Get Mystery Box with random crypto!

ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ Philosophy

የቴሌግራም ቻናል አርማ zephilosophy — ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ Philosophy
የሰርጥ አድራሻ: @zephilosophy
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.37K
የሰርጥ መግለጫ

ፍልስፍና  እውነትን በመፈለግ- ሀሳዊ እምነቶችን በማጋለጥ እና ጭፍን አመለካከቶችን በጥበብ በመመርመር ወደ ላቀ አሰተሳሰብ ያሻግራል።
በዚህ ቻናል አለም ላይ ያሉ ፍልስፍናዎች ፤ ርዕዮት አለሞች ፤  ሀይሞኖቶች እና አስተሳሰቦች በነፃነት ይዳሰሳሉ።

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2024-05-08 22:33:53 በፍም እሳት መቃመስ
በያዕቆብ ብርሀኑ

ተፈጥሮ ህብሯ፣ መገለጫ መልኳ (manifestation) እልፍ ነው፡፡ ውሉን ካገኘኸው፣ ከውሻ ጩኸት፣ ከውኃ እናት እንቅስቃሴ ትማራለህ፡፡ ከቴሌስኮፕና ማይክሮስኮፕ በላይ ደመነፍስህን ታምነዋለህ፡፡ የተፈጥሮን ውል ካገኘኸው ስለሁሉም ነገር ለመማር ዓይኖችህን መጨፈን ብቻ እንደሚበቃህ ይገባሃል፡፡ ዝም ረቂቅ ጸሎት፣ ዝም በመንፈስ መገናኘት እንደሆነ ይገለጥልሃል፡፡ ረቂቁ ነገር ያለው ያልተጻፈው፣ ያልተነገረው ፈጽሞ ሊጻፍ የማይችለው ውስጥ (in the inexplicable) መሆኑን ትቀበላለህ፡፡ ከቀኖና ይልቅ ኅሊና በላጭ መሆኑ ፍንትው ይልልሃል፡፡

ዝሙን መለማመድ፣ የተፈጥሮን ረቂቅ ውል ማሰስ ረቂቅ መንፈሳዊ ፍለጋ (mysticism) ነው፡፡ ሚስቲሲዝምን ከምሥራቁ ዓለም የሐይማኖት እና አስተሳሰብ ጽንፍ ጋር ብቻ አያይዘው የሚያስቡ ሰዎች ያስቁኛል፡፡ አፍሪካዊ የቮዶ (vodooo) አማኞችን ጠይቋቸው.. ‹‹ነጮች ወደ ቤተክስትያን ሄደው ተሰባስበው ስለመለኮት ይጮሃሉ፡፡ እኛ ግን እንዲሁ በመደነስ ብቻ መለኮታዊያን እንሆናለን›› ይሏችኋል፡፡ (The white poeple go to church and speak about God, but we simply dance and become God.)

ሚስቲዚም የትም አለ፡፡ ስህተተኛው ታናሽ ወንድማችን የሚሉትን ዘመናዊውን የሰው ልጅ ሽሽት በኮሎምቢያ አይደፈሬ የተራራ ሰንሰለቶች የሚኖሩት የኮጊ (Kogi) ጥንታዊ ቅዱስ ሕዝቦችም አኗኗርም ሆነ በእናትህ ዓይኔ ተርገበገበ ማንን ሊያሳየኝ ይሆን? ብሂል ውስጥ ሚስቲሲዝም አለ፡፡ አያቶችህ ወፍ መለሰችኝ፤ ‹ስቅ አለኝ ማን አነሳኝ፤ እጄን አሳከከኝ ምን ላገኝ ይሆን?› ሲሉ ምን ማድረጋቸው መሰለህ? በስግብግቡ የሰው ልጅ አእምሮ ምሪት በምክንያታዊነት ከማይደረስበት ከረቂቁ ተፈጥሮ ጋር ሲመሳጠሩ እኮ ነው!

ቢሆንም ዝሙን ጭጩን በምልዓት ለመዋረስ የተዘጋጀን ስላለመሆናች (since we are incapable of being_silent) ከማይነገረው ከዝምታው ጥልቅ ጥቂት ሀቲቶችን ለማፍካት መውተፍተፋችን ጤንነት እንደሆነ ተቀብለን እንቀጥላለን...

መጽሐፈ ሥነ ፍጥረት ‹‹እሁድ በመጀመሪያው ሰዓተ ሌሊት ፬ቱን ባህሪያት ውኃ፣ መሬት፣ አየር፣ እሳት) ካለመኖር (እምኅበ አልቦ ሀበቦ) ሰራቸው ይለናል፡፡ እነዚህ የሰው ልጅ አካል የተቀመረባቸው አራት የስጋ ወይም የአካል ባህሪያት እሳት፣ ውኃ፣ መሬት እና አየር የረቂቁ የአልኬሚ ጽንሰ ሀሳብም መሰረታዊ ትዕምርቶች (symbols) መሆናቸውን ልብ ማለት ያሻል፡፡ ውኃ፣ እሳት፣ አየር፣ መሬት በየትኛውም የዓለም ክፍል፣ በየትኛውም ቋንቋ፣ ዘመን፣ መንገድ መንፈሳዊ ሐሰሳ የሚያደርጉ ‌መሰጠቱ ያላቸው ሁሉ የሚጨባበጡባቸው ስጋችን የታነጻባቸው ባህሪያት ስለመሆናቸው በብዙ ታትቷል፡፡

ረቂቃዊያን (mystics) ደግሞ መቃተት፣ መቃበዛቸው የቱንም ያህል ሰርቦላ ቢሆን ዞሮ ዞሮ ያው ስሪታቸው የወል (communal) የውኃ፣ አየር፣ የመሬት እና የእሳት ነው... ሕልማቸውም ልዩነት የለውም፡፡ በየትኛውም መንገድ ያምልኩ ያመስግኑ ዞሮ ዞሮ ራስን ማብቃት፣ የሰውን መለኮታዊ ማንነት ማንቃት፣ የሰውን ልጅ ከራሱ ደመነፍሳዊ እስራት ነጻ ማውጣት፣ ከስሜት - ከስግብግብነት አዙሪት መንጻት ዓይነት...
ሣይንስ በደረሰበት ሰዋዊ አረዳድ መሰረት በማናቸውም ቦታ ሕይወት ይፈጠር ዘንድ እነዚህ አራቱ የስጋ ባህሪያት የግድ ያስፈልጋሉ፡፡ ሆኖም የተሰራንባቸው አራቱ አካለ ባህሪያት መግነጢሳዊ ኃይለ መልኮች (form of energies) እንጂ አንዲያው በሌጣው የሚፈከሩ ቁሳዊ ኢንቲቲስ› አይደሉም፡፡ እነዚህን አራት ስነባህሪያት በቅጡ በማጥናትና በማሰልጠን በእያንዳንዱ ሰው ውስጥ ያንቀላፋውን ጉልበት ማንቃት እና የሰውን ልጅ ወደ ቀደመ መለኮታዊ ማንነቱ መመለስ ይቻላል፡፡

@Zephilosophy
@Zephilosophy
5.3K views19:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-06 20:13:06 የፓርክ ፖለቲካ

በረከት በላይነህ በደጃፍ ቲቪ ከዳዊት ጋር ድንቅ ውይይት አድርጓል።

17 % የኢትዮጲያ ጠቃሚ መሬት በፓርክ ምክንያት ታጥሯል ።ባቢሌ እና ጭላሎ በመሰሉ ፓርኮች ለ13 ቀይ ቀበሮ እና ለአስራ ሁለት ዝሆን ብዙ ሚሊዮን ህዝብ መመገብ የሚችል ብዙ ሺህ ሄክታር መሬት ታጥሮ ተቀምጧል ይላል። አድምጡትና ሀሳብ ስጡበት

@Zephilosophy
6.1K viewsedited  17:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-03 14:02:41 አለ ክፍት ቦታ
ገጣሚ- ኤፍሬም ስዩም
@zephilosophy
6.1K views11:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-03 14:02:22 ግርባብ
ፍቃዱ አየለኝ
ተራኪ - ኤፍሬም ስዩም
@zephilosophy
5.5K views11:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-26 23:11:58 ራስን ማታለል (Bad Faith)

በሕይወትህ ለምን ያህል ጊዜ ለውድቀትህ ሌሎች ሰዎችን ወይም ሁነቶችን ወቅሰህ ታውቃለህ? እንዲህ ባይሆን ኖሮ እንዲህ እሆን ነበር' ብለህስ ታውቃለህ? አለቃህ፣ መምህራኖችህ፣ ወላጆችህ የሆነ ነገር እንድታደርግ አስገድደውህ ያውቃሉ?

የሃያኛው ክ/ዘመን ፈላስፋ የሆነው ዣን ፖል ሳርት እነዚህን ሃሳቦች በአንድ ሰብስቦ “bad faith' ብሎ ይጠራቸዋል። ይህም ራስን ማታለልን ያመላክታል። ብዙውን ጊዜ በሕይወት ላይ አማራጭ እንደሌለን ለራሳችን እናሳምነዋለን፡፡ ይህን ያደርግነው እንዲህ ስለሆነ ነው የሚል ምክንያትም ከድርጊቶቻችን ጀርባ እናስቀምጣለን። አሁን ላለንበት ደረጃ ያበቁንን አስገዳጅ ምክንያቶች እና ሰበቦች እንደረድራለን፡፡ ራስን ማታለል በዙሪያችን እስር ቤት የመገንባት ያህል ነው።

ማህበረሰቡ ባስቀመጠልን አስገዳጅ ህጎች አልያም ልማዶች ራሳችንን ወስነን በነጻነት ከመምረጥ እንገደባለን፡፡ ለምሳሌ ሜሴጅ እንደላከልሽ ወዲያውኑ አትመልሽለት” አይነት ተራ ሕጎች ጀምሮ እስከ በዳኛ የተደነገጉ ሕጎች ድረስ - የመምረጥ ነጻነታችን ይገደባል።

እናም ራስን ማታለል (bad faith) የሚጀምረው ለውድቀታችን እነዚህን ህጎች ተጠያቂ ስናደርግና በእነርሱ ውስጥ ስንሸሸግ ነው::

እናም ከማህበረሰቡ ተውስን የምንወስዳቸው ብዙ ጭንብሎች አሉን፡፡ በብዙ የሕይወት ክፍሎቻችን ላይ እንዲህ መሆን አለብህ ስለተባልን ልክ እንደ ተዋናይ ሆነን እንተውናለን፡፡
ነገር ግን ይለናል ሳርት፤ ህግ፣ ደንብ፣ ባህል እና ወዘተ... ከመምረጥ አያግዱንም፡፡ ምርጫዎችን የመምረጥ እና የመወሰን ፈቃዱም በእኛ እጅ ላይ ነው ያለው፡፡

በእያንዳንዷ ቅጽበት፣ በእያንዳንዱ ቀን ምርጫዎች አሉን። በእያንዳንዱ ሰከንድም የወደድነውን የመምረጥ ነጻነት አለን። ይህንን ነፃነት ምንም አይነት ነገር ከእኛ ሊቀማን አይችልም፡፡ ነጻ ለመሆንም የተገባን ነን።

በዚሁ ልክም ለእያንዳንዱ ምርጫዎቻችን ውጤት የምንጠየቀው እኛ ብቻ ነን። ቀድሞውኑ በሚገባ አመዛዝነን ካልወሰንን እና መንገዳችን ወደ መጥፎ መዳረሻ ካደረሰን፣ ከእኛ ውጪ ልንከሰው የሚገባ አካል አይኖርም፡፡ ጥፋታችንንም ከማመን ውጪ ማንም ላይ ማላከክ የለብንም፡፡

ነጻ ነህ ... ነጻነትህን ተጠቅመህ መንገድህን ምረጥ...

ምንጭ-ፍልስፍና ከዘርዓ ያዕቆብ እስከ ሶቅራጠስ
ዝግጅት-ፍሉይ አለም

@Zephilosophy
@Zephilosophy
9.2K views20:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-26 08:08:45 ጭፍን እምነትን አውልቃችሁ ጣሉ

ምንጭ ፦ የፍልስፍና ሀሁ
ፀሀፊ ፦ በላይ ደስታ

መሪር ሀሳቦችን ለማንሳትና ለመወያየት ካልደፈራችሁ? ሗላ ቀር የሆነውና ከቤተሰቦቻችን የወረስናቸው ልማዶችና አስተሳሰቦች እርስ በእርስ አባልተው ይጨርሱናል፡፡ ስለእውነት ነው የምላችሁ፣ እንደሰው ተፈጥረን እንደድመት የምናልፍ ከንቱዎች እንሆናለን። በየጎጡ ጎራ እየሰራን እንለያያለን:: እምነታችን ሁሉንም የዓለም ህዝብ ካልቀየረ ብለን አክራሪነት ውስጥ ተቻኩለን እንወተፋለን። በንቁ ሀሳባችን ካልተመራን፣ ያው መሪያችን ልማድ ሆኖ መቅረቱ ግልጽ ነው፡፡

በሀሳብ፣ ልማድና እምነት መካከል ሰፊ ርቀት አለ፡፡ በሀሳቡ የሚያምን ሰው ይልቃል። በእምነቱ የሚያምን ግን አዲስ ሀሳብ አይፈጥርም፡፡ ቀድሞ የተፈጠረውን ስርዓት ተቀብሎ ወደ ልጁ ሰፈር ያደርሳል። እንደዱላ ቅብብል ማለት ነው። የዱላ ቅብብል ተወዳዳሪ ስለዱላው ምንም የሚያስበው የለም፡፡ ዱላው ብረት ይሆን እንጨት አያስብም። የሱ ስራ፣ ከኋለኛው አጋሩ የተቀበለውን ዱላ ይዞ ወደ ፊት መሸምጠጥ ብቻ ነው። ከዚያ ከፊቱ ለሚጠብቀው ሯጭ እስኪያቀብል ሳያባራ ይሮጣል፡፡

በእምነትና በባህላዊ ስርዓት ውስጥ የሚኖሩ ህዝቦችም እንዲሁ ናቸው። ከአባቶች የወረሱትን እምነትና ትዉፊት የሙጥኝ ብለው ወደፊት ይሮጣሉ። ለቀጣዩ ትዉልድ እስኪያስረክቡና ህይወታቸው እስኪያልፍ የሚያስቡት አዲስ መንገድ አይኖርም፡፡ አእምሯቸው በጥልቀት እንዲያስብ ፈቃድ አይሰጡትም፡፡ ለዚህ ነው፣ ብዙ እምነት ውስጥ የሚኖሩ ህዝቦች ስልጣኔን የሚሸሹት።

እምነትን ብቻ የሁሉ ነገር ምንጭና መንገድ አድርጎ የሚቆጥር ህዝብ ያየለበት ማህበረሰብ ወይም ሀገር፣ ኋላቀርነቱ እዚያው ኋላ እንደቀረ የሚኖር ይሆናል። ትልቁ ፈተና ደግሞ፣ እምነት ውስጥ የተኛ ህዝብ ኋላ ቀርነቱን እንደጸጋ ማየቱ ነው፡፡ የትኛውም የኑሮ ገጠመኝ ማለትም ድህነት፣ አለመማር፣ አለማወቅ፣ የበታች መሆን፣ ስደት፣ በሽታ፣ ጦርነትና መሰል እልፍ ወረርሽኞች እግር ተወርች አስረውት ጭምር አያዝንም፡፡ እልህ ውስጥ አይገባም፡፡ ለምን እንዲህ ተፈተንኩ ማለትን አይፈልግም፡፡

"የፈጣሪ ፈቃድ ነው ብለን ዝም አልን” በሚል የተለመደ ዋሻ ውስጥ ይደበቃል፡፡ ይህን ለማረጋገጥ፣ ዛሬም ወደ ራሳችን ማየት ነው፡፡ እየወደቅንም ፈጣሪ የምንለውን ሀይል አመስጋኞች ነን። ብንራብ፣ ብንጠማ፣ ፈተናዎች ቢደራረቡብን፤ ጦርነት ውስጥ ብንናጥ ሁሌ እያመሰገንን እናልፋለን፡፡ ለምን በዚህ ሁኔታ ውስጥ ገባን? እንዴትስ መውጣት እንችላለን? ብለን አንጠይቅም። ምክንያቱም "ሁሉም ነገር የፈጣሪ ፈቃድ ነው” በሚለው ራሳችንን እናታልላለንና።

መፍትሔ የምንጠብቀው ከጸሎትና ከፈጣሪ ነው። እጆቻችንን ወደ መሬት አዙረን መዶሻና አካፋ አንይዝም፡፡ ምንም ሳንይዝ አየሩ ላይ ወደ ሰማይ አንጋጠን እንለምናለን። በዛ ጥፋታችን ለፈረሰ ቤት ጥገና የምንጠይቀው ፈጣሪን ነው:: ይህ መንገድ ለሁሉም ነገር መፍትሄ አይሆንም፡፡

ፍጹም አማኝ ሆኖ የተሰባሰበ ህዝብ ስልጣኔ የማይሰራው ለምን እንደሆነ ግልጽ ነው። የተሰባሰበው ሰማያዊ መንግስትን እያሰበ እንጂ፣ በእጁ የጨበጠውን የምድር ህይወት ከግምት አያስገባም፡፡ እየኖረ በመሆኑ ግን፣ የግድ መንግስት ይፈጥራል። የሚፈጥረው የመንግስት አይነት ግን ምድር ላይ ያለውን እውነት ያማከለ አይሆንም፡፡ የተዘበራረቁ መልኮች ይኖሩታል፡፡

የራሱን የህይወት መንገድ እንዲፈጥር ነጻነትን ያልተማረ ህዝብ፣ ጥያቄ አይጠይቅም፤ የተለየ ሀሳብም አያስብም፡፡ ሀሳብ የሚያድገው ደግሞ በፍልስፍና ነው ! በፍልስፍና አስተሳሰብ ያልተገራ ህዝብ በነጻነት ውስጥ ሆኖ የእውቀት ልዩነት የሚፈጥር የሀገር ቅርጽ አይወልድም፡፡ በጥንት ልማድና አሁን ባለው የሀገር ቅርጽ መሃል የተለየ ማንነት አይኖርም።

በልማድና በእምነት ውስጥ ብቻ የሚኖር ህዝብ አንደኛው ችግር ይኼው ነው፡፡ ከዘመን መለወጥ ጋር የሚያድግ ርዕዮት አይፈጥርም፡፡ የእርሱ ጉዳይ ዶግማዎችን እንዳሉ ማስቀጠል ነው፡፡ የባህል ዱላ ቅብብል ላይ የተገደበ ስርዓት ነው የሚፈጥረው፡፡ ባህል ግን ብቻውን ስልጣኔ አይሆንም ፤ ስልጣኔንም አያመጣም፡፡ ባህል የቡድን ባህሪ እንጅ የግለሰብ አስተሳሰብ አይደለም፡፡ የሳይንስ ወይም የፍልስፍና ተግባር ደግሞ ዶግማዎችን ብቻ ማስቀጠል አይደለም።

ኢትዮጵያ ዘመናትን ያስቆጠሩ ሥነቃላዊና የፅሁፍ ፍልስፍናዎች ባለቤት ናት። ከአስራ ሰባተኛው መቶ ክፍለ ዘመን በፊት፣ ከሌሎች የአፍሪካ ሀገሮች በተለየ መልኩ በርከት ያሉ የፍልስፍና ስራዎችን በመስራት በቀዳሚነት የምትጠቀሰው በጥንታዊው የግእዝ ቋንቋ ከተጻፉት የፍልስፍና ስራዎቿ መካከል ከፊሎቹን በትውልድ ካናዳዊ፣ በምርጫ ደግሞ ኢትዮጵያዊ የሆነው ፕሮፌሰር ክላውድ ሰምነር ወደ እንግሊዝኛ ቋንቋ በመተርጎም፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ እንዲታወቁ እድርጓል። ሌሎች በርካታ በግዕዝና በአረብኛ ቋንቋዎች የተፃፋ የጽሁፍ ስራዎች በጥንታዊ ቤተእምነቶችና ቤተመዛግብት ውስጥ ተቀምጦ አንስቶ የሚመረምራቸውን የሀገራቸውን ጠቢብ በመጠባበቅ ላይ ናቸው።

ፍልስፍና በጥቅሉ የተጻፉትንና በቃል ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚተላለፋትን የማህበረሰብ ወጎች፣ ልማዶች፣ ጥበቦች፣ የእውቀት ዘርፎችንና አስተሳሰቦችን፤ በግለሰብ ፈላስፋዎች፣ በአንድ ዘመን ተሰርተው በጽሁፍ የተላለፉትን ስራዎች የሚመለከት ምጡቅ የጥበብ ዘርፍ ነው። በቃል ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚተላለፉ ማኅበረሰባዊ ፍልስፍናዎች፤ በተረትና ምሳሌ፣ በምሳሌያዊ አነጋገሮች፣ በዘይቤዎች፣ በቅኔዎችና በወጎች ሊገለጡ ይችላሉ።

ሀገራችን ኢትዮጵያ፣ ገና ያልተጠኑ የበርካታ ጥንታዊ ስነ ጽሁፎች ባለቤት ናት፤ ማጥናትና መመርመር አቅቶን ሌሎች አጥንተው የቅጂ መብቱን ከመውሰዳቸውና የታሪክ ክፍትት ተፈጥሮ በመጪው ትውልድ ተወቃሾች ከመሆናችን ሰፊት፣ ከትምህርት ቤት ጀምሮ፣ በወጣቶች አዕምሮ ውስጥ የምርምር ሀሳቦችን በማንሳትና የዘርፉ ምሁራንም ተገቢውን ጥናትና ምርምር በማካሄድ፣ በየደረጃው ያሉ የትምህርት ተቋማትም፣ የፍልስፍና ጥበብን በትምህርትና በምርምር ስራቸው ውስጥ በማስገባት፣ ወጣቶች ከተለመደው አስተሳሰብ ወጥተው፣ በተለያዩ የፈጠራ አስተሳሰቦች ውስጥ እንዲመሰጡ ማበረታት ወቅቱ የሚጠይቀው አቢይ ስራ ነው፡፡

እየኖርን ባለነውም ሆነ ወደፊት በምንኖረው ዘመን፣ ለአንድ ሃገር አስፈላጊና ወሳኝ ነገሮች ናቸው ተብለው ከሚታመንባቸው ጉዳዮች መካከል፤ ለዘመኑ የሚመጥን የሳይንስ፣ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ውጤት ሊያመነጭ የሚችል ተመራማሪ ትውልድ ማፍራት መቻል ነው፡፡ አዳዲስ የሳይንስ ግኝቶችንና የተራቀቁ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን ሊያመነጩ የሚችሉ ጠይቂ አዕምሮዎች እንዲፈጠሩ ደግሞ፣ በነባሩ ባህላዊ አስተሳሰብ ውስጥ ያሉ ዜጎች፣ አዲሱ ትውልድ፣ የምርምር ሀሳቡን በሚያምንበት መንገድ ያለገደብ፣ እንዲያራምድና እንዲያዳብር መፍቀድ መቻል አለባቸው።

@Zephilosophy
@Zephilosophy
7.6K views05:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-25 09:20:11 #ጊዜ_አባካኞች

“በታሪክ ያሉ የምጡቅ አእምሮ ባለቤቶች ሁሉ በዚህ ነጠላ ጭብጥ ላይ ትኩረት ቢያደርጉ፣ የሰው ልጆች አእምሮ ድብቅነት ውስጥ ግራ መጋባታቸውን በጭራሽ ሊገልጹ አይችሉም፡፡ አንድም ሰው ከራሱ ግዛት አንድ ኢንች አይተውም፤ ከጎረቤት ጋር ያለ ትንሽ ግጭት በከባድ የሚያስከፍል ሆኗል፤ ሆኖም በሕይወታችን ውስጥ ሌሎች ጣልቃ እንዲገቡ በቀላሉ እንፈቅዳለን፤ የከፋው ነገር ደግሞ በአብዛኛው ሊያጠፉት ለሚችሉት ሰዎች መንገድ የምናመቻች መሆናችን ነው፡፡ ማንም ሰው ለአላፊ አግዳሚው ገንዘቡን አይሰጥም፤ ግን እያንዳንዳችን ለምን ያህል ሰዎች ሕይወታችንን ሰጥተናል! ለንብረትና ለገንዘብ እጃችን አይፈታም፤ ሁላችንም እጅግ ስስታሞች መሆን ለሚገባን ለሚባክን ጊዜ ግን የምናስበው እጅግ ትንሽ ነው፡፡”
                   #ሴኔካ

በአሁኑ ጊዜ ማለቂያ የሌላቸው መበጥበጫዎች አሉ፤ የስልክ ጥሪዎች፣ ኢ-ሜይሎች፣ ጠያቂዎች፣ የማይጠበቁ ሁኔታዎች አሉ፡፡ በባርነት ውስጥ የተወለደውና ኋላ ላይ ራሱን አስተምሮ የግሉን ኮሌጅ እስከ መክፈት የደረሰው ኮሌ ቡከር ቲ. ዋሽንግተን፣

“ያለ ምንም አላማ የሰውን ጊዜ ሊጠቀሙ የተዘጋጁ ሰዎች ብዙ ናቸው፡፡” ብሎ ነበር፡፡

በሌላ በኩል ፈላስፎች፣ የእነሱ ነባሪ ሁኔታ ውስጣዊ እውቀት መሆን እንደሚገባው ያውቃሉ፡፡ ግላዊ ቦታዎቻቸውንና ሀሳቦቻቸውን ከዓለም ረብሻ  በትጋት የሚጠብቁት ለዚያ ነው፡፡ የጥቂት ደቂቃዎች ምልከታ ከየትኛውም ስብሰባ ወይም ሪፖርት የበለጠ ዋጋ እንዳለው ያውቃሉ፡፡ በተጨማሪም በሕይወት የተሰጠን ጊዜ ትንሽ እንደ ሆነና ምን ያህል ፈጥኖ ሊያልቅ እንደሚችልም ይረዳሉ፡፡

ሴኔካ አካላዊ ንብረቶቻችንን መጠበቅ ላይ ጥሩ የሆንነውን ያህል፣ አእምሯዊ ድንበሮቻችንን ማስመር ላይ ግን ግድ የለሽ መሆናችንን ያስታውሰናል፡፡ ማንምም እንዳሻው ድንበራችንን አልፎ ሲገባ አንቃወመውም። ንብረት ተመልሶ ሊገኝ ይችላል፤ እንዲያውም ገና ብዙ የምድር ሃብቶች በሰው አልተነኩም።

#ጊዜ_ግን? ጊዜ ፈጽሞ ሊተካ የማይችል ሀብታችን ነው፤ ተጨማሪ መግዛት አንችልም፡፡ ማድረግ የምንችለው በተቻለ መጠን ጥቂት ብቻ ለማባከን ጥረት ማድረግ ነው፡፡

@Zephilosophy
@Zephilosophy
6.2K views06:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-25 08:14:41 ሕይወት የምትጀምረው መቼ ነው?

ሁለት ሰዎች በአንድ ጉዳይ ላይ ይከራከሩ ነበር፡፡ አንዱ፣ “ሕይወት የምትጀምረው ልክ አንድ ጽንስ በተጸነሰበት ቅጽበት ነው” በማለት ያንን እምነቱን በግለት ያስተጋባል፡፡

ሌላኛው ደግሞ፣ “አይደለም! ሕይወት የምትጀምረው የተጸነሰው ልጅ የመጀመሪያውን ትንፋሽ ወደመተንፈስ ደረጃy ሲደርስ ነው” በማለት የተጋጋለ ምላሹን ይናገራል፡፡

ይህንን ሃሳብ ሳይለቁ ለሰዓታት ሲከራከሩ የተመለከተ አንድ ሰው እያዋዛ አንድን ትምህርት ትቶላቸው አለፈ፣ “ሁለታችሁም ተሳስታችኋል፤ ሕይወት የምትጀምረው ሰው የተፈጠረለትን ዓላማውን ሲያውቅና ያንን መከተል ሲጀምር ነው”!!!

ዓላማችንን እንወቅ! በግለት እንከታተለው! እንኑረው!

@zephilosophy
6.5K viewsedited  05:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-23 22:43:42 አጫጭር ውብ ትረካዎች
በአንዱለም ተስፋዬ

@zephilosophy
6.8K viewsedited  19:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-23 16:27:26 ስለመፅሐፍ የተነገሩ አባባሎች!


ወዳጆች ዛሬ የአለም የንባብ ቀን እንደመሆኑ የንባብ ባህላችን እንዲዳብር ሊያነሳሱን የሚችሉ ስለመፃሕፍት የተነገሩ የተለያዩ ሠዎችን አባባል ዛሬ ልንዘክር ብዕራችንን ከወረቀቱ አገናኝተናል፡፡

መፅሐፍ የሚሠጡት ጥቅም የታወቀ ቢሆንም በማንበብ ብቻ ግን አዋቂ መሆን አይቻልም ባይ ነኝ፡፡ ምክንያቱም መፃሕፍትን ከማንበብ ባሻገር በንባብ ያገኘናቸውን ሃሳቦች ከሃሳባችን ጋር በማስተያየትና በማሻሻል፣ በማሠላሠልና በማስተዋል አዲስ ሃሳብ ካልፈጠርንበት መፅሐፍ ማንበብ ሳይሆን መፅሐፍ መቁጠር ነው የሚሆነው፡፡ ባነበብነው ሃሳብ ተገዝተንና አዲስ የባህሪ ለውጥ ወይም አዲስ ነገር ካልፈጠርንበት ማንበባችን ዕውቀት አይሆንም፡፡ ምክንያቱም ዕውቀት ስንል በተጨባጭ በተግባር የሚገለፅ ነውና፡፡
ለማንኛውም አባባሎቹን እነሆ እላለሁ..! ሃሳብና አስተያየታችሁ የተጠበቀ ነው፡፡ መልካም ንባብ!

‹‹መፅሐፍ አንድ ቁምነገር አለው፡፡ ይሄም እግርህን ከቤትህ ሳታነሳ ዓለምን እንድትዞር ያደርግሃል›› (ጁምባ ራሂሪ)

‹‹አንባቢ ከመሞቱ በፊት አንድ ሺ ኑሮ ይኖራል፡፡›› (ጆርጅ ማርቲን)

‹‹መፅሐፍት ተንቀሳቃሽ አስማቶች ናቸው›› (ስቴፈን ኪንግ)

‹‹እንደ መፅሐፍ ያለ ታማኝ ጓደኛ የለም፡፡›› (ኸርነስት ኸርሚንግወይ)

‹‹ አንድ ነገር አንርሳ! አንድ መፅሐፍ፣ አንድ እስኪብርቶ፣ አንድ ሕፃን፣ አንድ መምህር ዓለምን መለወጥ ይችላሉ፡፡›› (ማላላ ዮሶፍዜ)

‹‹ዓለም መፅሐፍ ናት፡፡ ዓለምን ተጉዘው ያላዩ መፅሐፍ ይግለጡ፡፡›› (ቅዱስ አውግስጦስ)

‹‹መፅሐፍ በየዕለቱ የሚያጋጥመንን የህይወት ጉድፍ የሚያስወግድልን የነፍሳችን ማጠቢያ ነው፡፡›› (ያልታወቀ ሠው)

‹‹ማንበብ ለአዕምሮ ሲሆን አዕምሮም አካላችን ምን ማድረግ እንዳለበት ያቀናጃል›› (ያልታወቀ ሠው)

‹‹መፅሐፍ ከባድ መሆን አለበት፡፡ ምክንያቱም ዓለሙ ሁሉ በእርሱ ታጭቋልና፡፡›› (ኮሜሊያ ፈንክ)

‹‹ዛሬ አንባቢ የሆነ ነገ መሪ ይሆናል፡፡›› (ማርጋሬት ፉለር)

‹‹ዛሬ ልታነበው የምትችለውን መፅሐፍ ለነገ አታቆየው፡፡›› (ያልታወቀ ሠው)

‹‹ካነበብኩ መላው ዓለም ለእኔ ክፍት ነው፡፡›› (ሜሪ ማክሎድ ቤቱን)

‹‹አንዳንድ መፅሐፍት ነፃ ይተዉናል፡፡ አንዳንዶቹ ደግሞ ነፃ አድርገው ይሠሩናል፡፡›› (ራልፍ ዋልዶ ኤመርሠን)

‹‹መፅሐፍ ወደፊት ልንሆን የምንፈልገውን የያዘ ህልማችን ነው፡፡›› (ኔል ጌማን)

‹‹ቤተ-መፃሕፍቶች ልክ እንደጥሩ ትዝታ መዓዛቸው ያውደኛል፡፡›› (ጃኩሊን ውድሰን)

‹‹መፅሀፍ አስተሳሰባችንን የሚያቀጣጥል መሣሪያ ነው፡፡›› (አላን ቤኔት)

‹‹ሌላ ሠው ያነበበውን ብቻ እያነበብክ ከሆነ ሌላ ሠው የሚያስበውን ብቻ ነው እያሠብክ ያለኸው፡፡›› (ሐሩኪ ሙራካሚ)

‹‹ቤት ያለመፅሐፍት ማለት አካል ያለነፍስ ማለት ነው፡፡›› (ሲስሮ)

‹‹ተራ ሠዎች ትላልቅ ቲቪ አላቸው፡፡ ብልህ ሠዎች ግን ቤተመፃሕፍት አላቸው፡፡›› (ያልታወቀ ሠው)

"መፅሀፍ ማለት በኪሳችን ይዘነው የምንዞረው በመልካም ፍሬዎች የተሞላ እርሻ ነው።” ቻይናውያን

“መፅሀፍ ስናነብ ወደ ውስጣችን በጣም ጠልቀን በመግባት ስለራሳችን የበለጠ ብዙ ነገሮችን ማወቅ እንጀምራለን።”
ዊልያም ሀዝሊት


@Zephilosophy
@Zephilosophy
10.1K viewsedited  13:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ