Get Mystery Box with random crypto!

ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ Philosophy

የቴሌግራም ቻናል አርማ zephilosophy — ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ Philosophy
የሰርጥ አድራሻ: @zephilosophy
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.37K
የሰርጥ መግለጫ

ፍልስፍና  እውነትን በመፈለግ- ሀሳዊ እምነቶችን በማጋለጥ እና ጭፍን አመለካከቶችን በጥበብ በመመርመር ወደ ላቀ አሰተሳሰብ ያሻግራል።
በዚህ ቻናል አለም ላይ ያሉ ፍልስፍናዎች ፤ ርዕዮት አለሞች ፤  ሀይሞኖቶች እና አስተሳሰቦች በነፃነት ይዳሰሳሉ።

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2024-04-15 23:07:49 "ፍቅር ግንኙነት ሳይሆን የመሆን
ሁኔታ ነው"

ምንጭ ፦ ህያውነት (ኦሾ)
ተርጓሚ ፦ ሀብታሙ ተስፋዬ

ፍቅር ግንኙነት ሳይሆን የመሆን ሁኔታ ነው፤ ከማነም ጋር ግንኙነት የለውም፡፡ አንድ ሰው ፍቅር ውስጥ ነው ወይም አፍቅሯል ሳይሆን የሚባለው <እገሌ ፍቅር ነው> ነው የሚባለው፡፡ በእርግጥ አንድ ሰው ፍቅር ሲሆን በፍቅር ውሰጥ ነው ያለው ነገር ግን ይህ ምርጫ ሳይሆን ውጤት ነው፡፡ ምንጩ ፍቅር መሆኑ ነው፡፡

ማን ፍቅር ሊሆን ይችላልን? ማን እንደሆናችሁ የማታውቁ ከሆነማ ፍቅር ልትሆኑ አትችሉም፡፡ ይልቁኑ ፍርሃት ትሆናላችሁ፡፡ ፍርሃት የፍቅር ተቃራኒ ነው፡፡ ሰዎች እንደሚያስቡት የፍቅር ተቃራኒ ጥላቻ አይደለም፡፡ ጥላቻ የፍቅር ተቃራኒ ሳይሆን ፍቅር ተገልብጦ ሲቆም ነው፡፡ እውነተኛ የፍቅር ተቃራኒ ፍርሃት ነው፡፡ ፍቅር ያሰፋል፣ ፍርሃት ያጠብባል፡፡ ፍርሃት ይዘጋል፣ ፍቅር ይከፍታል፡፡ ፍርሃት ያጠራጥራል፣ ፍቅር ያሳምናል፡፡ ፍርሃት ብቸኛ ያደርጋል፡፡ ብቸኛ ከማድረግም አልፎ ያጠፋል፡፡ የሌለ ሰው እንዴት ብቸኛ ይሆናል? እነዚህ ዛፎች፣ አዕዋፋት፣ ደመናዎች፣ ፀሃይ፣ ከዋክብት በሙሉ እናንተ ውሰጥ ናቸው፡፡ ፍቅር ማለት ውስጣዊ ቁልፋችሁን ስታውቁ ነው::

ማንም ህፃን ከፍርሃት ነፃ ነው፤ ህፃናት የሚወለዱት ያለምንም ፍርሃት ነው፡፡ ማህበረሰቡ ፍርሃት አልባ እንዲሆኑ ቢረዳቸውና ቢደግፋቸው ዛፎችና ተራሮች ላይ እንዲንጠለጠሉ፣ ውቅያኖሶችንና ወንዞችን እንዲያቋርጡ በረዳቸው ነበር፡፡ ማህበረሰቡ ጀብደኛ እንዲሆኑ፣ ካረጀ እምነት ይልቅ የማይታወቀውን እንዲመረምሩ ቢያደርጋቸው ኖሮ፤ ታላላቅ የህይወት አፍቃሪዎች ባደረጋቸው ነበር፡፡ ይህ ነው እውነተኛ ሃይማኖት፡፡ ከፍቅር በላይ ሃይማኖት የለም፡፡

ተመሰጡ፣ ደንሱ፣ ዝፈኑ፣ ወደ ውስጣችሁ ጠልቀችሁ ግቡ፡፡ የአዕዋፋቱን ዝማሬ በአንክሮ አድምጡ፡፡ አበቦቹን በአድናቆት ተመልከቱ፡፡ አዋቂ አትሁኑ፤ ነገሮችን አትፈርጁ አዋቂ መሆን ማለት ይህ ነው ለእያንዳንዱ ነገር መደብ፣ ፈርጅ ማውጣት፡፡ ከሰዎች ጋር ተገናኙ፣ ከሰዎች ጋር ተቀላቀሉ፣ በተቻላችሁ መጠን ከብዙ ሰዎች ጋር ተገናኙ፡፡ እያንዳንዱ ሰው በተለያየ ሁኔታ የእግዚአብሄርን መልክ ያሳያል፡፡ ከሰዎች ተማሩ፡፡ አትፍሩ፡፡

ፍቅር እምብዛም የማይገኝ አበባ ነው፡፡ ብቅ የሚለው አንዳንድ ጊዜ ነው፡፡ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች አፈቀርን ብለው የውሸት ኑሮ ይኖራሉ፡፡ እንደሚያፈቅሩ ያምናሉ፡፡ ከእምነት የዘለለ ግን አይደለም፡፡

ፍቅር ብርቅዬ አበባ ነው:: ብቅ የሚለው አልፎ አልፎ ነው፡፡ የሚከሰተው ፍርሃት ሳይኖር ሲቀር ነው፡፡ ይህም ማለት ፍቅር የሚከሰተው በጣም መንፈሳዊ ሃይማኖተኛ ለሆነ ሰው ነው፡፡ ሁሉም ወሲብን፣ መላመድን ሊያገኙ ይችላሉ፡፡ ፍቅርን ግን ሁሉም አያገኙትም፡፡

ፍቅር ድፍረት ይሰጣል፤ ፍቅር ፍርሃትን ያጠፋል ጨቋኞች የእናንተ ፍርሃት ጥገኛ ናቸው፡፡ አንድ ሺ አንድ ፍርሃት ይፈጥሩባችኋል፡፡ ስለዚህ በፍርሃት ትከበባላችሁ፤ ሥነ - ልቡናችሁ በፍርሃት ይሞላል፤ በውስጣችሁ ትሸበራላችሁ:: ፊታችሁ አንድ አይነት ገፅታ ብቻ ነው ያለው፣ ውስጣችሁ ግን በፍርሃት ድርብርብ የተሞላ ነው::

በፍርሃት የተሞላ ሰው ምርጫው ጥላቻ ብቻ ነው - ጥላቻ ተፈጥሯዊ የፍርሃት ውጤት ነው፡፡ በፍርሃት የተሞላ ሰው በብስጭት የተሞላ፣ ከህይወት የወጣ ነው፡፡ በፍርሃት የተሞላ ሰው ማረፊያው ሞት ይመስላል፡፡ ፈሪ ሰው ከህይወት በተፃራሪ ራሱን የሚያጠፋ ነው፡፡ ህይወት አደገኛ ትሆንበታለች፡፡ ለመኖር ማፍቀር ያስፈልጋል፡፡ ስጋ ለመኖር መተንፈስ እንደሚያስፈልገው፣ ለነፍስም ፍቅር ያስፈልጋታል፡፡ ፍቅር ደግሞ ክፉኛ ተበክሏል፡፡

የፍቅር ሃይላችሁን በክላችሁ በውስጣችሁ መከፋፈል ፈጥራችኋል፤ ውስጣችሁን ለሁለት ከፍላችሁታል፡፡ የርስ በርስ ግጭት ፈጥራችሁበታል፡፡ ሁልጊዜም በግጭት ላይ ናችሁ:: በዚህ ግጭት ሃይላችሁ ተሟጥጧል፡፡ ስለዚህም ህይወታችሁ ደስታ የራቀው ሆኗል፡፡ በሃይል የተሞላ ሳይሆን የደነዘዘ ጣዕም የሌለው፣ ብልህነት የሌለው ህይወት ሆኗል፡፡

ፍቅር ብልህነትን ይስለዋል፤ ፍርሃት ደገሞ ያዶለዱመዋል፡፡ ብልህ መሆን ማን ይፈልጋል? ስልጣን ላይ ያሉ ይህን አይፈልጉም፡፡ እናንተ ብልህ እንድትሆኑስ እንዴት ሊፈልጉ ይችላሉ? ብልህ ከሆናችሁ እቅዳቸውን ጨዋታቸውን ትነቁባቸዋላችሁ፡፡ ስለዚህ መሃይም እና የማይረባ እንድትሆኑ ይፈልጋል፡፡ ስራን በተመለከተ ውጤታማ እንድትሆኑ ይፈልጋሉ፤ ብልህ እንድትሆኑ ግን አይፈልጉም፡፡ በዝቅተኛ አቅማችሁ እንድትኖሩ ነው የሚፈልጉት፡፡

የሳይንስ ተማራማሪዎች እንደሚናገሩት የሰው ልጅ በመላ የህይወት ዘመኑ የአቅሙን አምስት በመቶ ብቻ ነው የሚጠቀመው፡፡ ተራው ሰው አምስት በመቶውን ከተጠቀመ ልዩ የሆነ ሰውስ? አልበርት አንስታይን፣ ሞዛርት፣ ቤትሆቨን? ተመራማሪዎቹ እንደሚሉት በጣም ከፍተኛ ተሰጥኦ ያላቸው እንኳን ከአስር በመቶ በላይ አይጠቀሙም፡፡ እና የላቀ ችሎታ አላቸው የምንላቸው እንኳን አስራ አምስት በመቶውን ብቻ ነው የሚጠቀሙት፡፡

ሁሉም ሰው የአቅሙን መቶ በመቶ የሚጠቀም ቢሆን ይህች ዓለም ምን እንደምትመስል አስቡ.... ጣዖታት በምድር ቀንተው ምነው ምድር ላይ በተወለድን ይሉ ነበር፡፡ ምድር ገነት ትሆን ነበር፡፡ አሁን ግን ሱዖል ናት፡፡

የሰው ልጅ ብቻውን ቢተው፣ ሳይበከል ቢቀር .... ፍቅር ቀላል ይሆን ነበር፤ ምንም ችግር አይኖርም፡፡ ቁልቁል እንደሚወርድ ውሃ ወይም ሽቅብ እንደሚወጣ ትነት፣ እንደሚያብቡ ዛፎች፣ እንደ ዘማሪ አዕዋፋት ይሆን ነበር፡፡ ተፈጥሯዊና ህያው ይሆናል!

ነገር ግን የሰው ልጅ ብቻውን አልተተወም፡፡ አንድ ህፃን ሲወለድ ጨቋኞች ዘልለው ሃይሉን ያደቁታል፤ ሃይሉን ያዛቡታል፤ መኖር ያለበትን ያህል ሳይሆን የውሸት ህይወት እየኖረ እንደሆነ እንዳያውቅ፣ እየኖረ ያለው በእውነተኛ ነፍሱ እንደሆነ እንዳይገነዘብ ያደርጉታል፡፡ ለዛም ነው በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች በዚህ ስቃይ ውስጥ የገቡት - እነዚህ ሰዎች እንደተሰናከሉ ራሳቸውን እንዳልሆኑ፣ አንድ የተሳሳተ ነገር እንዳለ.... ይሰማቸዋል ።

@Zephilosophy
@Zephilosophy
10.7K views20:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-03 23:13:19 አብዘርዲዝም - ካምዩ

ምንጭ ፦ ፍልስፍና ከዘርዓያዕቆብ እስከ ሶቅራጠስ
ምንጭ ፦ ፍሉይ አለም

መጠለያ ባጣህበት ሁኔታ በዝናብ እየተደበደብክ እየተጓዝክ ሳለ፣ መሳቅ ጀምረህ አታውቅም? የሆነ ጉዳይ በእጅጉ ተበላሽቶብህ ከዚህ በላይ ምን ሊመጣ አይነት ስሜት ፈገግ ብለህ አታውቅም? በችግሮችህ ውስጥ ሳለህ እያንዳንዷን ደቂቃ ወደህ አታውቅም? ይህን አልበርት ካምዩ አብሰርዲቲ ይለዋል፡፡

ካምዩ ፈረንሳያዊ የኤግዚስታንሻሊዝም (ህላዌነት) ፈላስፋ ነው፡፡ በቀላል ታሪክም ፍልስፍናውን ይጀምራል፡፡

ሲሲፈስ የተባለ የጥንታዊቷ ግሪክ ንጉስ አማልክቱን የሚያስቆጣ ተግባር ፈጸመ። ሲሲፈስ ሞትን በሰንሰለት አሰረው፡፡ ይህንንም በማድረጉ የሰው ልጅ ዘላለም ኗሪ ሆነ። በመጨረሻም አማልክቱ ሲሲፈስ ያደረገውን አወቁ፤ በርሱ ላይም ዘላለማዊ ቅጣት ፈረዱበት፤ የሞትንም ሰንሰለት በጠሱ፡፡ እናም ሲሲፈስ ለመቀጣጫ እንዲሆነው ዘላለም ድንጋይ ሲያንከባልል እንዲኖር ተፈረደበት። ግዙፍ ቋጥኝ እየገፋ ወደ ተራራ አናት ያደርስዋል፤ ወዲያውም ቋጥኙ ወደ ተራራው ስር ተንከባሎ ይወርዳል፤ ሲሲፈስም እንደገና ከታች ጀምሮ ወደ ላይ ቋጥኙን ይገፋዋል፡፡ ቋጥኙም ተመልሶ ወደ ተራራው ግርጌ ይወርዳል...

ይህ የሲሲፈስ ዘላለማዊ ቅጣቱ ነው። ያንተስ ሕይወት ከርሱ ይለያልን? የሲሲፈስ እልፍ ጊዜ እየተመላለሰ ቋጥኝ ማንከባለሉ ትርጉም አልባ እንደሆነ ይሰማሃል? ሆኖም ያንተ ሕይወት ትርጓሜው ምንድን ነው?

ሕይወትህን ልክ እንደ ሲሲፈስ ትርጉም አልባ ቋጥኞችን ስትገፋ ነው የምታሳልፈው፡፡ የማይሞላ ሆድ አለህ... ሚልዮን ጊዜ መግበኸው ሚልዮን ጊዜ ጎድሎብሃል፤ የማይሞላ ፍላጎት አለ... ሚልዮን ጊዜ ተደስተህ ሚልዮን ጊዜም ተከፍተሃል። በጠዋት ከእንቅልፍህ ትነሳለህ፤ ገንዘብን ፍለጋም ወደ ስራ ትሄዳለህ... ቀኑ ይመሻል ዳግም ይነጋል... በጥዋት ወደ ስራ ትሄዳለህ. ከእለታት በአንዱ ቀንም ራስህን በሞት አልጋ ላይ ታገኘዋለህ፡፡ እናም በሕይወት ዘመንህ የምታደርገው ነገር ሁሉ ልክ እንደ ሲሲፈስ ቋጥኝ መግፋት- ዘበት ነው!

የሰው ልጅ ህልቆ መሳፍርት በሌለው ሁለንተና ላይ ራሱን ሲያገኘው፤ “ለምን?” የሚል ጥያቄን ይጠይቃል። ለምን ተፈጠርኩ? ለምን እኖራለሁ? የሕይወቴ ትርጉምስ ምንድን ነው? ሆኖም እውነታው ይህ ነው... ያንተም የኔም የመኖር ሁኔታ በአጋጣሚዎች የተፈጠረ እንጂ ትርጓሜ ያለው ነገር አይደለም በጸጥታ ውስጥ ባለው በግዙፉ ሁለንተና ውስጥ አንተ ማን ነህና ሕይወትህ ትርጉም ይኖረዋል? ሁለንተናም ስላንተ ግድ የለውም... ለጥያቄህም መልስ የለውም፡፡ ሆኖም ይህ መሆኑን ብናውቅም፤ ሰው ነንና የሕይወታችንን ትርጉም መፈለጋችንን አናቆምም የሞትን ቀን ያበቃለታል። ሞት በሕይወታችን የኖርንላቸውን ተግባራቶች በሙሉ ዋጋ ያሳጣቸዋል፡፡ ይህንን ነው አብሰርዲዝም ወይም የሕይወት ዘበትነት ሲል የሚጠራው፡፡

እና ዘበት በሆነ ዓለም ላይ እንዴት እንኑር?

ታይታኒክ በተባለው ፊልም መጨረሻ ላይ መርከቧ እየሰመጠች ሳለ ሙዚቀኞች ቫዮሊን ሲጫወቱ ይታያል፡፡ እንደሚሞቱ ቢያውቁም፣ ቅጽበታቸውን ብቻ መኖር ጀመሩ፤ የሚወዱትንም ሙዚቃ ከልባቸው ተጫወቱ፡፡

ካምዩ በአንደኛው መጽሐፉ ላይ እንዲህ ይለናል - "የምር የሆነ አንድ የፍልስፍና ጥያቄ ብቻ ነው ያለው፤ ጥያቄውም - ራሴን ላጥፋ ወይስ ቡና ልጠጣ?”

እንደ ካምዩ እሳቤ የሰው ልጅ የሚኖርበት ምክንያት ከሌለው ሶስት ነገሮች ያደርጋል፡

የመጀመሪያው ራሱን ያጠፋል፡፡ ማለቂያ አልባ በሆነው ሁለንተና ውስጥ የምትበራ አንድ ሻማ የርሷ ጭል... ጭል ማለት ትርጉም የለውምና ራሷን እፍ ብላ ታጠፋለች፡፡ ይህን ካምዩ የዓለምን ዘበትነት ማምለጫ ይለዋል።

ሁለተኛው philosophical suicide ይፈጽማል፡፡ ይህም ማለት ሕይወት ትርጉም ባይኖራትም ትርጉም እንዳላት አድርጎ ማሰብ ይጀምራል። ለዚህ ዋነኛ ተጠቃሽ የሚሆኑት ጭፍን አማኞች ናቸው፡፡ በእምነት ውስጥ መመርመር የለም... የምትኖርበት አላማ እንዳለህ እና የምታምንበት ሀይል ለዚህ አላማ እንደፈጠረህ ያለምንም መጠራጠር በጭፍን ትቀበላለህ፡፡ ስለሆነም መኖርህ ዋጋ አልባ ወይም ዘበት እንደሆነ አይሰማህም፡፡

በሶስተኛነት የምናገኘው ካምዩ absurd hero ይለዋል። ይህ ሰው ሕይወቱ ትርጉም እንደሌላት ያውቃል፤ ለሌሎች ሰዎች ትርጉም የማይሰጥ ነገር ግን ለእርሱ ብቻ ዋጋ ያለው ... ለእርሱ ብቻ የሚሰራ የሕይወት ትርጉምንም ይፈጥራል። ይህ የትርጉም ፈጠራ ሂደትም በራሱ ደስተኛ ያደርገዋል። ለሲሲፈስም ድንጋዩን ወደ ተራራ ማንከባለሉ ለእርሱ ትርጓሜ አለው፡፡ ይህ ለስው ልጆች የከፈለው መስዋእትነት ምልክት ነው. ይህ አማልክቱ ለእርሱ የሰጡት ቅጣት ምንም እንዳልሆነ ማሳያ መንገዱ ነው... ፈገግ ብሎም ድንጋዩን ይገፋል... የእርሱ ፈገግታም አማልክቱን እንደሚያስቆጣቸው ያስባል። እናም ድንጋይ ማንከባለሉ ብቻ ልቡን በደስታ ይሞላዋል።

ካምዩም ሕይወት ትርጉም አልባ እንደሆነች ቢያውቅም እንኳ እንደ ሲሲፈስ ሁን ይልሃል። በዝናብ ውስጥ ደንስ... ትርጉም አልባ በሆነች ዓለም ላይ ለራስህ ብቻ እውነት የሆነ የመኖር ትርጉም ፍጠር፡፡

@Zephilosophy
@Zephilosophy
15.1K views20:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-03 22:43:38 ክቡር ሰው - ካንት

ምንጭ ፦ ፍልስፍና ከዘርዓያዕቆብ እስከ ሶቅራጠስ
ፀሀፊ ፦ ፍሉይ አለም

ከጓደኞችህ ጋር እራት እየበላህ፣ አንዱ ተስተናጋጅ ከመጠን በላይ እያጨበጨበ አስተናባሪውን ይጣራል “እዚህ ጋር አንድ ምግብ፡፡” አንዳንድ ሰውም በሰላም ላደረሰው ሾፌር “እንዴት ነህ፣ ቻው ወይም አመሰግናለሁ” ሳይል ከታክሲ ወርዶ ወደ ጉዳዩ ያቀናል፡፡ ወንጀለኞች ህጻናትን ሰርቀው እንደ እቃ ይሸጣሉ፡፡ መንግስትም አገሩን ከዳ ብሎ ያስበውን ግለሰብ ያስገድላል፡፡ እነዚህ ሁሉ ድርጊቶች በጋራ የያዙት ነገር ምን አለ?

ኢማኑኤል ካንት አስተናጋጁን የሚያመናጭቀው ጓደኛህም፣ ለሾፌሩ ግድ የሌለው ተሳፋሪም፣ ልጆች የሚጠልፉ ወንጀለኞችም፣ አስገዳዩ መንግስትም... ሁሉም የሰውን ልጅ አግባብ ባልሆነ ሁኔታ አስተናግደዋል ይለናል።

ካንት በምክንያታዊነት ላይ ባለው የጸና አቋም በእጅጉ ይታወቃል። ለእርሱ ምክንያታዊነት ከሁሉ የላቀ ንብረታችን እንደሆነ ነው የሚነግረን። ከዚህም በላይ ምክንያታዊነት ምን ልክ ምን ስህተት ምን ኃጢአት ምን ጽድቅ እንደሆነ ይለይልናል፡፡

ካንት የሞራል ህግጋት አይለወጤ እና የጸኑ ናቸው ብሎ ያስባል። የሚደረስባቸውም በምክንያት እና ምክንያታዊነት ብቻ ነው። ይህንንም ምክንያታዊ ግብረገብነትንም ለማስረዳት ካንት ባለ ብዙ ገፅ መጽሐፎችን አሳትሟል።

ካንት ሁሉም ሰው ሊነካ የማይገባው
ክብር አለው ይለናል። እናም የሁላችንም ድርጊቶች ይህን ክብር የጠበቁ ሊሆኑ ይገባል። በሁሉም ሁኔታዎች ውስጥ ብንሆንም የሰውን ክብር መንካት የለብንም፡፡ ሰዎች የምንገለገልባቸው ቁሳዊ መሳሪያዎች አይደሉም፡፡ ሁሉም የራሳቸው ዋጋ አላቸው። ለሁሉም ሰው ግድ ሊኖረን ይገባል።

ሁላችንም እንደ ግለሰብ ዋጋ እንዳለን እናስባለን፡፡ ዓለም የግለሰቦች ጥርቅም ናትና ለራሳችን የምንሰጠውን ዋጋ ለሁሉም ሰው መስጠት የተገባ ነው፡፡ እኛ ምንም አይነት ጥያቄ እና ምክንያት ሳንደረድር፣ ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ለራሳችን ከፍ ያለ ዋጋን ከሰጠን፣ እንደ ማህበርም ለሌሎች ሰዎች ዋጋ ሊኖረን ይገባል።

አዎ በማህበረሰብ ውስጥ አንደኛው ተገልጋይ፣ ሌላኛው አገልጋይ ሊሆን የተገባ ነው፤ ሆኖም በዚህ ሂደት ውስጥ ሰዎችን እንደ ሰውነታቸው ልናከብራቸው የተገባ ነው፡፡ አስተናጋጁም፣ የታክሲ ሹፌሩም ሆነ ሀገር ከዳተኛው ሰው ናቸው። ሁሉም ለራሳቸው ዋጋን ይሰጣሉ፡፡ ካንት ከእርሱ በኑሮ ደረጃ ዝቅ ያሉትን አገልጋዮቹን በታላቅ ክብር ይመለከታቸው ነበር፡፡

በቀጣይም ሰውን እንዴት ማዋራት እንዳለብህ ስታስብ ይህን “እንደ ሰው እያከበርኳቸው ነው ወይንስ እንደ መሳሪያ እየተጠቀምኩባቸው?” ይህም ቀላል እና ሊተገበር የሚገባው ግብረገባዊ ህግ ነው፡፡

@Zephilosophy
@Zephilosophy
23.8K views19:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-17 20:44:51 ማራኪ የዜን ትረካዎች
በግሩም ተበጀ

@Zephilosophy
@Zephilosophy
12.8K viewsedited  17:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-08 22:24:28 መሳጭ የኦሾ ትረካዎች
በግሩም ተበጀ

@Zephilosophy
@Zephilosophy
16.0K viewsedited  19:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-02 09:59:28 አድዋ፦ ሶስተኛው ፍልስፍናዊ  አብዮት !!!!!
**

<<
አድዋ ሶስተኛውን ፍልስፍናዊ አብዮት ትወክላለች፡፡ በጥቂቱ ርእሰነገሩን ለማስረዳት ያህል፣ በአለም ላይ ሶስት ፍልስፍናዊ አብዮቶች አሉ፡፡ ስለመልካም ግብ ግህደት (እውንነት) የነበረውን ሁሉ እንዳልነበረ ያደረጉ፣ በእግሩ የቆመውን በሙሉ በጭንቅላቱ የተከሉ፣ የውስጡን ወደውጪ የገለበጡ፣ተደብቆ የነበረውን ሁለንተና ሀቅ ነጻ ያወጡ እሳቤያዊ አብዮቶች ናቸው፡፡
‹‹የመጀመሪያው አብዮት ኮፐርኒከን ሬቮሉሽን፣ ሁለተኛው አብዮት ካንሺየን ሬቮሉሽን እና ሶስተኛው አብዮት ምኒሊከን ሬቮሉሽን በመባል ይታወቃሉ፡፡

"ኮፐርኒከስ በቶለሚ ተነጽሮ የነበረውንና ምድርን ማእከሉ (ጂኦሴንትሪክ ቪው) ያደረገውን ፍልስፍና ዘ ሳይንስ ወስነፈለክ ከውስጥ ወደውጪ በመገልበጥ ጸሀያዊው ስርአት (ሶላር ሲስተም) በምድር ዙሪያ የሚሽከረከር ሳይሆን ምድር ራሷ ናት በጸሀይ ዙሪያ የምትሽከረከረው፤ በማለት አዲስና ፋና ወጊ የሂልዮሴንትሪክ (ጸሀይን ያማከለ) አብዮትን በስነ ፈለክ አወጀ፡፡

‹‹ካንት በበኩሉ በስነእወቀት የፍልስፍና መስክ አዲስ አብዮትን ነፍስ ዘራበት፡፡ ነገሩ፣ ቀለል ባለ አገላለጽ እንዲህ ነው፡፡ በህሊናችን ውስጥ ያለውን ይዘት ልምድ አይወስነውም፡፡ ይልቅዬ ልምድን እራሱን የሚወስነው ህሊናችን ነው፡፡ እናም የምንዳስሰው አለም በራሱ ሆኖ የሚገኝ ሳይሆን የአእምሮአችን የተለያዩ ፈርጆች በወቀሩት፣ በሰሩት፣ ባበጃጁት፣ ፈር ባስያዙት፣ ልክ ባገቡት እና በጫኑበት ቅርጽና በለገሱት ስርአት መሰረት የሆነ ነው፡፡ እናም እውነታ ለእኛ ህሊናችን አቡክቶ በጋገረው መሰረት የሚታየው፣ የሚለበበው እና የሚቀርበው ሲሆን፣ እውነታ በራሱ ግን ምን እንደሆነ አይታወቅም፤ በማለት አዲስ የእሳቦት ፈር በስነ እውቀት ቀደደ፡፡

‹‹ሶስተኛው አብዮት በፖለቲካዊ ፍለስፍና ዘርፍ በምኒሊክ መሪነት አድዋ ላይ እውን የሆነው አብዮት ነው፡፡ እስከአድዋ ድል ድረስ ከኢትዮጵያ በስተቀር አለም በሙሉ በነጮች ገዢነት፣ በነጮች ፍጹም የበላይነት፣ በነጮች ወሮ ድልአድራጊነት፣ በነጮች ሉላዊ መሪነት፣ በነጮች ብቸኛ ተሰሚነት፣ ፍጹማዊ ፈላጭ ቆራጭነት ስር ስትፍገመገም ኖረች፡፡ ከአድዋ ድል በሁዋላ ግን ይህ ታሪክ በጭንቅላቱ ተተከለ፣ ከፍጹምነት አምድ ወደአንጻራዊነት ወታቦ ተሸኳለለ፤ ከአለማቀፋዊ ገዢ እውነታነት ወደወራዳ ፖለቲካዊ ድስትፊያነት ተንደባለለ፡፡

" ይህ የነጮችን የበላይነት በፍትህ የበላይነት፣ የዘርና የቀለም ልዩነትን መራሄነት በሰው ልጆች ሁሉ ልእልና ገዢ አስተምህሮነት፣ የጥቁሮችን መናቅና ውርደት በሰው ልጆች ሁሉ እኩልነት የተካ ሁለንተናዊ ፖለቲካዊ አብዮት ምንሊክ ሬቮሉሽን ወይም ሶስተኛው ፍልስፍናዊ አብዮት ተብሎ ይጠራል፡፡ "


ሰው ናሰው፣ ምእራፍ 1
ምንዳርአለው ዘውዴ

@Zephilosophy
@Zephilosophy
18.8K viewsedited  06:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-27 17:08:08 "በእርሻ ማሳዎቻችሁ ላይ የሚፈራረቁትን ወቅቶች ሁልጊዜ በፀጋ እንደምትቀበሉዋቸው ሁሉ የልቦቻችሁን የሀዘን ወቅቶችም  በፀጋ መቀበል ይኖርባችኋል።"
ካህሊል ጂብራን

"ሰዎች ፍቅር እውር ነው ይላሉ። እንዲህም የሚሉት የፍቅርን ትርጓሜ ስላላወቁ ነው። እኔ ግን እላችኋለሁ ፍቅር ብቻ ነው አይን ያለው። ከፍቅር ውጪ ሌላው በሙሉ እውር ነው። "
ኦሾ

"የእኛ ህይወት ግማሹን የምንወዳቸውን ሰዎች ለማግኘት እየጠበቅን፤ ግማሹ ደግሞ የምንወዳቸውን ስንሰናበት እናሳልፋለን።”
ቪክቶር-ሁጎ

"ሰዎች ብርቱዎችን ይጠላሉ ግን ይታዘዛላቸዋል ፤ ደካሞችንም ይወዳሉ ግን ይንቋቸዋልም! "
ዶስቶቭስኪ

"በብርሃን ስትሆን ሁሉ ነገር ይከተልሃል:: ጨለማ ውስጥ ከሆንክ ግን ጥላህ እንኳን አይከተልህም።"
  ሂትለር

‹‹ ቁንጅና ያለው ፊት ላይ አይደለም፡፡ ቁንጅና በውስጣችን የሚገኝ የልብ ብርሃን ነው፡፡ ››
ካህሊል ጂብራን

"የውሸት ጓደኛና ጥላ ሁለቱም አንድ ናቸዉ። ሁለቱም የሚቆዩት ፀሐይ እስካለች ድረስ ነው።"
-ዊሊያም ሼክስፒር

"አዋቂ ሆኖ ለመታየት የምናደርገው ጥረትና ከንቱ ድካም አላዋቂ አድርጎ ያስቀረናል"
         ሶቅራጥስ

"ሌሎችን የሚያሸብር ሁሉ እርሱ ራሱ በማያቋርጥ ፍርሃት የተዋጠ ነው።"
ክላውሲያ

"የሰው ልጅ የሚሰቃየው ራሱ ባጠረው አጥር ራሱ በገነባው ቅጥር ራሱ በሸበበው ውትርትር ነው። የዘር፣ የሃይማኖት፣ የርዕዮተ አለም ፣... የፍልስፍና አጥር። የብቸኝነት፣ የአውሬነት፣ የወፈፌነት ፣ ... አስማት የሚመስል አጥር።" ...
 ይስማዐከ ወርቁ

"ቤትህን ፅዱ አድርግ ልክ እንግዳ ትጠብቅ
ይመስል፣ ልብህን ፅዱ አድርግ ልክ ሞትህን ትጠብቅ ይመሰል"
አረቦች

“ሰው የሚማረው አንድም በፊደል፣ አንድም በመከራ ነው፣ አንድም በሳር “ሀ” ብሎ፣ አንድም በኣሳር “ዋ” ብሎ።”
ፀጋዬ ገ/መድህን

@zephilosophy
@zephilosophy
16.4K viewsedited  14:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-28 08:51:42 ከፍቅር ወደ አፍቃሪነት.......2

ምንጭ ፦ ነፃነት (ኦሾ)
ተርጓሚ ፦ ዘላለም ንጉሴ

መፈለግ (መውደድ) ከሰዎች ታላላቅ ፍላጎቶች አንዱ ነው:: ስለዚህ ፍቅር ህልውናን ይዞ ይኖራል። የሰው ልጆች እስካሉ ድረስ የፍቅርን ያህል ትልቅ ነገር አያገኙም፡፡ በምድር ላይ የሚገኝ ግን የምድር ያልሆነ ነገር ነው:: በፀሐይ ፊት እንደንስር የምትበሩበት ክንፍ ይሰጣችኋል።

ያለ ፍቅር አክናፋት አይኖሯችሁም፡፡ እጅጉን አስፈላጊ የመንፈስ ምግብና ተፈላጊ ነገር ከመሆኑ የተነሳ በዙሪያው ችግሮች ይከቡታል፡፡ ፍቅረኛህ ወይንም ፍቅረኛሽን ነገር የራስህ /ሽ/ ማድረግ ትፈልጋላችሁ ዛሬ ውብ ነገር አሳልፋችኋል፣ ለነገ ደግሞ ትጨነቃላችሁ፡፡ ስለዚህ ትዳር ይመጣል። ፍቅረኛችን ነገ እንዳትከዳን ስለምንፈራ በማህበረሰብና በሕግ ፊት ውል እንፈርማለን። ፍፁም አስቀያሚና ዘግናኝ ነገር ነው:: ፍቅርን ወደ ውል መለወጥ፣ ህግን ከፍቅር ማስቀደም ማለት፣ ማህበረሰብን ከራስህ ህልውና ማስቀደም ማለት ነው፡፡ የፍርድ ቤቶችን የጦር ሠራዊቱን፣ የፖሊሲንና የዳኞችን ከለላ በመሻት ጥምረታችሁን የተረጋገጠ ለማድረግ መጣር ማለት ነው:: ነገ ጠዋት ማንም አያውቅም፡፡ ፍቅር እንደነፋስ ሽውታ ሆኖ ይመጣል። ድጋሚ ታገኘው ይሆናል፣ ፈጽሞ ላይመጣም ይችላል። ሳይመጣ ከቀረ በህግና በትዳር የተነሳ ብቻ፣ በማህበረሰብ ክብር ከመጨነቅ የተነሳ ብቻ፣ በዓለም ዙሪያ ያሉት ጥንዶች ሕይወት ሁሉ ማለት ይቻላል፣ ወደ ወሲብ ንግድ ይለወጣል።

ከፍቅር በስተቀር በሌላ በማንኛውም ምክንያት፣ ለደህንነት ወይንም የገንዘብ ድጋፍ ለማግኘት ተብሎ ከማትወዳት ሴት ጋር መኖር፣ ከማታውቂው ወንድ ጋር መኖር ኑሯችሁን የወሲብ ንግድ ያደርገዋል፡ የወሲብ ንግድ ከዓለም ሙሉ ለሙሉ እንዲጠፋ እፈልጋለሁ፡፡ ኃይማኖቶች ሁሉ የወሲብ ንግድ መኖር የለበትም ይላሉ፡፡ የሰው ልጅ አይረቤነት የሚታየው ይህን በመሳሰሉ ሁኔታዎች ላይ ነው።

ከእምነት ማጣት ውስጥ ፍቅርን የሚያበለጽግና የሚያሳድግ ምንም ነገር የለም፡፡ ከነአካቴው ያጠፋዋል። አፍቅር ግን ሁለተኛ አታጥፋው፡፡ ፍቅር ትክክለኛ የሚሆነው ነፃነትን ሲያጎናፅፍ ብቻ ነው::

ቅድመ ሁኔታው ይህ ይሁን። እውነተኛ ፍቅር የሚባለው የሌላውን ሰው ነፃነት የማይጋፋ ከሆነ ነው:: የሌላውን ሰው የግል ኑሮና ማንነቱን ያከብራል፡፡ ዳሩ ግን በዓለም ዙሪያ የምናያቸው ፍቅረኞች ጥረት ግን ምንም ነገር የግል መሆን የለበትም የሚል ነው፣ ሁሉም ምስጢሮች ሊነገራቸው ይገባል። ግላዊነትን ይጠላሉ፣ ይፈራሉ፡፡ አንዳቸው የሌላቸውን ማንነት ያጠፋሉ፣ ይህን በማድረጋቸውም ሕይወታቸው ርካታና ደስታ የተሞላበት አንደሚሆን ያስባሉ፡፡ ሰቀቀናቸው እለት እለት እየጨመረ ይመጣል::

አፍቃሪ ሁን፤ እውነተኛ ሆነ ማንኛውም ነገርም ዘወትር እንደሚለዋወጥ አስታውስ፡፡ ትክክለኛ ፍቅር ዘለዓለም ይኖራል የሚል የተሳሳተ ግንዛቤ ተቀብለህ ሊሆን ይችላል። ትክክለኛ ጽጌሬዳ አበባ ዘለዓለም አትኖርም፡፡ ህያው ፍጥረት እንኳን አንድ ቀን መሞት ይኖርበታል። ሕልውና የማያቋርጥ ለውጥ ነው፡፡ ፍቅር ዘለዓለም ይኖራል የሚለው ሀሳብ እውነት ቢሆን ኖሮ  ፍቅር አንድ ቀን ቢጠፋ የምንደርስበት ምክንያታዊ ድምዳሜ፣ እውነተኛ ፍቅር አልነበረም የሚል ይሆናል፡፡

እውነተኛ ፍቅር በድንገት የሚይዝህ አንተ ስለጣርክ አይደለም:: በቃ ተፈጥሮ ስጦታ ነች:: ሲመጣ ግን አንድ ቀን እንዳመጣጡ ይሄዳል ብለህ ብትጨነቅ ኖሮ ከነአካቴው ባልተቀበልከው ነበር፡፡ ግን የሚያስጨንቅ ነገር የለም:: ምክንያቱም አንድ አበባ ሲከስም ሌላ አበባ ይፈነዳል።

ካልሆነ ግን ብዙም ሳትቆይ የሞተና የረገፈ አበባ ላይ ሙጥኝ ብለህ ትቀራለህ፡፡ እውነታውም ይኸው ነው። ሰዎች በአንድ ወቅት ህያው የነበረ የሞት ፍቅርን የሙጥኝ ብለው ይታያሉ:: አሁን ወደ ትዝታና ስቃይ ተለውጧል፡፡ ለክብርና ለህግ ካለህ ጭንቀት የተነሳም ታስረህ ትቀራለህ።

ካርል ማርክስ ለዚህ ትክክለኛውን ሀሳብ አቅርቧል፣ ይህም በኮሚኒውዝም ስርዓት ውስጥ ምንም አይነት ትዳር አይኖርም፡፡ ሩሲያ ውስጥ አብዮቱ ከፈነዳ በኋላም፣ በመጀመሪያዎቹ አራት አምስት ዓመታት ውስጥ ፍቅርን ነፃነት ለማድረግ ሞክረዋል። ግን የካርል ማርክስ ጽንሰ ሀሳብ ወደ ተግባር ሲለወጥ ችግር ተፈጠረ ምክንያቱም ትዳር ከሌለ ቤተሰብ ይጠፋል፡፡ ቤተስብ ከጠፋ ደግሞ የማህበረሰቡና የህዝቡ /ሀገር/ የጀርባ አጥንትና መሠረት ነው፡፡ ቤተሰብ ከጠፋ ሀገርም መጥፋቱ አይቀርም፡፡
ከአብዮቱ እውን መሆን ከአምስት ዓመታት በኋላ የሩሲያ ኮሚውኒስት ፓርቲ ይህን ሀሳብ ሙሉ በሙሉ ለወጠው። ትዳር ዳግመኛ ድጋፍን አገኘ፡፡ ፍቺ ተፈቅዶ ግን መፋታት እጅግ ከባድ ሆነ፡፡ ምክንያቱም ቤተሰቡ እንዳለ መቆየት ይችላል የሀገሪቱን አንድነት ለማጠናከርም ይረዳል:: ያለ ሀገር ፖለቲከኞችም ሆኑ መንግሥት ሊኖር አይችልም። ትዳር የመጣው የግል ንብረት ከሚለው ሀሳብ ጋር ተያየዞ ነው የሚለውን የማርክስን ሀሳብ አላነሱም፡፡ ምክንያቱም የግል ንብረት ሲጠፋ ትዳርም አንድ ላይ ይጠፋል:: ከዚያ በኋላ አልተነጋገሩበትም፡፡

ዓለም ወደ ብዙ አካላት እንድትከፋፈል አልፈልግም። ነፃ ግለሰቦች በራሱ ጊዜ በሚቀጣጠል ፍቅር ውስጥ፣ በፀጥታና በደስታ የሚኖሩባት አንድ ዓለም እንድትፈጠር እፈልጋለሁ፡፡ ገነትን እዚሁ መፍጠር እንችላለን፡፡ ገነትን ለመፍጠር የሚያስፈልገን እምቅ ሀይል ሁሉ ቢኖረንም እየተጠቀምንበት አይደለም፡፡ በተቃራኒው ግን ብዙ እንቅፋቶችን እየፈጠርን እንገኛለን።

እኔ የፍቅር ተፃራሪ አይደለሁም፡፡ ፍቅርን እጅግ እደግፈዋለሁ፡፡ ሁለት ሰዎች ሕይወታቸውን ሙሉ አብረው ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ መለያየት አለባችሁ ማለት ሳይሆን፣ ይህን አብሮ መኖር የሚመሠረተው ፍቅር ላይ ብቻ መሆንና የሌላውን ግላዊ ሕይወትና ነፍስ በማይነካ ነፃነቱን በሚጠብቅ ሁኔታ መሆን አለበት፡፡ ይህ የሌላው ሰው ክብር ነው።

አፍቃሪ መሆን ትችላለህ፣ ፍቅር መሆን ትችላለህ:: አፍቃሪ ብቻ ከሆንክ ፍቅርን ራሱን ብቻ ከሆንክ፣ ፍቅር ወደ ጥላቻ የሚለወጥበትን ምንም ዓይነት እድል አትሰጠውም፡፡ ተስፋ የምትጥልበት ነገር ስለማይኖር ድንገተኛ ነገር ሊረብሽህ አይችልም፡፡ ስለፍቅር የምንናገረው ግን በመንፈሳዊ ክስተትነቱ እንጂ ከስነ-ተፈጥሮ አንፃር አይደለም፡፡ ስነ ፍጥረት ሴሰኝነትን እንጂ ፍቅር አይደለም፡፡ የስነ-ፍጥረት ዓላማ ዘርን መተካት ሲሆን፣ የፍቅር ሀሳብ ስነ-ተፈጥሯዊ ብቻ ነው፡፡ ሰው ተራክቦ ከፈፀመ በኋላ ቢያንስ ለሚቀጥሉት ሃያ አራት ሰዓታት ፍቅረኛው እንደማትፈልገው ይሰማዋል፡፡ ይህ ደግሞ ከእድሜ ጋር የተያያዘ ነው፡፡ እድሜህ እየገፋ ሲሄድ ጊዜው አርባ ስምንት ሰአት፣ ወደ ሰባ ሁለት ሰአት... እያለ ይቀጥላል።

@Zephilosophy
@Zephilosophy
2.5K viewsedited  05:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-28 08:51:09 ከፍቅር ወደ አፍቃሪነት...........1

ምንጭ ፦ ነፃነት (ኦሾ)
ተርጓሚ ፦ ዘላለም ንጉሴ

ፍቅር  ሁለት ፍፁም የተለያዩ እንደውም ሙሉ ለሙሉ ተቃራኒ ትርጉሞች ሊኖሩት ይችላሉ፡፡ አንዱ ትርጉም ፍቅር በፍቅር ግንኙነት መልኩ ሲገለጽ እና ሌላው ደግም ፍቅር በራሱ ህልውና ይዞ ሲገኝ ነው:: ፍቅር ወደ ፍቅር ግንኙነት በሚለወጥበት ወቅት ባርነት ይሆናል:: ምክንያቱም የምንጠብቃቸውና የሚጠበቁብን ነገሮች እንዲሁም መረበሽ እና ፍርሀትን ይፈጥሩብናል፡፡ ከሁለቱም ወገንም እኔ እበልጥ ስሜት ይመጣል፡፡ የኃይል እሽቅድምድም ይሆናል:: የፍቅር ግንኙነት ትክክል አይደለም:: ፍቅር ህልውና ይዞ ሲገኝ ግን ሙሉ በሙሉ የተለየ ነገር ይሆናል፣ ስታፈቅር ከፍቅር ሌላ የፍቅር ግንኙነት እየፈጠርክ አይደለም ማለት ነው:: ፍቅርህ እንደ አበቦች ጥዑም መዓዛ ይሆናል። የፍቅር ግንኙነት አይፈጠር፣ ይህን አድርግ፣ ባህሪህ እንዲህ ይሁን አይልህም:: ከአንተ ምንም አይፈልግም። ያካፍላል። በማካፈሉም ምንም ሽልማት አይፈልግም፡፡ ማካፈሉ በራሱ ሽልማት ነው፡፡

ፍቅር ለአንተ እንደ አበቦች መዓዛ በሚሆንበት ጊዜ ታላቅ ውበት ይኖረዋል ከሰብዓዊነት በላይ የመጠቀ መለኮታዊ ነገር ይኖረዋል፡፡

ፍቅር ብቻውን ከመጣብህ ምንም ልታደርገው አትችልም፡፡ በማንኛውም ሰው ላይ አሳርን አያመጣም አንተም በማንኛውም ሰው እንድትታሰር አይፈቅድም፡፡

ግን ከልጅነት አንስቶ የፍቅር ግንኙነቶችን የመፍጠር ልምድ አለህ፡፡ ከማታውቀው ወንድ ጋር የአባትና የልጅ ግንኙነት ትፈጥራለህ:: አባትህ መሆኑን በፍፁም ርግጠኛ ልትሆን አትችልም፡፡

አንድ የሰዎችን መዳፎች በመመልከት ዕጣ ፈንታቸውን ስለሚተነብይ ሰው የሰማሁት ታሪክ አለ። በእጅ መዳፍ ንባብና በአስትሮሎጂ በመሳሰሉት እንዲሁም በእግዚአብሔርም የማያምን አንድ ወጣት ወደዚሁ ሰው ይሄድና፣ ሳይንስህ ትክክል ከሆነ እጄን አንብብና አባቴ የት እንደሚገኝ ንገረኝ አለው።»

አዋቂውም መዳፉን ተመልክቶ እንዲህ አለው «አባትህ አሳ እያጠመደ ነው፡፡» ወጣቱ ኢአማኒ ሳቀ፡፡ «እኔ የምለው ይህንኑ ነው፣ የማይረባ ሥራ ነው:: አባቴ ከሞተ ሶስት ዓመት ሆኖታል፤ ዛሬ እንዴት አሳ ለማጥመድ ይሄዳል።>>

አዋቂውም ሲመልስ፣ «ይህ እኔን አያገባኝም፤ እውነቱ ግን ያ የሞተው ሰው አባትህ ያለመሆኑ ነው፡፡ ትክክለኛ አባትህ አሳ እያጠመደ ነው፡፡ ወደ እናትህ ሂድና ጠይቃት፡፡ ታማኝና እውነተኛ ከሆነች የሞተው ሰው አባትህ እንዳልሆነ ትነግርሀለች። አንተ ግን አባትህ ነው ስለተባልክ ከእሱ ጋር የአባትና የልጅ ፍቅር ግንኙነት ፈጥረሀል፡፡

ሕይወታችሁ በሙሉ በብዙ ዓይነት ግንኙነቶች የተሞላ ነው:: ይህ መሰል ግንኙነቶች ደግሞ እውነትም ይሁን ሀሰተኛ፣ እጅግ ውስብስብ የሆነ ስነልቦናዊ ባርነትን ይፈጥራል። ወይ ሌላውን ባርያ ታደርጋለህ፡፡ ወይንም ራስህ ባርያ ትሆናለህ::

ሌላው መታወስ ያለበት ነጥብ ደግም ራስህን ባርያ ሳታደርግ ሌላውን ሰው ባርያ ማድረግ አትችልም፡፡ ባርነት ባለሁለት ሶስት ሰይፍ ነው፡፡ አንደኛው የበለጠ ጠንካራ፣ ሌላው የበለጠ ደካማ ሊሆን ይችላል፤ ግን በሁሉም የፍቅር ግንኙነቶች ውስጥ አንደኛው አሳሪ ሌላው ታሳሪ ይሆናል። ከእሱ አንፃር ሲመለከተው እሱ አሳሪው አንተ ደግሞ ታሳሪ ትሆናለህ። የሰው ልጅ ይህን በመሰለ ሀዘንና ሰቆቃ የመኖሩ ዋነኛ ሀቅና ምክንያት መካከል አንዱ ይኸው ነው፡፡

ጥላቻ ደግሞ ከፍቅርህ የጠነከረ ግንኙነት ይፈጥራል ምክንያቱም ፍቅርህ ከአንገት በላይ ነው:: ጥላቻህ እጅግ ጥልቅ ነው:: ጥላቻህን የወረስከው ከእነስሳዊነት ባህሪህ ነው:: ፍቅርህ ለመጪው ሕይወትህ ያለህ ብቸኛ እምቅ ኃይልህ ነው:: እውን የሆነ ክስተት ሳይሆን ወደፊት ፍሬ የሚያፈራ ዘር ነው:: ጥላቻህ ግን ሙሉ በሙሉ በተግባር ላይ የሚገኝ፣ እጅግ የጎለመሰ፣ ያለፈው የብዙ ሺህ ዓመት ታሪክህ ህያው ቅርፅ ነው፡፡ የሚያድግበት ጊዜና ቦታ የነበረው:: ለውጡ መከሰት የሚጀምረው ግን በሰው ልጆች ላይ ነው::

ግን ማንንም እኔን ከመጥላት ማገድ አልችልም ስለዚህ ማንም ሰው እንዲያፈቅረኝ ማድረግ አልችልም:: ልገልፀው የምችለው ነገር ቢኖር ጥላቻም ሆነ ፍቅር የግንኙነት መልክ በሚይዝበት ጊዜ ንፅሕናውን እንደሚያጣ ብቻ
ነው፡፡

ፍቅርህን ህልውናህ አድርገው፡፡ ፍቅር
እንዲይዝህ ሳይሆን አፍቃሪ እንድትሆን ጣር፡ ፍቅር ባሪያህ ነው። ለአንተ ፍቅር የህልውናህ ጥፁም መዓዛ ነው:: ብቻህን ብትሆን እንኳን በአፍቃሪ ኃይል ትክበባለህ፡፡ የሞተ ነገርን ለምሳሌ ግዑዝ ወንበርን ብትዳስስ እንኳን ከእጅህ ፍቅር ይፈልቃል:: ፍቅርህን የምትሰጠው ለምንም ወይንም ለማንም ሊሆን ይችላል፡፡

በፍቅር ስሜት ውስጥ መሆን የለብክም እያልኩ አይደለም፡፡ ዳሩ ግን በፍቅር ስሜት ውስጥ መኖር የምትችለው ቀድሞውን የፍቅር ግንኙነት አስተሳሰብህን በምትተውበት ጊዜ ነው:: ፍቅር በሰዎች መሀል የሚመሰረት ግንኙነት ዓይደለም።

ሁለት ሰዎች አንድ ላይ እጅግ አፍቃሪ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ አፍቃሪነታቸው በጨመረ ቁጥር በመካከላቸው የሚፈጠረው የፍቅር ግንኙነት ይጠፋል። አፍቃሪነታቸው በጨመረ መጠን፣ አንዳቸው ከሌላቸው የሚፈልጉትንና አንዳቸው በሌላቸው የሚጥሉት ተስፋ ይቀንሳል፡፡ ውስጥም ይገባሉ፡፡

በውል ሳይተዋወቁ ፍቅርን ብቻ እያሰቡ ሲወዳደሱ በመጨረሻ መወቃቀስ ይጀምራሉ፡፡ ለዚህም ነው ምንም ዓይነት ተስፋ ማድረግ እንደማያስፈልግ ልታስታውስ የምፈልገው፡፡ ፍቅር የራስህ ውስጣዊ እድገት መሆኑን አውቀህ አፍቅር። ፍቅርህ ወደላቀ ብርሀን፣ ወደላቀ እውነትና ነፃነት ከፍ ያደርግሀል፡፡ ግን የፍቅር ግንኙነት አትፍጠር፡፡

አንድ ነገር ብቻ አስታውስ፣ ፍቅር ማንኛውንም ዓይነት መጥፎ ነገር የማጥፋት አቅም አለው፣ ፍቅርን ወደ ፍቅር ግንኙነት እንዲለወጥ ከፈቀድክለት ግን፣ ፍቅር ይጠፋና የጓደኝነት ስሜት በውስጥህ ያለው ውብ ባህሪ ሲሆን ጓደኝነት ግን ወደ ትስስር ያመራል፡፡

ስለዚህ ፍቅር መልካም ነገር ነው:: እንደውም ፍቅር የሌለበት ነገር
ሁሉ ስህተት ነው:: ግን ፍቅር ከፍተኛ ዋጋ በመሆኑ ከማንኛቸውም ዓይነት በካይ መርዘኛ ነገሮች መጠበቅ አለበት፡፡ ትስስር ይበክለዋል። ዓለም በግለሰቦች የተሞላች እንድትሆን እፈልጋለሁ:: «ጥንድ» የሚለው ቃል እንኳን ይጎዳኛል፡፡ የሁለት ግለሰቦችን ህልውና አጠፋችሁ ማለት ነው፡፡ ጥንድ በራሱ ውበት የለውም፡፡

ዓለም በግለሰቦች ብቻ የተሞላች ትሁን፡፡ ፍቅር በራሱ ጊዜ ጎምርቶ ሲፈነዳ ፍቅርን ዘምሩት ፣ ጨፍሩት፣ ኑሩት፣ ግን ፍቅርን ወደ ሰንሰለት አትለውጡት፡፡ ሰውን በባርነት ለመያዝ አትሞክሩ፣ ሌላም ሰው በባርነት እንዲይዛችሁ አትፍቀዱ፡፡

ነፃ ግለሰቦችን የያዘች ዓለም በትክክል ነፃ አለም ትሆናለች።

ይቀጥላል

@Zephilosophy
@Zephilosophy
2.4K views05:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-19 19:51:24 የሚያስፈልገው ምን ያህል ነው?
Repost

ከዘመን ዘመን ሳይንስ እየተራቀቀ ተክኖሎጂ እየመጠቀ ለሰው ልጅ መሰረታዊ ፍላጎትን የሚያቀል ፈጠራ እየተበራከተ መጥቷል። ሩጫን እና ሸክምን የሚቀንሱ እልፍ ግኝቶች በገፍ ቢቀርቡም ሩጫ አልቀለለም ሸኽም አልቀነሰም።

የየእለት ኑሯችሁን ተመልከቱ። ለቅንጦት ተብለው የሚጀመሩ ነገሮች ሳይቆዩ መሰረታዊ ፍላጎት ይሆናሉ። ለትርፍ ጊዜ ታስበው የተጀመሩቱ በመደበኛ ጊዜ የሚከወኑ ይሆናሉ። ጊዜን ይቆጥባሉ ተብለው የተጀመሩቱ ጊዜን የሚሻሙ ሆነው ይገኛሉ።

ምንድነው እየሆነ ያለው?
ፌስቡክ የቅንጦት አልነበር? አሁን መሰረታዊ ፍላጎት ወደ መሆን ራሱን አሸጋግሯል።

በፊት ሰዎች ከተረፋቸው ገንዘብ ላይ በመቀነስ የሚሸምቱት ቁስ ዛሬ ላይ መሰረታዊ ፍጆታ ከመሆን አልፎ መወዳደሪያ ሆኗል።

የሚያስፈልገን ምን ያህል ነው? በየትኛው ፍላጎትስ መዳኘት አለብን? የማይሞላ ፍላጎትን ለማስታገስ የምንሮጠው እስከየት (እስከመች) ነው?

ህይወትን ያቀላል ተብሎ የተጀመረው በሂደት ህይወትን የሚያከብድ ይሆናል። ጊዜን ለመቆጠብ የተጀመረው መንገድ ጊዜን ይበላል። ለቅንጦት ያህል እንከውነው የነበረው መሰረታዊ ፍላጎት ወደ መሆን ይሻጋገራል።

የሚያስፈልገን ጥቂት ብቻ ሆኖ አላስፈላጊ የሆነውን ለማግበስበስ ታትረን ይሆን?  ወይስ የሚያስፈልገንን ሁሉ ለማከማቸት ተጋን?

@Tfanos
@Zephilosophy
5.0K viewsedited  16:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ