2023-02-11 15:59:19
ወደ ዓለማዊው ትግሉ ስንመልሰው...
የአገራችን ፖለቲከኞች ከብጹዓን አባቶቻችን የሚማሩት ቁምነገሮች አሉ ብዬ አምናለሁ። በእርግጥ በአባቶቻችን ቁመና ልክ መገኘት ከባድ ነው።
ፖለቲከኞቻችን የተወሰነም ቢሆን እስቲ ከብጹዓን አባቶቻችን ጽናትን፣ ተስፋ አለመቁረጥን፣ ቁርጠኝነትን፣ ሃቀኝነትን፣ ለወጠኑት ዓላማ እስከ ቀራንዮ ድረስ መታመንን፣ እራስን ለወጠኑት ዓላማ አሳልፎ መስጠትን፣ ብስለትን፣ ምክንያታዊነትን፣ ገቢራዊነትን፣ የመርህ ባለቤትነትን፣ የዓለማ ጥራትን፣ ለመዳረሻ ግብ ተከታይን ወይም አባልን አንድ አድርጎ መምራትን፣ የዲፕሎማሲ ወይም የውይይት ጥበብን፣ የመግለጫ አሰጣጥ ብልሃትን፣ እርስ በእርስ መከባበርን፣ ግብረ ገብነትን፣ ሚስጥር ጠባቂነትን፣ ቁጥብነትን... ወዘተ
ማስታወሻ:- ከላይ የዘረዘርኳቸውን እሴቶች ባለቤት የሆኑ በሰላማዊ መንገድ ለመታገል የቆረጡ የፖለቲካ ድርጅቶች ከመጡ? ቀልቤን በገዘው ድርጅ አባል ሁኜ ለመታገል፣ የድርጅቱን፣ ራዕይ፣ ዓላማ፣ ግብ እና የድርጅቱን መሪዎች አክብሬ እንዲሁም የሚሉትን አዳምጬ በቁርጠኝነት ለመተግበር ዝግጁ መሆኔን በዚሁ አጋጣሚ አሳውቃለሁ።
1.5K views12:59