Get Mystery Box with random crypto!

Getachew shiferaw

የቴሌግራም ቻናል አርማ getachewshiferaw — Getachew shiferaw
የሰርጥ አድራሻ: @getachewshiferaw
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 44.30K

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2024-05-02 09:00:35
14.5K views06:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-02 09:00:21 የሚገርሙ፣ የሚያሳዝኑም ጉዳዮች ናቸው!

1) የጌታቸው ረዳ ጊዜያዊ አስተዳደር ከመቀሌ ውጭ ተንቀሳቅሶ ስብሰባ ማድረግ እንደማይችል ራሱ ጌታቸው ለትግራይ ሕዝብ ተናግሯል። ትግራይን የሚያስተዳድረው ከጦርነቱ በፊት የነበረው፣ ወንጀለኛ የተባለው መዋቅር ነው። ይህን ጌታቸው ረዳ በሚዲያ ወጥቶ ያረጋገጠው ነው። ይህ ህገወጥ መዋቅር ስለሆነ ነው ጊዜያዊ አስተዳደር ማዋቀር ያስፈለገው።

ትግራይ ውስጥ ከመቀሌ ውጭ ስብሰባ እንኳ ማድረግ የማይችለው የጌታቸው ረዳ አስተዳደር፣ በህጋዊ ስምምነት የተሰጠውን ትግራይን እንዳያስተዳድር ተደርጎ፣ በማያገባው ከትግራይ ውጭ ያሉትን የአማራ ግዛቶች እንዲያስተዳድር ነው የተደረገው። ሰሞኑን ትህነግ በወረራቸው የአማራ አካባቢዎች ጊዜያዊ አስተዳደሩ መዋቅሩን አሰማርቷል። ትህነግ ለጊዜያዊ አስተዳደሩ የፈቀደለት የወረራ አላማ ስለሆነ ነው። ትግራይ ውስጥ አንድም ቀበሌ እንዳያስተዳደር የተደረገው ጌታቸው የአማራን አካባቢዎች ግን በህገወጥ መንገድ እንዲይዝ ተደርጓል።

2) ሰሞኑን በትግራይ ፖለቲካ አጀንዳ የሆነ ጉዳይ አለ። ትህነግ የአማራ አካባቢዎች ተወልደው ያደጉትን አመራሮቹን "ትግሬ አይደላችሁም" እንዳላቸው የጊዜያዊ አስተዳደሩ አመራር ረዳኢ ሓለፎም ቃል በቃል ተናግሯል። የትግሬ ካባ የሚሰጠንም የሚቀማንም ሌላ ቡድን አለ ብሏል። የአድዋውን ቡድን ነው። ታዲያ ራያ ያደጉትን አመራሮቹን "ትግሬ አይደሉም። ባንዳ ናቸው።" ወዘተ እያለ የሚፈርጅ ራያን መሬቱንና መሬቱን ብቻ እንደሚፈልግ ግልፅ ነው። አመራሮቹን በጠላትነት የፈረጀ ለሕዝቡማ ያለው ጥላቻን መገመት ቀላል ነው። በተደጋጋሚ በተግባርም የታየ ነው።

3) ራያን የወረረው የትህነግ ታጣቂ "አርሚ 24" ይባላል። መከላከያን በመታበት ጥቅምት 24 የተሰየመ ነው። መከላከያ የተገደለበትን ቀን ማስታወሻ ያደረገውን
ኃይል ነው እያገዘ የሚገኘው።

4) የሰላም ስምምነቱ ያለ ምንም ማወላዳት የደነገገው፣ የጊዜ መንዛዛት ያልተቀመጠበት የትጥቅ መፍታት ነው። በማያሻማ መልኩ በአንድ ወር ውስጥ ትጥቅ ይፍቱ ተብሎ ነበር። ጭራሽ አስታጠቋቸው። መከላከያ ትግራይን ይረከብ ተብሎ ነበር። ጭራሽ መከላከያ ከትግራይ ወጥቶ አማራ ላይ ዘምቶ፣ ትጥቅ መፍታት የነበረበት ትህነግ አማራ ክልልን በኃይል እንዲይዝ ተደረገ

5) ትህነግ ባለፉት ወረራዎች ዘረፋ የሚፈፅሙትን በየጦሩ አደራጅቶ አሰማርቷል። በዘረፉት ልክ ጥቅም አግኝተዋል። እንደ ጀግና ታይተዋል። ይህ ኃይል ግን ወደ ትግራይ ተመልሶ አረመኔ ሆነ። የአርሶ አደር በሬ አርዶ መብላት፣ የተቋማትን ብረታብረት መዝረፍ ወዘተ። ሰሞኑን የትግራይ ክልል ውሃ መሳቢያ ብረቶች እየተዘረፉ መሆኑ በስፋት እየተሰራጨ ነው። ይህን የራሴ የሚለውን ትግራይን እየዘረፈ ያለ ኃይል ነው ጠላቴ ወደሚለው አማራ ይዘውት የመጡት። ከራያ ብቻ ከ50 ሺህ በላይ ሕዝብ የተፈናቀለውም ይህ አረመኔ ኃይል በሚፈፅመው ወንጀል ምክንያት ነው።

ይህ ሁሉ እየሆነ ያለው አማራ ላይ ነው!
13.2K views06:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-01 17:52:17
13.1K views14:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-01 17:52:06 የወረራ ዝግጅት!

ራያን የወረረው ትህነግ ጠለምትንና ወልቃይትን ለመውረር ቅድመ ዝግጅት እያደረገ ይገኛል። በዚህም መሰረት በሱዳን በኩል፣ አርሚ 11 ጠለምትን ለመውረር፣ አርሚ 17 ወልቃይትን ለመውረር ዝግጅት ላይ ነው፣ አርሚ 35 ከአክሱም ወደ ሽሬ የተንቀሳቀሰ ሲሆን ጥቅምት 24 መከላከያን የመቱበትን ማስታወሻ ያደረጉት "አርሚ 24" ደግሞ ራያን የወረረው ነው።

ይህ በሆነበት ብልፅግና የአማራ አስተዳደሮችን በሕገወጥ መልኩ አፍርሶ በተፈናቃይ ስም የወረራ በር እየከፈተና እያገዘ ይገኛል። እንደ ገለልተኛ "ትጥቅ መፍታት አለባቸው" እያለ የሚቀልደውም ዝግጅታቸውን ስለማያውቅ አይደለም። ማዘናጊያ ነው።

በሌላ በኩል በተቃዋሚም ሆነ በሌላ ስም ትህነግ ጋር ስምምነት ለመፈፀም የሚደረግን ሂደት የህዝብ ለህዝብ እያስመሰለ፣ የትህነግን ወረራ የሚያድበሰብስም የትህነግና ብልፅግናን የጓዳ ውልና የወረራ አላማ የሚያስፈፅም የአማራ ጠላት መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል።
14.1K views14:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-01 14:35:07 ያዘዝነውን ካላስፈፀመ መከላከያንም እናቀምሰዋለን ብለዋል! በአማርኛ ነው! ቀጥታ ትዕዛዝ ነው!


ሰሞኑን ትህነግ ባደረገው ሰልፍ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር አመራር መከላከያ በተገኘበት በአማርኛ ጭምር ያስተላለው ዛቻ ነው። መከላከያ የምንፈልገውን ካላስተገበረ ሱሪያችን ያውቃታል። ይቀምሳል ተብሏል።

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር አመራር የአማራን ርስቶች ለመያዝ ህፃናትና አዛውንቶች ይዘን እንደማንመጣ ይታወቃል ብሏል። እንዳሉት ተፈናቃይ ይዘው አልመጡም። ታጣቂ ነው ይዘው የመጡት። መከላከያም ባዘዝነህ መልኩ ካልሰራህ ሱሪያችን ታውቃታለህ ተብሏል። ይህ ጌታቸው ረዳ የሚያዘው ጊዜያዊ አስተዳደር አመራር ነው።


በጓዳ ውሉ ብቻ እንሄዳለን አላሉም። አለፍ ብለዋል። መከላከያን እንደ ቀበሌያቸው ሚሊሻ እናዘዋለን፣ ካልሆነ እናቀምሰዋለን ብለዋል።
14.0K viewsedited  11:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-01 13:44:25
15.0K views10:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-01 13:44:17 ትህነግ የጓዳ ውሉን ይፋ አደረገው!

ትህነግ በጀኔራል ታደሰ ወረደ በኩል የጓዳ ውሉን በማያሻማ መልኩ ይፋ አድርጓል። ብልፅግና ጠለምትና ራያን በቅርቡ፣ ከዛም ወልቃይትን አሳልፎ ለመስጠት የተዋዋለበትን በይፋ ተናግሯል። ከ50 ሺህ በላይ ንፁሃን በትህነግ ታጣቂ ከራያ የተፈናቀሉት በጓዳ ውሉ መሰረት እንደሆነ ይታወቃል። አማራ እየተወረረ ያለው በጓዳ ውሉ መሰረት ነው።

የብልፅግና አመራሮች ስለ ትህነግ ትጥቁን መፍታት ወዘተ ሲያወሩ "ውሸታቸውን ነው" የምንለው በምክንያት ነው። ጦርነት የሚፈልግ ኃይል ወዘተ እያለ የሚያወግዙ የሚመስሉት ውሸት ነው። የአማራን ግዛቶች አሳልፈው ለመስጠት የተዋዋሉት በወረራ መሆኑ ይፋ ወጥቷል። ታደሰ ወረደ ብልፅግና አማራን በኃይል እንዲይዙ የሰጣቸውን ድጋፍና ፈቃድ በሚዲያ ወጥቶ ሲገልፅ ይህ ሁለተኛ ጊዜው ነው። እነ ተመስገን ጥሩነህ "ያፈነገጠ ወዘተ" እያሉ ሀሰት ሲናገሩ፣ ጀኔራል ታደሰ በይፋ መጥቶ ከብልፅግና ጋር የተዋዋሉት የጓዳ ውል መሆኑን እየገለፀ ነው።

አማራን በትህነግ እያስወረረ የሚገኘው ብልፅግና ነው። ትህነግ ባለፈው በጌታቸው ረዳና ታደሰ ወረደ፣ ዛሬም በታደሰ ወረደ በኩል ወረራው ከብልፅግና ጋር በተስማሙት መሰረት የተደረገ እንደሆነና እንደሚቀጥል ሲገልፅ ብልፅግና ትንፍሽ አላለም። የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደሮች ናቸው ወረራው በስምምነት የተፈፀመ መሆኑን የሚናገሩት። ያፈነገጠ ወዘተ የሚባለው ነጭ ውሸት ነው። ማዘናጊያ ነው። የጓዳ ውሉን ማድበስበሻ ነው!
15.7K views10:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-30 10:38:39 ሬዲዮው የትህነግ/ህወሓት ባትሪ ሳይጎርስ!
13.3K views07:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-30 09:18:16
14.6K views06:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-30 09:18:07 የእስር ሰለባው ጋዜጠኛ ለምክክር ኮምሽኑ ያነሳቸው ወሳኝ ጥያቄዎች

ሞኝን እብባ ሁለት ጊዜ ነደፈው፤ አማራስ ሁለት ጊዜ ይነደፍ ይሆን! በፍጹም!

(ዳዊት በጋሻው ከቃሊቲ እስር ቤት)

ሚያዚያ 13 እና 14 2016 ዓ.ም በትጥቅ ትግል ላይ የሚገኙ ኃይሎች ወደ ምክክር እንዲመጡና ለዚህም ከለላ እንደሚደረግ የሚገልፀ ዜና ተመለከትኩ፡፡ ይህንን ያሉት የሀገራዊ ምክክር ምክትል ዋና ኮሞሽነር ሂሩት ገ/ስላሴ ናቸው፡፡ ወቅቱ አሰቃቂ የጭንቅ ጊዜ ሆነ እንጅ ንግግራቸው ሙሉ የኮሜዲ ይዘት ያለው ነው፡፡ ግለሰቧ ይህንን በተናገሩበት ወቅት የአማራ ልጆች በማንነታቸው ብቻ እየተመረጡ የሀገሪቱን እስርቤቶች ሞልተዋል፡፡ የአማራ ልጆች በአዲስ አበባ እና በሌላው የሀገሪቱክፍሎች በሀሠት እየተከሰሱ ፤ እንደ አዋሽ አርባ ባሉ የማሰቃያ ቦታዎች መከራቸውን እያ ባለበት ወቅት ከለላ እናደርጋን እንመካከር እያሉ ማውራት ህሊና ቢስነት ነው፡፡ በታሪክ ፊትም ተጠያቂ ያደርጋል፡፡ የአማራ ልጆች የዕድሜ ፣የሙያ የፆታ፣ የእምነት፣ የት/ት ደረጃ ልዩነት ሳይኖር በጅምላ እየታሰሩ ነው፡፡ በሀገሪቱ ያሉ እስር ቤቶች በመሙላታቸው የብልፀሸግና ፓርቲ አመራሮች በኦሮምያና በአፋ አማራ የሚታጎርባቸው ወህኒ ቤቶች በአጭር ጊዜ እንዲሰሩ ማዘዛቸው ተረጋግጧል፡፡ በዚህ ሁኔታ ነው እንግዲህ ስለምክክርና ስለከለላ ዋስትና እየተወራ ያለው፡፡ እስኪ ለኮሚሽኑ አባላት በተለይም ለዋናና ለምክትላቸው እነዚህን ጥያቄዎች ላንሳ፡-

1. በአማራ ህዝብ ላይ እየተፈፀመ ያለውን የዘር ማጥፋትወንጀል እያያችሁና በዚህም ላይ ምንም ሳትሉ ስለምክክር ስታወሩ ህሊናችሁ ምን ይላችኋል?

2. በአስቸኳይ አዋጅ ሰበብ ንፁሀንን በድሮን እየተጨፈጨፉ እናንተ እንመካከር ስትሉ ህዝቡ ምን የሚል ይመስላችኋል?

3. ፖሊስና ደህንነት የነቁ አማሮችንበመላው ሀገሪቱ እያሳደዱ ባሉበት ሁኔታ እናንተን አምኖ ጠረንጴዛ የሚስብ ያለ ይመስላችኋል?

4. እናንተ ከለላ እንስጣችሁ የምትሏቸው የአማራ ህዝብ የትግል መሪዎች በፍትህ ሞኒስቴር ተከሰው በጋዜጣ ተጠርተዋል፡፡በአንድ በኩል የወንጀል ክስ ከፍቶ በሌላ በኩል ከለላ ልስጥ ማለት አይጋጭም ወይ?

በመሰረቱ እኔ ጥያቄን ባሳደገኝ ህዝብ ጨዋነት ልክ በትህትና ላቅርብ ብዬ እንጅ ስለ 11ዱም ኮሚሽነሮችመረጃም ማስረጃም አለኝ፡፡

ለምሳሌ ያህል ስለ ፕ/ር መስፍን አርአያ ፣ መሐመድ ድፈር፣ ዮናስ አዳዬ፣ ዘገዬ አስፋው በደንብ መናገር ይቻላል፡፡
የምክክር ኮሚሽኑ አባል አቶ ዘገዬ አስፋው የኦነግ ስራ አስፈጻሚ መሆን በሽግግሩ ወቅት የአማራ ህዝብን አስጨፍጭፏል፡፡ ይህ ተራ አሉባልታ ሳይሆን በሰነድ የተቀመጠ ሀቅ ነው፡፡በመሆኑም በወቅቱ የግብርና ሚኒስትር ነበር፡፡ በጥቅሉ በአማራ ህዝብ ላይ የዘር ማጥፋት ወንጀል የፈፀመና ያስፈፀመ በመሆኑ ህዝብ በወንጀል ይፈልገዋል ፡፡ በተጨማሪም የአማራ ልጆች በአዲስ አበባ ዙርያ ቤታቸው ፈርሶ፣ ተፈናቅለው በስቃይ ላይ ሆነው ፤ለንብረታቸውና ለህይወታቸው ምንም ይቅርታና ዋስትና ሳይደረግ በማን አለብኝነት ሸገር ከተማ ብሎ አቶ ሽመልስ አብዲሳ ከተማ ሲያስመርቅ አቶ ዘገየ አስፋው የድግሱ ተካፋይ ነበር፡፡ ስለሌሎችም ሙሉ ማስረጃ አለ፡፡ የኮሚሽኑ ገለልተኛነት እዚህ ድረስ ነው፡፡ ለማንኛውም ለአፍና ለይምሰል እንኳን እነዚህን ጥያቄዎች ለማንሳት ሞክሩ፡-

1) መንግስት የምትሉት አካል ተኪስ እንዲያቆምና የዘር ፍጅቱን እንዲተው

2) አዋጅ ተብዬው መግደያና ማሳደጃ እንዲቀርና ለዚህም ተጠያቂ እንዲሆን

3) በመላው ሀገሪቱ ያለውን የንፁሀን ግድያ እንዲያቆም በተደጋጋሚ ብትናገሩ ለይምሰል እንኳን የተሸለ ይሆናል፡፡

በመሰረቱ ዐቢይ አህመድ ምክክር ኮሚሽንና ሽግግር ፍትህ እያለ ያለው፦

1. በነዚህ ተቋማት ሰበብ የውጭ ምንዛሬ ለማግኘት

2. ዓለም አቀፉን ማህበረሰብ ይሄው ላወያይ ነው ለማለትና ስልጣንን ለማራዘም ነው፡፡ ያም ሆነ ይሕ ግን ከዚህ በኋላ የአማራን ህዝብ ለዓመታት አይደለም ለቀናት መሸወድ ወይም በሽመልስ አብዲሳ አገላለፅ (ኮንቪንስና ኮንፊውዝ) ማድረግ በፍፁም አይቻልም፡፡ ከዚህ በኋላ ጥቅም ላይ የሚውል አይደለም፡፡

ለማንኛውም ለይምሰል የሚደረግ የትኛውም ድርጊት ከህዝብ አያመልጥም፡፡
መንግስቱ ሀይለማርያም በስተርጅና ለስደትና ለውርደት፤ መለስ ዜናዊን በህዝብ ፊት ለውርደት ብሎም ለሞት የዳረጓቸው ሁኔታዎች እልህና ይምሰል ናቸው ( የፈጣሪን ሀያልነት ረስቼ አይደለም)፡፡ ያም ሆነ ይህ አማራን እያሳደዱ መመካከር፤ ማስነገር ጊዜው አልፎበታል፡፡ የአማራ ህዝብ ከዚህ በፊት በወለጋ፣ በመተከል፣ በሀረርጌ፣ በአርሲ፣ …. ሲጨፈጨፍ ነበር፡፡ አሁን ደግሞ ጭፍጨፋው ቤቱ በር ላይ ነው፤ይ የማንክደው ሀቅ ነው፡፡ ለህልውና መታገል ደግሞ ፈጣሪም ዓለም አቀፍ ማህበረሰብም የሚደግፈው ነው፡፡
ሕዝብ ማሸነው አይቻልም
የአማራ ህዝብ ትግል ለእውነት፣ ለፍህ፣ ለለውጥ ነው፡፡
14.4K views06:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ