እንዲሰረዝ ብቻ ሳይሆን፣ ወደ አምላካችን ወደ እግዚአብሔር ለመመለስና ከእርሱ ጋር ያለን ሕብረት እንዲታደስ ከነብዩ ኤርሚያስ ጋር እንዲህ ብለን እንጸልይ ፦
“አቤቱ መልሰን እኛም እንመለሳለን፤ ዘመናችንን እንደቀድሞ አድስ።”
አምላካችን እግዚአብሔር ከገባንበት የከንቱ ህይወት አዘቅት ውስጥ የሚያወጣን እንደዚሁም እንደገና አስቀድሞ ወዳዘጋጀልን ክብር ሊመልሰን የሚፈልግ አፍቃሪ አባት ነው።
የጠፋው ልጅ ወደ አባቱ ሲመለስ ከአባቱ ባሪያዎች አንዱ ሆኖ ለመስራት ነበር የተመኘው! አባቱ ግን ወደ ቀድሞ የልጅነት ክብሩና ስልጣኑ መለሰው። በአመጽ ከቤቱ ኮብልሎ ያጣውን ሁሉ አደሰለት።
አምላካችን ለእኛም ተመሳሳዩን ሊያደርግልን “ወደ እኔ ኑ” ይለናል። እኛም ለዚህ ጥሪው ምላሽ በመስጠት “አቤቱ፣ መልሰን፣ አድሰን” እንበለው። ህይወታችንን በትክክል ሊያድስና ሊያስተካክል የሚችለው አስቀድሞ የፈጠረን እርሱ ብቻ ነው ።
ምንም እንኳን ህይወታችን ነብዩ ህዝቅኤል እንደተመለከታቸው የደረቁና የተበታተኑ አጥንቶች እንደገና የመታደስ ተስፋ የሌለው ቢመስልም፣ ለእግዚአብሔር ግን የሚሳነው እንደሌለ እናስታውስ።
እርሱ እነዚያን ዐጥንቶች እንደገና ገጣጥሞ ስጋ አልብሶ፣ እስትንፋስ ዘርቶ፣ ታላቅ ሰራዊት አድርጎ ያቆመ ሁሉን ቻይ አምላክ ነው። ይህንን በማመን፣ ከእርሱ የራቀውን ህይወታችንን ወደ እርሱ ልመሶ፣ የተመሰቃቀለውን ህይወታችንን እንዲያድስልን “አቤቱ ወደ አንተ መልሰን፣ አድሰን።” ብለን እንጸልይ።
አባት ሆይ፣ መልሰን እኛም ወደ አንተ እንመለሳለን፤ ዘመናችንን እንደ ቀድሞ አድስልን። አሜን።
75 views19:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 22:26:51
72 views19:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 22:04:49 ቀን 3 “ይህንን ኃጢአት አትቁጠርባቸው”
ከ2014 ወደ 2015 በጸሎት ለመሻገር በምንሳተፍበት በዚህ መርሃ ግብር፣ በግልና በጋራ ስለሰራነው ኃጢአት ከእግዚአብሔር ዘንድ ምሕረትን ልንጠይቅ እንደሚገባ አይተናል። ዛሬ ደግሞ በእኛ ላይ በደል ለፈጸሙብን ከእስጢፋኖስ ጋር በመተባበር “ጌታ ሆይ፣ ይህንን ኃጢአት አትቁጠርባቸው” ብለን ከልባችን እንጸልይ።
ቂም ከምንም በላይ የሚጎዳው ያቄመውን ሰው ሲሆን ፣ይቅር ማለት ደግሞ ከሁሉም በላይ ነጻ ሚያወጣው ይቅር ባዩን ነው። ቂም ወደ ራሳችን አዙረን የያዝነው ጩቤ ነው። እንጎዳዋለን ብለን ያሰብነውን ሰው ከምንጎዳው በላይ እራሳችንን እንደምንጎዳ ቂም ይዘን የምናውቅ ሰዎች እናስተውላለን። አንድ ወዳጄ አበሳጭቶኝ በቂም የተሞላሁበትን ጊዜ አስታውሳለሁ። በመንገድ ባየሁት ቁጥር ውስጤ በንዴት ይቃጠላል። በተለይ በተለይ ባገኘሁት ቁጥር ከሌሎች ጋር ሲሳሳቅ ሲደሰት አየው ነበርና፣ ናብከደነጾር ሰባት እጥፍ እንዳነደደው እሳት የኔም የንዴት እሳት ሰባት እጥፍ ይነድ ነበር። በእርግጥም ቂም ወደ ራሴ አዙሬ የያዝኩት ጩቤ እንደሆነ ተረዳሁ። እናንተስ? እስኪ የየራሳችሁን ተሞክሮ አስታውሱ ቂም በመያዛችሁ ሰላማችሁ ፣ ደስታችሁ፣ እረፍታችሁ ጨመረ ወይስ ቀነሰ? ጠቢቡ ሰለሞን ይህንን አስመልክቶ እንዲህ ይላል፦”በደልን ንቆ መተው መከበሪያው ነው” ምሳ 19፥11።
መጽሐፍ ቅዱስ በደፈናው ይቅር በሉ አላለንም። ይልቁንም “ጌታ ይቅር እንዳላችሁ እናንተም ሌላውን ይቅር በሉ” (ቆላ 3፥13) ነው የሚለው። ይሄንን በትክክል መረዳት ይኖርብናል። ምክንያቱም ብዙዎች ይቅርታን ስናደርግ ክርስቶስን ሞዴል ከማድረግ ይልቅ ከቃሉ ጋር የማይስማሙትን አለማዊ አካሄዶች የምንከተል ስለሆንን ነው። አንዳንዶቻችን “መጥቶ እግሬ ስር ካልተንደባለለ ይቅር አልለውም!” የምንለው መፈክር አለን። ጌታ ግን ይቅር ያለን ገና ጠላቶቹ ሳለን መሆኑን አንርሳ። እኛንም ያስተማረን አንደዚያው እንድናደርግ ነው። እስጢፋስኖ የጌታችን የኢየሱስን ሞዴል ነበር የተከተለው። በሃሰት ተወንጅሎ፣ በድንጋይ ሲወገር፣ እርሱም እንደ ጌታው “ይህንን ኃጢአት አትቁጠርባቸው” ብሎ ጸለየ።
አባት ሆይ፣ ቂም ይዘን በቀልን ተጠምተን ከአመት አመት እንዳንሻገር፣ ይልቁንም አንተ ጠላቶችህ ሳለን ይቅር እንዳልከን፣ እኛም ጠላቶቻችንን ይቅር እንድንል በጸጋህ እርዳን። አሜን።
225 views19:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 22:04:45
209 views19:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 23:01:49 ቀን 2 “ኃጢአትን ሠርተናል፥ … አቤቱ፥ ይቅር በለን፤”
ከ2014 ወደ 2015 በጸሎት ለመሻገር በምንሳተፍበት በዚህ መርሃ ግብር፣ ትናንትና የግል ኃጢአታችንን ይዘን ዳዊት “አቤቱ ማረኝ” ብሎ የጸለየውን ጸሎት በመጋራት በእግዚአብሔር ፊት በንስሓ ቀርበናል።
ዛሬ ደግሞ ከዳንኤል ጋር በመተባበር ስለ ግል ብቻ ሳይሆን በማህበር ስለሰራነው ኃጢአት በንስሓ በእግዚአብሔር ፊት በመቅረብ የእርሱን ምሕረት እንለምን። ምንም እንኳን ዳንኤል የአምላኩን ፈቃድ ይከተል የነበረም ቢሆን፣ ነገር ግን የሕዝቡን ኃጢአት እንደራሱ በመቁጠር “በድለናል፣ ክፋትን አድርገናል” እያለ በንስሓ በአምላኩ ፊት ስለ ህዝቡ ዐመፅ ይቅርታን ለመነ።
እኛም ተመሳሳዩን መንፈስ በመጋራት በምድራችን ላይ ስለተፈጸመው ክፋት በደል፣ ከአምላካችን ከእግዚአብሔር የፍቅር ሕግ ዘወር ብለን በጥላቻ ስለተፈጸሙት ድርጊቶች ሁሉ “አቤቱ፣ ይቅር በለን” እያልን ይህንን ዳንኤልን ጸሎት ከልባችን እንጸልይ።
“ከሚወዱህና ትእዛዝህን ከሚፈጽሙ ሁሉ ጋር የፍቅር ቃል ኪዳንህን የምትጠብቅ፣ ታላቅና የተፈራህ አምላክ፤ ጌታ ሆይ፤ እኛ ኀጢአት ሠርተናል፤ በድለናልም፤ ክፋትን አድርገናል፤ ዐምፀናልም፤ ከትእዛዝህና ከሕግህ ዘወር ብለናል። …
እግዚአብሔር ሆይ፤ እኛና ንጉሦቻችን፣ ልዑሎቻችንና አባቶቻችን በአንተ ላይ ኀጢአት ስለ ሠራን በኀፍረት ተከናንበናል። ምንም እንኳ በእርሱ ላይ ያመፅን ብንሆን፣ ጌታ አምላካችን ይቅር ባይና መሓሪ ነው። እግዚአብሔር አምላካችንን አልታዘዝነውም፤ ደግሞም በአገልጋዮቹ በነቢያት በኩል የሰጠንን ሕግ አልጠበቅንም፤ …
“አሁንም አምላካችን ሆይ፤ የአገልጋይህን ጸሎትና ልመና ስማ። ጌታ ሆይ፤ ስለ ስምህ ስትል ፊትህን ወደ ፈረሰው መቅደስ መልስ። አምላክ ሆይ፤ ጆሮህን አዘንብለህ ስማ፤ ዐይንህን ገልጠህ መጥፋታችንንና ስምህ የተጠራበትን ከተማ ተመልከት። ልመናችንን የምናቀርበው ስለ ጽድቃችን ሳይሆን፣ ስለ ታላቅ ምሕረትህ ነው። ጌታ ሆይ፤ አድምጥ! ጌታ ሆይ፤ ይቅር በል! ጌታ ሆይ፤ ስማ! አድርግም፤ ስምህ በከተማህና በሕዝብህ ላይ ተጠርቶአልና አምላኬ ሆይ፤ ስለ ስምህ ስትል አትዘግይ።” ዳንኤል 9፡ 4-20
አዎ፣ ስለጽድቃችን ሳይሆን ስለ ታላቅ ምሕረቱ አምላካችን የእኛንና የህዝባችንን በደል ይቅር ብሎ እንዲደርስልን እንጸልይ።
አባት ሆይ፣ እኛም ዳንኤል እንደ ስለራሳችንና ስለሕዝባችን ኃጢአት በፊትህ በስሓ እንቀርባለን፤ ስለታላቅ ምሕረት ብለህ ቅር በለን። በቃችሁ በለን። አሜን።
293 views20:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 23:01:44
243 views20:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 22:11:11 በጸሎት መሻገር
ቀን 1 “ማረኝ”
በኢትዮጵያ ቀን አቆጣጠር 2014ን ሸኝተን 2015ን ለመቀበል ዛሬን ጨምሮ አስራ አራት ቀናት (ሁለት ሳምንት) ብቻ ቀርተውናል። ታዲያ አሮጌ ሊባል ትንሽ ከቀረው ከያዝነው አመት ወደ አዲሱ አመት በእግዚአብሔር የጸጋ ዙፋን ፊት ልዩ ቆይታን በማድረግ አብረን በጸሎት እንድንሻገር ለውድ አንባቢዎቼ ጥሪ ላቀርብላችሁ እወዳለሁ። በሕይወት ብንኖርና ጌታ ቢፈቅድ ከዛሬ ጀምሮ በየማለዳው በተለየ ጸሎት ወደ ጌታ በመቅረብ በአዲስ መንፈስ ወደ አዲስ አመት መግባት እንዲሆንልን ልባዊ ጸሎቴ ነው።
ታዲያ ዛሬ በዚህ የጸሎት መርሐ ግብራችን የመጀመሪያ ቀን በእግዚአብሔር ፊት የምንቀርብበት የጸሎት ርእስ የእግዚአብሔርን ምህረት ለግል ኃጢአታችን የምንጠይቅበት ሊሆን ይገባል። እስቲ መለስ ብለን ያለፉትን የአመቱን ቀናት እንዴት እንዳሳለፍናቸው እንቃኝ። ንስሓ ያልገባንባቸው ኃጢአቶች ይኖሩ ይሆን? አሁንም ድረስ የምንወድቅ የምንነሳበት፣ የምናነክስበት የኃጢአት ልምምድ ይኖረን ይሆን?
ዳዊት በፈጸመው ከባድ ወንጀል ልቡ በተሰበረ ጊዜ ያቀረበውን እንዲህ የሚለውን ልመና እኛም ከልባችን እንጸልየው፦
"እግዚአብሔር ሆይ እንደ ቸርነትህ መጠን፣ ምሕረት አድርግልኝ"፡፡ መዝሙረ ዳዊት 51:1
ይህንን ልመና በትክክል ለማቅረብ ደግሞ የሚከተሉትን ሦስት ነጥቦች ማስተዋል ያስፈልገናል።፡፡
1. ይህንን ልመና የሚያቀርብ ሰው በቅድሚያ ከእግዚአብሔር ዘንድ ምህረት እንዳለ ሊያምን ይገባል።
"የእግዚአብሔር ሁሉን አዋቂነት፣ ሁሉን ቻይነት፣ ቅድስናው ሁሉ የሚገርሙ ባህርያቱ ናቸው።፡፡ ምህረቱ ግን ከነዚህ ሁሉ በላይ አስደናቂ ነው። ሊያጠፋን ሲችል፣ ከአእምሮእችን በላይ የሆነውን መስዋእትነት ከፍሎ፣ ይሄውም በመስቀል ላይ ራሱን በመስጠት፣ ይቅር ሊለን መረጠ። እንግዲህ "ምህረት አድርግልኝ" ስንል በእርሱ ዘንድ ይህ ምህረት እንዳለ በማስተዋል እንቅረብ።
2. ይህንን ልመና የሚያቀርብ ሰው ምህረት እንደሚያስፈልገው የሚያምን መሆን አለበት።
ምህረት 'ይገባናል' ብለን የምናገኘው ጉዳይ አይደለም።፡፡ ለኃጢአተኛው የሚገባው ሞት ሲሆን፣ ይህንን ደሞዙን ለኃጢአተኛው መክፈል ደግሞ ለእግዚአብሔር የቅድስናውን ክብርን አያጎድልበትም።፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ቀድሞ በተሠራ ጽድቅ ምህረት ይገባኛል ብሎ መጠየቅ አይቻልም።፡፡ እናም በሃጢአት ለወደቀው ሰው ብቸኛው ማምለጫ የእግዚአብሔር ምህረት ነው።፡፡
3. ይህንን ልመና የሚያቀርብ ሰው ምህረትን ለመቀበል የሚናፍቅ ልብ ሊኖረው ይገባል።፡፡
ለአንድ ሰው በእግዚአብሔር ዘንድ ምህረት መኖሩንና፣ ያም ምህረት ለእርሱ እንደሚያስፈልገው ማወቅ ብቻውን በቂ አይደለም።፡፡ ይልቁንም ይህንን ምህረት በግል ለመቀበል መጓጓትና ‹‹እኔን ማረኝ›› ማለት ያስፈልጋል።፡፡ እግዚአብሔር መሐሪ መሆኑን ማወቅ ብቻውን ሩቅ አያስኬድም፤ ምህረቱን በግሉ ያልተካፈለ ሰው የበረከቱ ተካፋይ ሊሆን አይችልም።
አባት ሆይ፣ አንተ መሐሪ መሆንህን በማስተዋል፣ እኔ ደግሞ ምሕረትህ የሚያስፈልገኝ ኃጢአተኛ መሆኔን በመረዳት፣ "እንደ ቸርነትህ መጠን ምሕረት አድርግልኝ" ብዬ ከልቤ እንድጸልይ እርዳኝ። አሜን።
354 views19:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 22:10:32
259 views19:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ