Get Mystery Box with random crypto!

ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ Philosophy

የቴሌግራም ቻናል አርማ zephilosophy — ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ Philosophy
የሰርጥ አድራሻ: @zephilosophy
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.37K
የሰርጥ መግለጫ

ፍልስፍና  እውነትን በመፈለግ- ሀሳዊ እምነቶችን በማጋለጥ እና ጭፍን አመለካከቶችን በጥበብ በመመርመር ወደ ላቀ አሰተሳሰብ ያሻግራል።
በዚህ ቻናል አለም ላይ ያሉ ፍልስፍናዎች ፤ ርዕዮት አለሞች ፤  ሀይሞኖቶች እና አስተሳሰቦች በነፃነት ይዳሰሳሉ።

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2024-05-25 13:12:50 ባሕርን መሆን _

ባንድ ወቅት በሕይወቱ ደስታን ያጣው ታዳጊ ወጣት አንድ የዕድሜ ባለጸጋን ሽማግሌ ሕይወት እንዳማረረችው ገልጾ መፍትሄ እንዲጠቁሙት ጠየቃቸው፡፡ ሽማግሌው የወጣቱን ሀሳብ በጥሞና ካደመጡ በኋላ በእፍኙ ሙሉ ጥሬ ጨው በብርጭቆ ውሃ ጨምሮ በጥብጦ እንዲጠጣው አዘዙትና “ጣምናው እንዴት ነው?” በማለት ጠየቁት፡፡ ፊቱን አኮሳትሮ “በጣም አስቀያሚ ነው!” ሲል መለሰላቸው፡፡ ሽማግሌው ፈገግታ እያሳዩት ወጣቱን ወደ ባሕር ዳርቻ ወስደው  ሌላ ጭብጥ ሙሉ ጨው  ባሕሩ ውስጥ እንዲጨምርበት አመላከቱት፡፡

በመቀጠልም  ከባሕሩ ጨልፎ እንዲጠጣ ካደረጉ በኋላ “ጣዕሙ እንዴት ነው?” ሲሉ በድጋሜ ጥያቄ አቀረቡለት፡፡ “ጥሩ ነው” በማለት መለሰ ታዳጊው፡፡ አስከትለውም  “የጨው ኮምጣጣነትና ያ አስቀያሚው ስሜት ተለይቶሃል?” በማለት ጠየቁት፡፡ “በፍጹም” ሲል መለሰ ወጣቱ፡፡

ከዚህ ሁሉ የተግብር ትምህርት ቀጥሎ ሽማግሌው የወጣቱን እጅ ይዘው ከጎኑ ተቀመጡና ይሄንን መከሩት፡፡ በሕይወት ጎዳና የምታደርጋቸው ትግሎች እንደ ንጹህ ጥሬ ጨው ናቸው፡፡ ነገር ግን የስቃዩ መጠን ተመሳሳይ ቢሆንም የምንሸከመው ስቃይ የሚወሰነው በምንይዝበት ዕቃ መጠን ይወሰናል፤ ችግሩን የምናስተናግድበት አግባብም የሚፈጥረውን ጫና በዛው ልክ ይለያየዋል፡፡ ችግሩ ሲጠናብህ ልታደርገው የሚገባው ዋናው ነገር ምልከታህን ማስፋት ብርጭቆውን ሳይሆን ባሕሩን መሆን ነው ትልቁ የአኗኗር መላው፡፡
እናም ብርጭቆ መሆንህን አቁመህ ባሕሩን ሁን በማለት አሰናበቱት፡፡

       ምንጭ፡-Stop being a glass,
                    Become a lake

 @zephilosophy
5.5K views10:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-24 19:20:27 ኑዛዜው  

አንድ ሰው ይሞታል።17 ግመሎች እና 3 ልጆች ነበሩት።ኑዛዜ ሲነበብ "የግመሎቼን ግማሽ ለመጀመሪያው ልጄ አንድ ሶስተኛውን ለሁለተኛው ልጄ እንዲሁም የግመሎቼን አንድ ዘጠነኛ ለመጨረሻው ልጄ ተናዝዣለሁ"ይላል። ልጆቹ ግራ ተጋቡ ምንድን ነው ማድረግ የሚችሉት? የ17ቱ ግመሎች ግማሽ ለመጀመሪያው ልጅ ይሰጥ ተብሏል የ17 ግማሽ 8 ይሆን እና አንድ ግመል ይተርፋል እና አንዱ ግመል ሊሰነጠቅ ነዉ? ይሄንንም ቢያደርጉ እንኳ መፍትሄ አይሆንም ምክንያቱም የግመሎቹ አንድ ሶስተኛ ደግሞ ለሁለተኛው ልጅ ይሰጥልኝ ብሏል አባትዬው። ይሄም ቢሆን ችግሩን አይፈታውም።የግመሎቹ አንድ ዘጠነኛ ደግሞስ ለሦስተኛው ልጅ ይሰጥ ይላል ኑዛዜው። ግመሎቹ ሁሉ ተቆራርጠው ማለቃቸው እኮ ነው።ለችግሩ መፍትሄ ለማግኘት በመንደሩ የታወቀ የሒሳብ ምሁር ዘንድ አመሩ።ሰውየው በጉዳዩ ላይ በጥልቀት ቢያስብበትም መፍትሄ ግን ሊያገኝለት አልቻለም።           

"እኔ በህይወቴ ቁጥሮችን እንጂ ግመሎችን አካፍዬ አላውቅም ይሄ ተራ ማጃጃያ ነው የሚመስለኝ።ኑዛዜው በትክክል መተግበር ካለበት ግን ግመሎቹን መሰንጠቅ ግድ ነው።" አላቸው ልጆቹ በሰውየው ምክር አልተስማሙም። ግመሎቹ እንዲሰነጠቁ አይፈልጉም። ታዲያ ምን ተሻለ??? ነገሩን በቅርበት ሲከታተል የነበረ አንድ ሰው ወደ እነሱ ጠጋ ብሎ "ከቁጥር ይልቅ ስለ ግመሎች የሚያውቅ ሰው ብታማክሩ ይሻላችኋል" ሲል መከራቸው። እነሱም በሰውዬው ምክር ተስማምተው ስለ ግመሎች የሚያውቅ ሰው ሲፈልጉ አንድ እርጅና የተጫጫነው፣ያልተማረ፣ነገር ግን ከህይወት ልምድ ብልህነትን የቀሰመ አዛውንት አገኙና ችግራቸውን አማከሩት።

አዛውንቱ ሰው ስቆ "አታስቡ ነገሩ ቀላል ነው"አላቸው ከዛም አዛውንቱ የራሱን አንድ ግመል አበደራቸውና የግመሎቹ ቁጥር 18 ሆነ "ከዚህ በኋላ ተካፈሉ" አላቸው። በኑዛዜው መሰረት የግመሎቹ ግማሽ 9 ነውና ለመጀመሪያው ልጅ ተሰጠው፤ደስም አለው። የግመሎቹ አንድ በሶስተኛ 6 ነውና ለሁለተኛው ልጅ ተሰጠው፤ደስም አለው። የግመሎቹ አንድ ዘጠነኛ 2 ነውና ለሶስተኛው ልጅ ተሰጠው፤ደስም አለው።አንድ ግመል ቀረ ሽማግሌው አንድ ግመል አበድሯቸው አልነበር፣ያበደራቸውን አንድ ግመል መልሶ ወሰደ።"አሁን መሄድ ትችላላችሁ" ብሎ አሰናበታቸው፤እነሱም ተደሰቱ።         

ተራ እውቀት(Knowledge) ተግባራዊ አይደለም።በልምድ የካበተ ጥበብ(wisdom) ግን ተግባራዊ እና ተጨባጭ ነው።ተግባራዊ የማይሆን እውቀት ተራ የቃላት ጨዋታ ነው ጥበብ እና ብልህነት ግን ከህይወት ልምድ የተጨለፉ ናቸው።                               

Osho

@zephilosophy
5.1K viewsedited  16:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-21 23:17:23 ግንኙነቶች (RELATIONSHIPS)

ሰዎችን ለመገምገምና የመሰለንን ማንነት ለመስጠት ምን ያህል ፈጣኖች ነን! ለሌሎች የራሳችንን የፈጠራ ማንነት ስንሰጣቸውና ስንሰይማቸው ኢጐአችን
ይደሰታል።

እያንዳንዱ የሰው ልጅ እንደዚያ እንዲያስብና እንዲያምን በሁኔታዎች ተቃኝቷል (conditioned) ሆኗል። ኹሉም ሰው በውልደት ፣ ወይም በልጅነት ገጠመኝ እንዲሁም ባደገበት ባህላዊ መስተጋብር ተቃኝቶ እንደዚያ ለማሰብና ለማመን ይገደዳል።

ይህ ቅኝታቸው ነው እንጂ ማንነታቸው አይደለም። ለሰዎች ስም ስንሰጥና እንዲህ ናቸው ብለን ስንበይን ማንነታቸውን ከሁኔታዊ ቅኝታቸው ጋር አደናግረናል ማለት ነው። ለሰዎች ሃሰተኛ ማንነት ስንሰጣቸው እኛ የፈጠርነው ማንነት ለእነርሱም ሆነ ለእኛ እስር ቤት ይሆንብናል።

በሰዎች ላይ መፍረድ ማቆም ማለት እነርሱ የማያደርጉትን አለማየት ማለት አይደለም። ባሕርያቸውን እንዳለ መቀበልና ማንነታቸው ሳይሆን የተቃኙበት (conditioning) ሁኔታ መሆኑን መገንዘብ መቻል ማለት ነው። ለዚያ ሰው ማንነት ከመፍጠርም መታቀብ ማለት ነው።

ይህንን ማድረግ ስትጀምሩ ሰዎችን በቅኝታቸው፣ በአካላቸውና በአእምሮ እይታችሁ መሰየም ታቆማላችሁ። የዚያኔ ግንኙነታችሁ በኢጐ ከመመራት ነፃ ይወጣል።

ኢጐ ሕይወታችሁን እየመራው ከሆነ ሃሳብ ፣ ስሜትና ድርጊታችሁ በሙሉ ከፍርሀትና ከምኞት ይመነጫሉ። በመሆኑም ከሌሎች ጋር ያላችሁ ግንኙነት እነርሱን በመፍራት ወይም ከእነርሱ ነገሮችን በመፈለግ ይመሠረታል።

ከግንኙነት አጋራችሁ የምትፈልጉት ደስታ ፣ ቁሳቁስ ፣ ክብር ፣ ትኩረት ወይም ለራሳችሁ ያላችሁን አመለካከት ለማጉላት እነርሱን እንደ ማነፃፀሪያ መጠቀም ሊሆን ይችላል። እናንተ ከእነርሱ የተሻላችሁ መሆናችሁን ለማሳየት የግድ እነርሱን ልትፈልጉ ትችላላችሁ። የምትፈሩት ነገር ደግሞ ነገሮች ከፈለጋችሁት ተቃራኒ ሊሆኑ ከቻሉ የሚፈጠርባችሁን የበታችነት ስሜት ሊሆን ይችላል።

ሙሉ ትኩረታችሁን አሁናዊ ቅጽበት ላይ ስታደርጉ ከኢጐ ባሻገር የሆነ እይታ ይኖራችኋል። አሁናዊ ቅጽበትን እንደመጠቀሚያ ማየት ታቆማላችሁ። የዚያኔ ራሳችሁን ከሌሎች ጋር በማነፃፀር ከፍ ማድረጋችሁ ያበቃል። ከምትገናኙት ሰው ጋር ሳላችሁ ሙሉ ትኩረታችሁን ለእነርሱ ስጡ። የዚያኔ የእነርሱ ያለፈና የወደፊት ታሪክ ወይም እናንተ የሰጣችኋቸው መለያ ማንነት ይወገዳል። ከኢጐ ፣ ከፍላጐትና ከፍርሀት የተላቀቀ እይታ ይኖራችኋል። ስለዚህም ትኩረት ወይም ንቁ የሆነ ፀጥታ (alert stillness) ወሳኝ ቁልፍ ነው።

ነገሮችን መፈለግና መፍራት የሌለበት ነፃ ግንኙነት ምን ያህል አስደናቂ ሊሆን እንደሚችል አስቡ። ፍቅር ምንም ነገር አይፈልግም ፤ በምንም አይፈራምም።

የእርሷ ያለፈ ገጠመኝ ያንተም ቢሆን ፤ ሕመሟ ሕመምህ ቢሆን ፤ የነበራት የማስተዋል ደረጃ ያንተም ቢሆን አንተም እርሷ ያደረገችውን ታደርግ ነበር። ይህንን ሃቅ በመረዳት ብቻ ርኅራኄ ፣ ይቅርታና ሰላምን ወደ ግንኙነታችሁ ማስገባት ትችላላችሁ።

የቀረቧችሁን ሰዎች በሙሉ፤ ወደ አሁናዊ ስፍራችሁ የሚገቡትን ኹሉ እንደተከበረ እንግዳ መቀበልና በማንነታቸው ማየት ስትጀምር እነርሱም መቀየር ይጀምራሉ።

አንድን ሰው በሰውነቱ ለማወቅ ስለ እርሱ ያለፈ ታሪክ ፣ የነበረበት ሁኔታና የመሳሰለውን ነገር አያስፈልጋችሁም። ብዙ ጊዜ ሰዎችን ማወቅ ስለእነርሱ ማወቅ ይመስለናል። ይሁንና ማወቅና ስለእነርሱ ማወቅ የተለያዩ ናቸው። አንዱ የሚታይን ነገር ማወቅ ሲሆን ሌላው ግን ከሃሳባችን ባሻገር በፍፁም ፀጥታ
እነርሱን ማወቅ ነው።

ለዕለታዊ ጉዳዮች እንደሆንን ስለሰዎች ማወቅ ጠቃሚ ነው። ይሁንና ስለእነርሱ ማወቅን ወደ ግል ግንኙነታችን ስናመጣው አስቸጋሪ ይሆናል። የሰዎች ታሪክ የግንኙነት እንቅፋትና አጥር ይሆናል። እውነተኛውን ሰብአዊ ማንነት ከማየትም ይጋርደናል። ስለዚህ ከሌሎች ጋር የሚኖረን ግንኙነት በአጥር የተለየ መሆን የለበትም። የሃሳብ እንቅፋት ከሌለ በኹሉም ሰብአዊ ግንኙነት ላይ ፍቅር
ይነግሳል።

አብዛኛው የሰው ግንኙነት በቃላት ልወውጥ ላይ የተመሠረተ የሃሳብ ዓለም መስተጋብር ነው። ፍፁም ፀጥታን ወደግንኙነት ማምጣት አስፈላጊ ነው። ፀጥታ የሌለበት ግንኙነት ፍሬያማ ሊሆን አይችልም። አብራችሁ በፀጥታ መቀመጥና መመሰጥ ያስፈልጋል።

ፀጥታ እናንተ የምትፈጥሩት ሳይሆን በራሱ ያለ ነገር ነው። ስለዚህ ፀጥታውን ማግኘት ብቻ ይጠበቅባችኋል። ፀጥታን የምታገኙት የአእምሮ ጩኸታችሁ
ሲቋረጥ ነው።

ፀጥታ ከጠፋ ግንኙነታችሁ በጩኸትና የአእምሮ ሁካታ የተሞላ ይሆናል። ችግርና ግጭትም የዘወትር ክስተታችሁ ይሆናል። ፀጥታ በዚያ ስፍራ ሲኖር ግን የትኛውም ችግር ይወገዳል።

እውነተኛ አድማጭነት ፀጥታን ወደ ግንኙነታችን የምናመጣበት ሌላው መንገድ ነው። ሰዎችን የእውነት ስታደምጧቸው የፀጥታ ስፍራ ትፈጥራላችሁ። ይሁን እንጂ የዚህ ዓይነቱ እውነተኛ አድማጭነት በብዛት የለም። ሰዎች በራሳቸው ሃሳብ በመዋጥ የተናጋሪውን ቃላት በመመዘን ፤ ቀጥሎ የሚናገሩትን በማሰብ የእውነት ከማድመጥ ይታጐላሉ። ወይም ደግሞ በራሳቸው ሃሳብ ርቀው በመሄድ ሙሉ በሙሉ የሚነገረውን አያደምጡ ይሆናል።

የእውነት ማድመጥ ማለት አሁናዊ ትኩረት ውስጥ መግባት ማለት ነው። ማድመጡ በራሱ ከሚነገሩት ቃላት በላይ ጠቃሚ ነው። በፍፁም አትኩሮት ስናደምጥ ተናጋሪውን አድማጩ በፀጥታ ስፍራ ይዋሃዳሉ። “ሌሎች” የሚል መነጠል ሳይኖር አንድነት ይሰፍናል።

ምንጭ፦ አሁናዊ ሀይልን ማግኘት
ትርጉም ፦ ሙሉቀን ታሪኩ

@Zephilosophy
@Zephilosophy
5.2K viewsedited  20:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-20 23:43:49 ያልታዩ ነገሮች - በርክሌ

ምንጭ ፦ ፍልስፍና ከዘርዐያዕቆብ እስከ ሶቅራጠስ
ፀሀፊ ፦ ፍሉይ አለም

በጥቅጥቅ ጫካ መሃል አንድ ዛፍ ወደቀ፤ ሆኖም በጫካው ውስጥ ማንም አልነበረም፡፡ ዛፉ ሲወድቅ እና መሬቱን ሲመታው ድምጽ ያሰማልን? የሆነ የሚሰማ አካል ሳይኖር ድምጽ ማውጣት ማለት ምን ማለት ነው? ያልተሰማ ድምጽ ምን አይነት እንደሆነ ማሰብ እንችላለን? በሃሳብህ ለማሰብ ሞክር፡፡ በአእምሮህ ውስጥ ምን አለ? ምን ይመስላል?

ይህ ሃሳብ የአስራ ስምንተኛ ክፍለ ዘመን አይሪሻዊ ፈላስፋ የሆነው ጆርጅ ባርክሌ የሃሳባዊነትን (Idealism) ፍልስፍና
እንዲመራመር አደረገው፡፡

ፈላስፎች እንግዳ ወደሆኑ ስፍራዎች ይጓዛሉ፤ ከሚጓዙባቸው ቦታዎች መሃል ሃሳባዊነት አንዱ ነው፡፡ ለምሳሌ ያህል ጓደኛህ ከአንተ አእምሮ ውጪ በውኑ ዓለም እንዳለ አረጋግጥልኝ?

ምናልባትም ወደ እርሱ በጣቶችህ ልትጠቁመኝ አልያም እየነካህ ልታሳየኝ ትችላለህ፡፡ “ይኸው እዚህ ጋር አለ፤ እንደዚህ አድርጌ በጥፊ ስመታው ያመዋል፣ ምላሽም ይሰጣል” ልትለኝ ትችላለህ።

ለበርክሌ ጓደኛህን መንካትህ ብቻውን በቂ ማስረጃ አይደለም፡፡ አዎ... ዓለምን የምትረዳበት የራስህ የስሜት ህዋሶች አሉህ ሆኖም ይህ ማለት እውነታውን ያረጋግጡልሃል ማለት አይደለም፡፡ ዳክዬ ማየትህ ብቻ ዳክዬ እንዳለች ማረጋገጫ አይሆንህም፡፡ ምናልባትም የተመለከትከው ዳክዬ መሳይ ነገር ይሆናል። ምናልባትም የምትኖርበት ዓለም ሁሉ በህልምህ ያለ ዓለም ሊሆን ይችላል፤ ጓደኛህም የህልም ዓለምህ አካል ይሆናል። በመንገድ ስትጓዝ የአእምሮ እክል ያለባቸው ሰዎች አጋጥመውህ አያውቅም? ልክ በራሳቸው ዓለም እንዳሉ ሆነው ይንቀሳቀሳሉ፣ ከማይታዩ ሰዎች ጋር ያወራሉ፣
ለብቻቸው ይስቃሉም---

የሰው አእምሮ ስለ ዓለም ያለው እውቀት የተገደበ ነው፡፡ ብዙ ጊዜ “መስሎኝ _ ነበረ” እንላለን፡፡ ነገሮችን የምናይበትም መንገድ ነገሮቹን በትክክል ይገልጻቸዋል” ማለት አንችልም፡፡ በዳክዬዋ እና በአንተ መካከልም እውቀትህን የሚገድብ ወንዝ አለ፡፡

ባርክሌ በሃሳብህ አንድ ነገርን አስብ ይልሃል፤ ለምሳሌ ብርቱካንን በሃሳብህ ሳል አሁን ደግሞ ብርቱካንን እንደማታየው ሆነህ ስለ ብርቱካን አስብ... ይህን ማድረግ በጥቂቱም ቢሆን ይከብዳል፤ ግን ትችላለህ፡፡ ለምሳሌ አይንህን ጨፍነህ ብርቱካንን በእጅህ እየነካካኸውና ሽታውን እያሸተትከው ወይም እየቀመስከው እንደሆነ ማሰብ
ትችላለህ።

አሁን ደግሞ ብርቱካኑ ያለ ሽታ እና ያለ ጣዕሙ፤ ያለ መዳሰስ ወይም ያለ መታየት ምን እንደሚመስል አስብ... ክብደቱ በእጅህ ላይ አይሰማህም፣ ስለ ቀለሙ እና ቅርጹ ማሰብ አትችልም፣ ጣዕሙን መቅመስ አልያም ሽታውን ማሽተትም አትችልም፡፡ ከሰውነት ህዋሳቶችህ ውጪ ሆነህ ብርቱካን ይህን ይመስላል ብለህ ግለጽልኝ?

አትችልም..... ብርቱካኑን የምትገልጽበት ምን ቀረህ? ምንም!

ይህንን ነው ባርክሌ ሲያጠቃልለው esse est percip ያለው። ሃረጉ የተፈጠረው ከላቲን ቃላት ሲሆን፣ ትርጓሜውም “መሆን ማለት ማስተዋል ነው፡፡” ወንበር በውኑ ዓለም ላይ ያለ ነገር ለመሆን የግድ የሚያስተውለው አካል ያስፈልገዋል። የሚዳስሰው አልያም የሚመለከተው ሰው ከሌለ ወንበሩ በውኑ ዓለም አለ ማለት አንችልም። በጫካ ውስጥ የወደቀው ዛፍ ሰሚ ከሌለው ድምፅ አያሰማም፣ ጓደኛህም አንተ ካላየኸው ወይም ካልነካኸው በውኑ ዓለም አለ ማለት አንችልም፡፡

የእውኑ ዓለምም የሚፈልቀው ከአንተ አእምሮ በመነሳት ነው፡፡ ህንጻዎችን ስትመለከት፣ የአበባ መዓዛን ስትምግ፣ ትኩስ ቡና ምላስህን ሲያቃጥለው እነዚህ ሁሉ በአእምሮህ ያሉ የውኑ ዓለም መገለጫዎች ናቸው፡፡ የውኑ ዓለምም የሚያየው (የሚያስተውለው)
አካል ሳይኖር ሲቀር መኖሩ ያበቃለታል፡፡

ሆኖም ግን ሰው (ወይም ሌላ አስተዋይ) በማይደርስበት በረሃ ላይም እኮ ዛፎች፣ ተራሮች፣ ድንጋዮች አሉ ... ይህ ስለምን ሆነ? ለምንስ እነርሱም አልተሰወሩም።

የባርክሌ ምላሽ ቀላል እና አጭር ነው፤ “እግዚአብሔር አለ!” ተመልካች በሌለበት ሁሉ፣ በአጽናፈ አለሙ በሙሉ እግዚአብሔር ተመልካች ነው፡፡ ለዛም ነው የተከልናት አበባ ወደ ቤታችን እስክንመለስ ድረስ ሳትሰወር የምትጠብቀን፤ ለዚህም ነው በጥቅጥቅ ደን መሃል የወደቀ ዛፍ ድምጽ የሚያሰማው፡፡

ይህ የባርክሌ ሃሳብ ከላይ ለሚያየው ቀልድ ይመስላል፤ ሆኖም በዘመናዊው የሳይንስ ዓለምም ቢሆን የባርክሌ ሃሳብ ከፊል እውነትነት አለው፡፡ ለምሳሌ እጅህን ብቆነጥጥህ የቱ ጋር ነው ህመሙ የሚሰማህ? “እጄ ላይ ነዋ” ትለኝም ይሆናል፡፡ ግን አይደለም። ሰዎች ለምን ፓራላይዝ የሚሆኑ ይመስልሃል? በብዛት የሚታወቀው ምክንያት ከአእምሯቸው ጋር የተገናኘ ነው፡፡ የአእምሯቸው (ወይም የህብለሰረሰራቸው) የሆነ ክፍል ላይ እክል የገጠማቸው ሰዎች ከአካል ክፍላቸው አንዱ ይደነዝዛል ወይም ፓራላይዝ ይሆናል፡፡ እጁ ፓራላይዝ የሆነ ሰው ላይም የፈላ ውሃ ብታፈስበት አያቃጥለውም። ምክንያቱም የማቃጠል ስሜት ያለው በአእምሮ ውስጥ እንጂ፣ በእጁ ላይ ወይም በሻዩ ላይ አይደለም፡፡ ጣዕምም፣ ድምጽም፣ ቀለማትም ሁሉም በአእምሮ ውስጥ ያሉና አእምሮ የእውኑን ዓለም ለመረዳት የሚጠቀምባቸው መንገዶች ናቸው፡፡

@Zephilosophy
@Zephilosophy
5.1K views20:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-19 10:22:29 እብዱ ዮሐና
ከካህሊል ጂብራን እጅግ ተወዳጅ ከሆኑ ስራዎች ውስጥ አንዱ ነው
Credit to ትረካ ቲዩብ

መልካም ሰንበት
@zephilosophy
5.6K viewsedited  07:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-18 23:04:26 የኦሾ አስገራሚ የልጅነት ታሪኮች
ተራኪ - ግሩም ተበጀ
@Zephilosophy
6.1K viewsedited  20:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-17 20:44:38 -ዛሬም የሚያስፈልጉን ነፃነቶች
-ቁልፍ እና ድልድይ
-ውይ ሴቶች!!
ተራኪ-አንዱአለም ተሰፋዬ
@Zephilosophy
@Zephilosophy
6.9K viewsedited  17:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-17 19:48:50 ተመስጦ ወይስ እብደት
ኦሾ
@zephilosphy
6.7K viewsedited  16:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-16 23:25:52 #ሰውና_ተፈጥሮው
አዲስ መጽሐፍ

5ት ድንቅ ትምህርቶችን እነሆ ለቅምሻ፦

The Laws of Human Nature የተሰኘው የሮበርት ግሪን ድንቅ መጽሐፍ #ሰውና_ተፈጥሮው በሚል ርእስ በቅርብ ቀን በገበያ ላይ ዋለ ።

ታዋቂውን 48 Laws of POWER የተሰኘውን መጽሐፍ 48ቱ የኃያልነት ሕጎችን በሚል በተረጎመችው #ሃኒም_ኤልያስ የተተረጎመ ሲሆን፣ ልክ እንደ #የኃያልነት_ሕጎች_መጽሐፍ ጥፍጥ ብሎ ከተዘጋጀው #ሰውና_ተፈጥሮው አዲስ መጽሐፍ ላይ ለቅምሻ 5ቱን ድንቅ ትምህርቶች እነሆ ብለናል፦


#አንድ
#መርዛማ_ሰዎችን_አስወግድ

ከመርዛማ ሰዎች ጋር አብዝተን የምንገናኝ ከሆነ በአካልም ሆነ በአእምሮ ሊጎዱን ይችላሉ ይለናል። እነዚህ ከልክ ያለፈ ትችት የሚሰጡ፣ ምቀኛ፣ ትዕቢተኛ፣ ጠበኛ ወይም ራስ ወዳድ የሆኑ ሰዎችን ያጠቃልላል።  እነዚህን ባህሪያት በራሳችን እና በሌሎች እንዴት መለየት እንዳለብን እና ራሳችንን ከእነሱ እንዴት ማራቅ እንዳለብን ያስተምረናል።

#ሁለት
#ስሜታዊነትህን_ተቆጣጠር

ስሜታችን ምን ያህል በጥልቅ እንደሚገዛን እና ውሳኔዎቻችንን እና ድርጊቶቻችንን እንዴት እንደሚነካ አናውቅም። ምክንያታዊነትን በማዳበር እነዚህን ስሜታዊ ተፅእኖዎች እንዴት መቋቋም እንደምንችል ማወቅ የግድ ይለናል። እራሳችንን ጠንቅቆ ማወቅ፣ ስሜቶቻችንን ከሥሮቻቸው መፈተሽ፣ የምላሽ ጊዜያችንን ማዘግየት፣ የአስተሳሰብ እና የስሜታዊነት ሚዛንን ማግኘትን የመሳሰሉ ስልቶችንም ሮበርት ግሪን በመጽሐፉ ይጠቁመናል።

#ሶስት
#ከጓደኞችህ_ጋር_አብረህ_ወደ_ገደል_አትግባ

ከሌሎች ጋር ለመስማማትና ብቻችንን ላለመሆን ብለን የሌሎችን አስተያየት ወይም ግምት ከልክ በላይ እንዳንቀበል ያስጠነቅቀናል።  ይህ ግለሰባዊ አቅማችንን እንድናጣ እና ለቡድን አስተሳሰብ እንድንጋለጥ ሊያደርገን ይችላል።

#አራት
#ሳታቋርጥ_የተሻለ_ነገርን_ፈልግ

ባለን ነገር እንዳንረካ እና ሌላ ቦታ ያለን የበለጠ ደስታን የሚሰጥ ነገር እንድንፈልግ ይገፋናል። ከመጠን በላይ የሆነ ምሬትም ወደ ብስጭት፣ ጭንቀት፣ መሰላቸት ወይም ሱስ እንደሚመራን፣ ከዚህ ይልቅም እስካሁን ያገኘነውን በምስጋና ተቀብለን፣  ራሳችንን በማሻሻል ላይ ማተኮር እንዳለብን ያሳየናል።

#አምስት
#በሰዎች_ጭምብል_ስር_ምን_እንዳለ_ተመልከት

ሮበርት ግሪን፣ ሰዎች ብዙውን ጊዜ እውነተኛ ሀሳባቸውን እና ስሜታቸውን ከራስ መተማመናቸውና ከአካላዊ ውበታቸው ስር  እንዴት እንደሚደብቁ ያሳየናል።  በሌሎች ቃላት እና ድርጊቶች ውስጥ ያሉ የማታለል ምልክቶችን እንዴት መለየት እንደሚቻል ያብራራልናል። እንዲሁም በሰዎች ፊት ሀቀኝነታችንን እና ታማኝነታችንን ሳናጣ እንዴት መጫወት እንዳለብንም ያስረዳናል።

#ሰውና_ተፈጥሮው መጽሐፍ በቅርብ ቀን በገበያ ላይ ይውላል።

ሌሎች የሮበርት ግሪን ምርጥ የእንግሊዝኛ መጽሐፍት እጅግ በጥራት ታትመው በገበያ ላይ፦

#The_Laws_of_Human_Nature


@Zephilosophy
@Zephilosophy
6.1K views20:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-08 23:21:21 እሳት፣ ውሀ፣ አየር እና መሬት
The fourth element

እሳት

እሳተ ሥሪቱ ፍጹም የእንከንየለሽነት፣ የምኅረትየለሽነት መሆኑ እሙን ነው፡፡ የእሳትንም ያህል ፍጹም ቅን፣ ገር እና በስነተፈጥሮው ቀጥተኛ ነገር መኖሩን አላውቅም፡፡ እሳት ከብሉያት፣ ነብያት፣ ወንጌላዊያን፣ ከአፈታሪኮች እና ባለቅንያት ዘመን ጀምሮ ብዙ የተባለለት መለኮት አከል ረቂቅ ክንውን ሆነ፡፡
የሰው ልጅ ከተሰራባቸው አራቱ የስጋ ባህሪያት ውስጥ ምናልባት ከአየርም በላይ እጅግ ረቂቁ ይኸው እሳት ሳይሆን አይቀርም፡፡ እሳት ሲፈጅ፣ ሲበላ እንጂ ሲያርፍ ማደሪያው የት፣ ሲግለበለብ መከሰቻው ከወዴት እንደሆንስ ስንኳ የሚያውቅም የለም፡፡ እሳት የነካውን ሁሉ የሚያነጻ (purifying) ወይም የሚያገረጣ (terrifying) አቅም አለው፡፡ ቁም ነገሩ ለየትኛው አሰልጥነነዋል የሚለው ብቻ ነው፡፡

እሳት ንጹህ ነው፡፡ ቅን ነው፡፡ ገር ነው፡፡ ግን ደግሞ አውዳሚ፣ ጨራሽ፣ ፈጅ፣ ቀሳፊ፣ ቁጡም ነው፡፡ የዚህ ረቂቅ የነበልባል ፍጥረት ጥሪ እና ምሪት ሰብዓዊነትን ማበልጸግ መሆኑ ጥንት ከአፈታሪክ፣ ከነፕሮሚተስ ዘመን ጀምሮ ይታወቃል፡፡ ሁላችንም ውስጥ ስንረሳው እንደ ዶርማንት ቮልካኖ, ወይ በተኛበት ሳር እንደሚበቅልበት ዘንዶ ሊያንቃላፋበጎሬያችን ተወሽቀን እንድናጎላጅ ሊያሰንፈን፣ ስናነቃው ግን ከራሳችን አልፎ ለዓለሙ በሙሉ ሲትረፈረፍ የሚያስችል እሳታዊ ኃይል በውስጣችን አሸልቧል፡፡ የረቂቁ መንፈሳዊ ሽግግር ጠበብት አልኬሚስቶች የሰው ልጅን እሳታዊ ባህሪይ ራስን ከመግዛትና ለራስ ከሚሰጥ ዋጋ ጋር ያይዙታል፡፡

የእሳት ገዥ ሥነ ባህሪ (fire dominant form of energy) ያላቸው ግለሰቦች ለሚከውኑት ማንኛውም ተግባር ጥልቅ ፍቅር (passion) ይኖራቸዋል፡፡ የኃይል ባለቤቶችና እና አንደተ ርቱዓን ናቸው፡፡ ሆኖም የሚንቀለቀል ነበልባላዊ ፍላጎታቸውንና ጉልበታቸው በጊዜ መግራት ካልቻሉ ደፋርነታቸው፣ እንግዳነታቸው እንደ ብልግና (arrogancy) ሊቆጠርባቸው ይችላል፡፡


ውኃ

ውኃ  ሕይወት ነው፡፡ ንቅናቄ (movement) ፍሰት፣ ደግሞ ይሄን የሕይወትነት ጸጋውን ያድስለታል፡፡ የወንዝ ውኃ ከኩሬ መብለጡ ንቅናቄ ሕይወት ቢሆን አይደለምን? ውኃ ያድሳል፤ ያነጻል፤ ይፈውሳል፤ ያሻግራል፡፡ ግን ደግሞ ይሸረሽራል፤ ይበረብራል፤ አለት ይሰባብራል፡፡ ቅርጸ ተለዋጭነቱም (በጠጣር፣ በፈሳሽና በትነት መልክ መከሰት መቻሉ) ተሻግሮ አሻጋሪነቱን ይገለጣል፡፡ አካላችን የሚያድሰው ዋነኛው ኃይል እሱ ነው፡፡
አፍሪካዊው እና መላው ጥንታዊ ሕዝቦች የውኃ አካላት፣ ሐይቆች፣ ወንዞች፣ ኩሬዎች እና ባህራት የመናፍስት ማደሪያ እንደሆኑ ያምናሉ፡፡ ለጥንታዊ ሕዝቦች ውኃ በስነተፈጥሮው ቅዱስ ነው፡፡
የውኃ ገዥ (Dominant) ሥነ ባህሪይ ያላቸው ሰዎች የተረጋጉ፣ ጸጥተኞች፣ በሰከነ ከባቢ ሳይቀር ገለል ማለትን የሚመርጡ ቁጥቦች ናቸው፡፡ በተጨማሪም ብልሆች፣ ጥልቆች፣ ረቂቆች፣ በራስ መተማመን ያላቸው፣ ፈተናን መቋቋም የሚችሉ ይሆናሉ፡፡


መሬት

መሬት ከአራቱ የአካል ባህሪያተ በላይ የመስከን፣ የመርጋት፣ ስር የመያዝ ምልክትነት አለው፡፡ የመሬት መሪ ሥነ ባህሪ ያላቸው ሰዎች መጋቢ (በመንፈስ፣ በደመነፍስ)፣ አበልጻጊ፣ ተንከባካቢዎች፣ ታማኞች፣ ቅኖች፣ ጽኑዎች ናቸው፡፡ ጥንታዊ ሕዝቦች ሁሉ ነገራቸው ከመሬት ጋር የተሳሰረ ነው፡፡ ቢዘሩ፣ ቢለቅሙ፣ ቢያድኑ፣ ቢቆፍሩ፣ ቢተከሉ... ከመሬት!


አየር

አየር ከደመነፍስ፣ ከመንፈስ (spirit) ጋር የተያያዘ ስነ ባህሪ ነው፡፡ ለሥነ-ሕይወት መፈጠርና መቀጠል ወሳኝ ግብዓት ነው፡፡ ረቂቅ ስለሆነ አይያዝ፣ አይታይ፣ አይጨበጥም፡፡ ሆኖም በዙሪያ ገባው ላይ በሚፈጥረው ተሻጋሪ ተጽዕኖ በቀላሉ እንረዳዋለን፡፡ ረቂቅ ቢሆንም ቅሉ እንደአንዳች፣ ወይ እንደ ጠባቂ መልአክ ዘወትር አጠገባችን መሆኑን በውል እንገነዘባለን፡፡ እንደ እሳት እና ውኃ ሁሉ የለውጥ አቀጣጣይ (catalyst)፣ እንደ ውኃ ሰጋር (ተንቀሳቃሽ) ባህሪይነት አለው፡፡
የአየር ገዥ (Dominant) ሥነ ባህሪ ያላቸው ሰዎች ቅን፣ ቻይ፣ ሰዎችን መመዘን የማይወዱ ነጻ ሰዎች ናቸው፡፡ በተጨማሪም አየር የዕውቀት የመብቃት ሥነ ባህሪ ነው፡፡


መፅሀፍ -በፍም እሳት መቃመስ
ደራሲ- ያዕቆብ ብርሀኑ
@Zephilosophy
6.5K viewsedited  20:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ