Get Mystery Box with random crypto!

Natnael Mekonnen

የሰርጥ አድራሻ: @natnaelmekonnen21
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 175.28K
የሰርጥ መግለጫ

በቀጥታ መረጃዎችን ለመስጠት ሲፈልጉና ማስታወቂያ ማሰራት ከፈለጉ 👉 @NatnaelMekonnen7
Facebook.com/natnaelmekonnen.et
Instagram.com/natnaelmekonnen21

Ratings & Reviews

1.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2024-04-08 17:27:37
ክፍለጦሮች በአሸባሪው ኦነግ ሸኔ ላይ የሚወስዱትን እርምጃ አጠናክረው መቀጠላቸው ተገለፀ።

በምስራቅ ወለጋ ዞን በዲጋ ወረዳ የማዕከላዊ ዕዝ አንድ ክፍለጦር በአሸባሪው ኦነግ ሸኔ ላይ ሰሞኑን ባደረገው የተቀናጀ ኦፕሬሸን የሸኔ ቡድን መደምሰሱን የክፍለጦሩ አዛዥ ሌተናል ኮሎኔል ታደሰ እንዳለው ገልፀዋል።

የህዝብን ሠላም መንሳት አላማው አድርጎ የሚንቀሳቀሰው አሸባሪው ኦነግ ሸኔ በማህበረሰቡ ላይ የሚያደርሰውን ጥቃት ለማስቆምና ቡድኑን ሙሉ በሙሉ በማጥፋት የሃገሩን ሰላም ለማረጋገጥ ክፍለጦሩ ተልዕኮውን በድል አድራጊነት ቀጥሏል ሲሉ አዛዡ ተናግረዋል።

ክፍለጦሩ ሰሞኑን በጠላት ላይ በወሰደው እርምጃ የሽብር ቡድኑ ለጥፋት ተግባሩ ይጠቀምበት የነበረውን  ብሬን ፣ ክላሽ ፣ የክላሽ መጋዘን ፣የብሬን ጥይት ፣ ቦንብ፣ የክላሽ ጥይት ፣ሽጉጥና የተለያዩ መድሃኒቶችን በቁጥጥር ስር ማዋል መቻሉን ሌተናል ኮሎኔል ታደሰ እንዳለው አሳውቀዋል።

በተመሳሳይ በሆሮ ጉድሩ ወለጋ ዞን በሀባቦ ወረዳ እየተንቀሳቀሰ ህብረተሰቡን ለስቃይ እና ለእንግልት ሲዳርግ እንዲሁም መሰረተ ልማቶችን ሲዘርፍ እና ሲያቃጥል የቆየዉ አሸባሪዉ የሸኔ ቡድን ክፍለ ጦሩ በሚወስደው የተቀናጀ እርምጃ እጅ እየሠጠ ይገኛል።

እጃቸውን ለሰራዊቱ  ከሰጡት መካከል ለሊሳ ዋሚ ላለፉት አመታት በሽብር ቡድኑ በቆየሁበት ጊዜ ህብረተሰቡን በማሠቃየት በዘረፋ ላይ ተሰማርቸ ነበር ግን ትክክል አልነበርኩም አሁን ወደ ሠላም ተመልሻለሁ ብሏል።

የአካባቢዉ ነዋሪዎች የሽብር ቡድኑ አባላት በሰላማዊ መንገድ ለመከላከያ ሰራዊቱ እጅ መስጠታቸውን እንዲቀጥሉበትና በአካባቢውም የልማት ሥራ እንዲሠራ ሃሳብ ሰጥተዋል።
25.6K views14:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-06 17:18:29
ወጣት ሶፎኒያስ አስራትን ገድለው ተሽከርካሪውን ዘርፈው የተሰወሩ ማንነታቸው ያልታወቁ ወንጀል ፈፃሚዎችን በ48 ሰዓት ውስጥ ከዘረፉት ተሽከርካሪ ጋር በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡ ወንጀሉን የፈፀሙ አካላትን ለመቆጣጠር የምርመራና የክትትል ቡድኑ ሌት ከቀን በመስራት ውጤት ማምጣቱ ገልፆል፡፡

በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ልዩ ቦታው አሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ አካባቢ ወደ አቦ ቤተ-ክርስቲያን በሚወስደው መንገድ ላይ ወጣት ሶፎኒያስ አስራት ተገድሎ ይገኛል፡፡

የወጣቱ መገደል ሪፖርት የደረሰው አዲስ አበባ ፖሊስ የወንጀል ምርመራና የክትትል ቡድኖችን በማዋቀር የገዳዮቹን ማንነት በማወቅ ወንጀለኞቹን ህግ ፊት ለማቅረብ ወደ ስራ ይገባል፡፡
ሟች ወጣት ሶፎኒያስ መጋቢት 24 ቀን 2016 ዓ/ም ከንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 ናሆም ሆቴል አካባቢ ከሌሊቱ 8፡00 ሰዓት ላይ ማንነታቸው የማይታወቁ ሦስት ግለሰቦችን አሳፍሮ ወደ ቦሌ ሚካኤል ለማድርስ መሄዱን ጉዳዩን ለመከታተል የተቋቋመው የምርመራና የክትትል ቡድን አባላት ባደረጉት ክትትል ያረጋግጣሉ፡፡
ወንጀል ፈፃሚዎቹ ወንጀል ለመፈፀም አቅደው እና ተደራጅተው የትራንስፖርት አገልግሎት ፈላጊ መስለው ሹፌሩን በመቅረብ ከተሳፈሩ በኋላ አንገቱን በገመድ አንቀው በመግደል አስክሬኑን በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 አሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ አካባቢ ወደ አቦ ቤተክርስቲያን በሚወስደው መንገድ ላይ በመጣል አይነቷ ቪትዝ የሴሌዳ ቁጥር ኮድ 2A 93488 ተሽከርካሪ ጨምሮ ሁለት ሞባይል ስልኮችን ዘርፈው ይሰወራሉ፡፡

ፖሊስ ሌት ተቀን ባደረገው ብርቱ ክትትል ልዩ ልዩ ፖሊሳዊ ቴክኒኮችን በመጠቀም ወንጀል ፈፃሚዎቹ የሰረቁትን ተሽከርካሪ ለመሸጥ እየተስማሙ መሆኑን በበቂ ማስረጃ ካረጋገጠ በሗላ ክትትሉን በመቀጠል ሦስቱን ዋና ወንጀል ፈፃሚዎች የሰረቁትን መኪና በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 ልዩ ቦታው ቦሌ ቡልቡላ አካባቢ ለመሸጥ እየተደራደሩ እንዳለ በቁጥጥር ስር በማዋል የተሰረቀችውን መኪና ፣ ሁለት ሞባይል ስልኮችን ልዩ ልዩ ኤግዚቢቶችን ይዞ ምርመራውን መቀጠሉን ጨምሮ ገልፆል፡፡ ፖሊስ ባደረገው ክትትልና ምርመራ ማንነታቸው የማይታወቁ ወንጀል ፈፃሚዎችን በ48 ሰዓት ጊዜ ውስጥ በመለየት ሦስት ዋና ወንጀል ፈፃሚዎችንና ሦስት ግብራበሮቻቸውን በቁጥጥር ስር ማዋሉ ታውቋል፡፡

በመጨረሻም ለዚህ ስራ ስኬታማነት ቀና ትብብር ላደረጉ አካላት አዲስ አበባ ፖሊስ ምስጋናውን እያቀረበ የሜትር ታክሲ አገልግሎት የጥሪ ማዕከል ቁጥሮችን ሳይጠቀሙ አገልግሎት መስጠት ሆነ መቀበል እንዲሁም ከሚታወቀው የአገልግሎት አሰጣጥ ውጭ በዋጋ ድርድር የሚሰጥ የትራንስፖርት ግልጋሎት ለእንዲህ አይነት ወንጀል እየዳረገ ስለሆነ ተሳፋሪዎች ሆኑ አሽከርካሪዎች ጥንቃቄ ሊያደርጉ እንደሚገባ ፖሊስ መልእክቱን አስተላልፏል፡የምርመራ ሥራው እንዳበቃ የፍርድ ሂደት ውጤቱን በቀጣይ ለህዝብ እንደሚገለፅ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል ፡፡
21.2K views14:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-06 14:53:09
በታላቅ ድምቀት የተከበረው የ2017 ዓ/ም የሲዳማ ብሔረሰብ ዘመን መለወጫ ፊቼ ጨምበላላ በዓል በሰላም መጠናቀቁን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ገለፀ።

የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሽመልስ ቶማስ የበዓሉን ፍፃሜ አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች ህብረተሰቡና ፖሊስ በጋራ ተቀናጅተው መስራት በመቻላቸው በዓሉ በሰላም ተከብሮ መጠናቀቁን ገልፀዋል።

በዓሉ ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን ኃላፊነት ለተወጡ ለሁሉም የክልሉ ህዝብ፣ ሌት ከቀን ደከመን ሰለቸን ሳይሉ የፀጥታውን ስራ ላከናወኑ ለሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ ለፌደራል ፖሊስ፣ ለክልሉ ፖሊስ አመራርና አባላት እንዲሁም ለአጋዥ የፀጥታ ሀይሎች በኮሚሽኑ ስም ምስጋናቸውን ያቀረቡት ኮሚሽነሩ በቀጣይም በክልሉ ሁሉም ዞንና ወረዳዎች በዓሉ ቀጥሎ የሚከበር በመሆኑ የተለመደዉን ሰላም የማስጠበቅ ስራ በቅንጅት በመስራት ሁሉም ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።
23.4K views11:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-06 11:02:39
ትኩረት ለወላጅ አልባ ህፃናት

ሃሳቡ የተፀነሰው ከ6 ዓመታት በፊት ነው። መቅደስ የልጆች አድማስ ሙሉ በሙሉ አገር በቀል የሆነና በአርቲስት መቅደስ ፀጋዬ @mekdes_tsegaye_official የተመሰረተ የበጎ አድራጎት ድርጅት ነው::

ድርጅቱን ሙሉ ለሙሉ በመገንባትና በሙሉ አቅሙ ስራውን እንዲጀምር ለማድረግ እስከ አንድ ቢሊዮን ብር የሚያስፈልግ መሆኑን የገለፀችው አርቲስት መቅደስ በመጀመሪያው ዙር 200 ህፃናትን ከመላው ኢትዮጵያ እንደሚቀበል ተነግራለች።

ልዩ ትኩረት እና ጥበቃ ለሚያስፈልጋቸው ወላጅ አልባ ህፃናት ሁሉን አቀፍ እንክብካቤ በመስጠት በቀጣይ የሕይወት ጉዟቸው ስኬታማ እንዲሆኑ ለማድረግ ትኩረቱን አድርጎ የሚሰራ የበጎ አድራጎት ማዕከል እንደሆነ የተገለፀ ሲሆን በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ላይ በተሰማሩ ተፅእኖ ፈጣሪ ግለሰቦች በቦርድ አባልነት ተሰይመዋል፡፡ .

ያልተከፈለ ብዙ እዳ አለብኝ በማለት ህልሟን ይዛ ወደ ህዝብ የመጣችው አርቲስት መቅደስ፣ ማእከሉን እውን ለማድረግ ይፋ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሀግብር በሳምንቱ መገባደጃ በስካይ ላይት ሆቴል አስጀምራለች።
25.1K views08:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-06 11:02:25
ELEGAS ENGINEERING PLC
የእርስዎ አሳንሰር መፍትሄ ባለሙያዎች

ለ Elevator እና ለEscalator ከፍተኛ ደረጃ የምህንድስና መፍትሄዎች ያስፈልጎዎታል? በኢንዱስትሪው ውስጥ ግንባር ቀደም ኩባንያ ከሆነው ELEGAS ኢንጂነሪንግ አለሎት። ባለን ሰፊ ልምድ እና እውቀት ላለፉት 17 አመታት በአስራ በአምስት ሀገራት በልዩ ጥራተ‍እ አገልግሎት ስናቀርብ ቆይተናል። አሁን ደግሞ ላለፉት ሁለት ዓመታት የአገር ውስጥ ገበያን እያገለገለ አዲሱን የግንባር መስሪያ ቤታችን በኢትዮጵያ መከፈቱን በደስታእንገልፃለን።
በ ELEGAS ምህንድስና፣ ልዩ ፍላጎቶችዎን ለማሟላት የተዘጋጁ ምርጥ የምህንድስና መፍትሄዎችን በማቅረበ‍ኣችን እንኮራለን። የድርጅታችን ባለ ሞያዎች በምንሰራው እያንዳንዱ ፕሮጀክት የላቀ ጥራት ለማቅረብ ቁርጠኛ ናቸው።

ሚለየን ምንድነው?

የገጠማ ስራን ጨምሮ በአራት ወራት ውስጥ ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን አሳንሰሮች ከቱርክ የማድረስ ችሎታችን። ጊዜ ወሳኝ ነዋ

በተጨማሪም ከእያንዳንዱ ሊፍት ግዢ ጋር ጥቅል እናቀርባለን። በምርቶቻችን ላይ ለጋስ የሁለት ዓመት ዋስትና ያገኛሉ። በተጨማሪም የአሳንሰርህን ረጅም ዕድሜ እና ጥሩ አፈጻጸም ለማረጋገጥ የአንድ አመት ነጻ ጥገና እናቀርባለን።

የዋጋ አወጣጥን በተመለከተ፣ የፕሮጀክትዎን ፍላጎት የሚያሟላ ተለዋዋጭነት እናቀርባለን።

FOB፣ CIF፣ ወይም DDP፣ የዋጋ አወጣጥ አማራጮቻችንን ከተወሰኑ መስፈርቶች ጋር በማዛመድ እናዘጋጃለን።

ገጠማ የሚደርጉላችሁ የበርካታ
አመታት ከቱርክ የመጡ ልምድ ያላቸው crewዎች ናቸው።

We Care

አድራሻ:- ቡልጋሪያ ማዞሪያ የትራፊክ መብራት አጠገብ አዌባነ ህንፃ 1ኛ ፎቅ


+251 971 71 71 71
+251 994 69 69 69

www.elegas.com.tr

Email:- ethiopia@elegas.com.tr
21.9K views08:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-06 11:01:59
ናሽ ልዩ የጥርስ ህክምና ክሊኒክ ዘመኑ ባፈራቸው መሳሪያዎ ች በመታገዝ ሙሉ የጥርስ ህክምናን በመስጠት ላይ ይገኛል::  ከምንሰጣቸው አገልግሎቶች መካከል በከፊል
➢ መጥፎ የአፍ ጠረንን ማከም
➢ የቆሸሹ ጥርሶችን በማሽን እናፀዳለን
➢ በህክምና መዳን የማይችሉትን ጥርሶች መንቀል
➢ ወጣ ገባ ያሉ ጥርሶችን በ ኦርቶዶንቲክ አፕላይንስ እና በብሬስ ማስተካከል
➢ የጥርስ ስር ህክምናን መስጠት
➢ የተቦረቦሩ ጥርሶችን እንሞላለን
➢ የተነቀሉ ጥርሶችን በሰው ሰራሽ አርተፊሻል መተካት
➢ የጥርስ ራጅ አገልግሎት መስጠት

አድራሻ: ሜክሲኮ ቡልጋሪያ ጫፍ ትራፊክ ማብራቱ አጠገብ
  Tel: 0913858561
17.1K views08:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-06 10:50:18
#አይዴ_ጨምበላላ

የሲዳማ ብሔር ዘመን መለወጫ ፊቼ-ጨምበላላ በታላቅ ድምቀት በሀዋሳ ከተማ እየተከበረ ይገኛል። አባቶች በሶሬሳ ጉዱማሌ የቄጣላውን ዜማ እያሰሙ ይገኛሉ።

የሲዳማ ክልል ባህል ቱሪዝም ቢሮ ሃላፊ አቶ ጃጎ አገኘሁ የሲዳማ ህዝብ በፊቼ-ጨምበላላ ከዘመናቶች በፊት ከአለም የቀደመበት ታሪካዊ ፍታህዊነትን ያሰፈነበት በመሆኑ ዛሬ ዓለም ያደረሰብ ፍትሃዊነት እና እኩልነት ሲዳማ ከዛሬ መቶ አመታቶች በፊት ሲያደርገው የነበረ ነው።

በመሆኑም በፊቼ ጨምበላላ አባቶች በትኬሻቸው ጋሻ/ወንቆ እና ጦር በመያዝ ቄጣላ የሚያደርጉበት ኩነት ያለው ሲሆን ቄጣላ ደግሞ የሲዳማ አባቶች ሃዘናቸውን እና ደስታቸውን ብሎም ስሜታቸውን የሚገልፁበት የዜማ ስልት ነው። ይህም ፊቼ ጨምበላላ በአለም ቅርፅነት በዩኔስኮ በPerformance ሂደት እንዲመዘገብ የቄጣላ ዜማ ስርዓት ትልቅ አስተዋጽኦ ያደረገ መሆኑንም ገለፀዋል።

በተለይም በከሰሞኑ የተመረቀው የአፊኒ ፊልም የሲዳማ ህዝብ ግጭት አፈታት ሂደት ላይ ትኩረት ያደረግ ሲሆን አፊኒ ማለትም (አወቃችሁ) ማለት ሲሆንን የአፊኒ የግጭት አፈታት ባህልም የተወሰደው ከዚህው ከጨምበላላ በዓል ላይ መሆኑን የገለፁ ሲሆን በቂም በበቀል እና በግጭት ፊቼ ጨምበላላ መክበር በፍፁም እንደማይቻል አቶ ጃጎ ገለፀዋል።

አሁን የምናከብረው የጨምበላላ በዓል በጨምላላን እንኑር በሚል መሪ ቃል እንደመንግስት እየተከበረ መሆኑንም ገልፀዋል።
19.5K viewsedited  07:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-04 13:48:07
እየተከናወነ ያለው የህግ ማስከበር ስራ ውጤት እያመጣ በመሆኑ ሰላም እና መረጋጋት ለመምጣት የሚያስችል ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ።
የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳይ እንዲሁም የለውጥና የብልጽግና ዓመታት ጉዞን በተመለከተ ዛሬ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡
በመግለጫቸውም፤ መንግስት በሰላማዊ የመፍትሄ አማራጭ ችግሮችን በድርድርና በውይይት ለመፍታት፤ በሌላ በኩል ደግሞ ይህ አማራጭ ተቀባይነት ሲያጣ የሀገሪቱ ህግ በሚፈቅድለት አኳኋን ህግ የማስከበር ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል።
ይህም በመሆኑ በአብዛኞቹ የሀገሪቱ አካባቢዎች አንጻራዊ ሰላምና መረጋጋት መፍጠር መቻሉን ገልጸው፤ ይህንን ይበልጽ ማጽናት፣ መጠበቅና ዘላቂነቱን ማረጋገጥ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።
በአማራ ክልል የተጀመረው የህግ ማስከበር ስራ ውጤታማነቱን ጠብቆ መቀጠሉን ገልጸው፤ ክልሉም ከሞላ ጎደል ወደ ተሟላ ሰላም እና መረጋጋት ለመምጣት የሚያስችል ሁኔታ ተፈጥሮለታል ብለዋል፡፡
12 ሺህ የሚሆኑ የታጠቁ ሃይሎች መንግስት ያቀረበውን የሰላም ጥሪ በመቀበል ተሃድሶ በመውሰድ ወደ ህብረተሰቡ መቀላቀላቸውንም ጨምረው ገልፀዋል፡፡
ከ10 ሺህ ያላነሱ የቀድሞ የክልሉ ልዩ ሃይል አባላትም በተደረገላቸው ጥሪ መሰረት በተሃድሶ ስልጠናዎች አልፈው ክልሉን ከጥፋት ሃይሎች ለመታደግ የበኩላቸውን ድርሻ እየተወጡ እንደሚገኙ አመልክተዋል።
በሌላ በኩል የሽብር ቡድኑ ሸኔ ላይ እየተወሰደ ያለው እርምጃ ተጠናክሮ መቀጠሉን ጠቅሰው፤ በመጋቢት ወር ቡድኑ በሚንቀሳቀስባቸው አካባቢዎች ላይ የመከላከያ ሰራዊት ባደረገው አሰሳ እና ዘመቻ መጠነ ሰፊ እርምጃ መወሰዱን ተናግረዋል፡፡
በዚህም በርካታ የሽብር ቡድኑ አባላት መደምሰሳሰቸውን እና ለበርካታ አመታት ቡድኑ በብቸኝነት የተጠቆጣጠሯቸው ዋሻዎች፣ ጫካዎች እንደ መደራጃ፣ የሎጂስቲክስ ማከማቻ እና ማሰልጠኛ የሚጠቀሙበትን መቆጣጠሩን ገልፀዋል፡፡
በአጠቃላይ በተሰራው የህግ ማስከበር ስራ በተገኘው ውጤት ሰላም እና መረጋጋት ለመምጣት የሚያስችል ሁኔታ መፈጠሩን ተናግረዋል።
20.0K views10:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-04 13:45:43
ELEGAS ENGINEERING PLC
የእርስዎ አሳንሰር መፍትሄ ባለሙያዎች

ለ Elevator እና ለEscalator ከፍተኛ ደረጃ የምህንድስና መፍትሄዎች ያስፈልጎዎታል? በኢንዱስትሪው ውስጥ ግንባር ቀደም ኩባንያ ከሆነው ELEGAS ኢንጂነሪንግ አለሎት። ባለን ሰፊ ልምድ እና እውቀት ላለፉት 17 አመታት በአስራ በአምስት ሀገራት በልዩ ጥራተ‍እ አገልግሎት ስናቀርብ ቆይተናል። አሁን ደግሞ ላለፉት ሁለት ዓመታት የአገር ውስጥ ገበያን እያገለገለ አዲሱን የግንባር መስሪያ ቤታችን በኢትዮጵያ መከፈቱን በደስታእንገልፃለን።
በ ELEGAS ምህንድስና፣ ልዩ ፍላጎቶችዎን ለማሟላት የተዘጋጁ ምርጥ የምህንድስና መፍትሄዎችን በማቅረበ‍ኣችን እንኮራለን። የድርጅታችን ባለ ሞያዎች በምንሰራው እያንዳንዱ ፕሮጀክት የላቀ ጥራት ለማቅረብ ቁርጠኛ ናቸው።

ሚለየን ምንድነው?

የገጠማ ስራን ጨምሮ በአራት ወራት ውስጥ ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን አሳንሰሮች ከቱርክ የማድረስ ችሎታችን። ጊዜ ወሳኝ ነዋ

በተጨማሪም ከእያንዳንዱ ሊፍት ግዢ ጋር ጥቅል እናቀርባለን። በምርቶቻችን ላይ ለጋስ የሁለት ዓመት ዋስትና ያገኛሉ። በተጨማሪም የአሳንሰርህን ረጅም ዕድሜ እና ጥሩ አፈጻጸም ለማረጋገጥ የአንድ አመት ነጻ ጥገና እናቀርባለን።

የዋጋ አወጣጥን በተመለከተ፣ የፕሮጀክትዎን ፍላጎት የሚያሟላ ተለዋዋጭነት እናቀርባለን።

FOB፣ CIF፣ ወይም DDP፣ የዋጋ አወጣጥ አማራጮቻችንን ከተወሰኑ መስፈርቶች ጋር በማዛመድ እናዘጋጃለን።

ገጠማ የሚደርጉላችሁ የበርካታ
አመታት ከቱርክ የመጡ ልምድ ያላቸው crewዎች ናቸው።

We Care

አድራሻ:- ቡልጋሪያ ማዞሪያ የትራፊክ መብራት አጠገብ አዌባነ ህንፃ 1ኛ ፎቅ


+251 971 71 71 71
+251 994 69 69 69

www.elegas.com.tr

Email:- ethiopia@elegas.com.tr
18.6K views10:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-04 13:45:19
ናሽ ልዩ የጥርስ ህክምና ክሊኒክ ዘመኑ ባፈራቸው መሳሪያዎ ች በመታገዝ ሙሉ የጥርስ ህክምናን በመስጠት ላይ ይገኛል::  ከምንሰጣቸው አገልግሎቶች መካከል በከፊል
➢ መጥፎ የአፍ ጠረንን ማከም
➢ የቆሸሹ ጥርሶችን በማሽን እናፀዳለን
➢ በህክምና መዳን የማይችሉትን ጥርሶች መንቀል
➢ ወጣ ገባ ያሉ ጥርሶችን በ ኦርቶዶንቲክ አፕላይንስ እና በብሬስ ማስተካከል
➢ የጥርስ ስር ህክምናን መስጠት
➢ የተቦረቦሩ ጥርሶችን እንሞላለን
➢ የተነቀሉ ጥርሶችን በሰው ሰራሽ አርተፊሻል መተካት
➢ የጥርስ ራጅ አገልግሎት መስጠት

አድራሻ: ሜክሲኮ ቡልጋሪያ ጫፍ ትራፊክ ማብራቱ አጠገብ
  Tel: 0913858561
17.0K views10:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ