Get Mystery Box with random crypto!

Getachew shiferaw

የቴሌግራም ቻናል አርማ getachewshiferaw — Getachew shiferaw
የሰርጥ አድራሻ: @getachewshiferaw
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 44.30K

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2024-04-13 23:51:30 ማጭበርበሪያ!

ደብረፅዮን የሚመራው ትህነግ/ህወሓት የወልቃይት፣ ራያ፣ ጠለምትና አበርገሌ ወረዳና ቀበሌ አስተዳደሮችን መልምሎ ትግራይ ውስጥ ፅ/ቤት ከፍቶላቸዋል። ከስር እንደሚታየው በአማራ ግዛቶች ስም የፌስቡክ ገፅ ከፍተው የሚያስተዳድራቸው ትህነግ/ህወሓት እንደሆነ አድርገው፣ ሽሬና መቀሌ የወረዳና የቀበሌ እንዲሁም ከተማ አደረጃጀቶች እንደሆኑ አድርጎ ባነር አሳትሞ እየሰበሰበ፣ በአካባቢዎቹ ስም ህገወጥ ማህተም ቀርፆ ደብዳቤ እየፃፈ ወደ አዲስ አበባ መጥቶ ደግሞ "ተፈናቃዮች ይመለሱ" ይላል።

ሰሞኑን በነበረው ስብሰባ ሞንጆሪኖና የትህነግ ጀኔራሎች ትህነግ/ህወሓት ያለምንም ልዩነት የተስማማበትን እስከነ መዋቅሩ መመለስ አቋም እንዲያራምዱ ተደርጎ፣ እነ ደብረፅዮን ከዚህ ሀሳብ የሚለዩ መስለው ቀርበዋል። ጌታቸው ረዳም ሆነ ደብረፅዮን በዚህ ጉዳይ ከጀኔራሎቹ ጋር ልዩነት የላቸውም። የቤት ስራ ነው የተከፋፈሉት። በውይይት የተወሰኑት እንዲሳተፉ ቀሪው የተለየ አቋም የያዘ መስሎ በተግባር እንዲሰራ ነው። በዚህ ማጭበርበሪያ መሰረት ከብልፅግና ጋር እየተሰበሰቡ ነው። ብልፅግና የአማራን ርስቶች በዚህ ሂደት አሳልፎ ለመስጠት እየሰራ ነው።
16.5K views20:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-12 12:52:28 "ፎርማት" ተደርጎ ተከራዬ!

እኔ አይደለሁም ያልኩት። አለቃው ነው። እንደ አመታዊ የፋይናንስ ሪፖርት ቁጠሩት። ኤርሚያስ ለገሰ መከራየቱን አለቃው ቴድሮስ ፀጋዬ በቀጥታ ስርጭት ተናግሯል። እነ ቴድሮስም ከሌላ ቀምተው ነበር የተከራዩት። አሁን ባለጊዜ ጨምሮ ወሰደው።

ትህነግ ኤርሚያስን በቴድሮስ በኩል ነበር የሚያዘው። አሁን አለቃው በብስጭት "ፎርማት ተደርጎ ተከራይቷል" ብሏል። ያው እነ ቴድሮስ (አንዱ የትህነግ ክንፍ) ኪራዩን መክፈል ስላልቻሉ ሌላ ተከራየው። የፖለቲካ ገበያው ሲሞቅ ዋጋ አስወደደ።

በእርግጥ ቴድሮስ ይህን ያለው በድሮው ዕዝ ስለማይሰራለት እንጅ ኤርሚያስ በሌሎች ቡድኖች በኩል ለትህነግ እየሰራ ነው። ደሞዝ ጨምሩኝ ብሎ ካልሆነ ከዛ ሰፈር ያለው የረዥም ጊዜ ውል ነው። ግን ፖለቲካው ተለዋዋጭ ስለሆኑ ሁለት ቦታ ተቀጥሯል። ፖለቲካው ሲገለባበጥም ቋሚ ገቢ ይኖረዋል። እየተገለባበጠ መስራት ነው።

ከወራት በፊት እንደፃፍኩት ኤርሚያስ ሬድዮ ነው። ባትሪ ያለው እስከመጨረሻው ከፍቶ ያስጮኸዋል። እስካሁን ይህን ራዲዮ ከፋች የነበረው ቴድሮስ አሁን በሌላ ሰው እጅ ነው ብሏል። የማስታወቂያ ከሰጡት በመሃል በመሃል ይዘፍንላቸዋል። የተሻለ የሚከፍለው ከሆነ ልዩ ዞንም፣ ልዩ ወረዳም የፈለገ ይከራየዋል። የሀሰተኛ ፖስተሮችም ቢሆን ካገኙት ማሪያምን እየሰደበ ፕሮግራም ከመስራት ወደኋላ አይልም።

ኤርሚያስ በቀጥታ ስርጭት ተሸጠ ተለወጠ ሲባል ደፍሮ የድሮ አለቃውን አይናገርም። ምክንያቱም በርካታ መረጃ ተይዞበታል።
20.4K viewsedited  09:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-12 11:51:56
16.8K views08:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-12 11:51:45 የተፈለገው ይሄ ነው!

ትህነግ ወደራያና ወልቃይት ተፈናቃይን አልመልስም ብሏል። ከእነ ሙሉ መዋቅሬ ነው የምመለሰው ብሎ እየሰራ ነው። ብልፅግና ሰሞኑን ያለ በጀት ከህዝብ ገንዘብ ሰብስበው ልማት የሚሰሩትን አስተዳደሮች አፈርሳለሁ ያለ ሲሆን ትህነግ እስከ ቀበሌ ድረስ አመራር፣ የፓርቲ መዋቅር፣ ፀጥታ አደራጅቶ እየጠበቀ ነው። ትግራይ ውስጥ ቁጭ ብለው የራያና ወልቃይት እስከ ቀበሌ ድረስ መዋቅር ተብለው ተዘጋጅተው መግለጫ እየሰጡ፣ መታወቂያ እያደሉ፣ በማህተም ደብዳቤ እየፃፉ ይገኛሉ። ብልፅግና ይህን ያውቃል።

የተፈለገው የህዝብ አስተዳደርን አፍርሶ ለትህነግ ማስረከብ ነው። የመጀመሪያው ትህነግ የሁመራ ፅ/ቤት ብሎ ያደራጀው መዋቅር የሚጠቀምበት ገፅ ማስረጃ ሲሆን ሁለተኛው የአላማጣ ከንቲባ ብሎ ማህተም አስቀርፆ ደብዳቤ የሚፅፍበት ነው። ሁሉም ወረዳዎች፣ ቀበሌዎች፣ ከተሞች መሰል መዋቅር አዘጋጅቶ ህጋዊ አስመስሎ እየሰራው ነው።

"ተፈናቃይ ይመለስ" ማለቱን ተከትሎ ደግሞ "ኬር ኢትዮጵያ" በሚባል ድርጅት ድጋፍ በርካታ መታወቂያ ተዘጋጅቷል። ራያና ወልቃይትን የማያውቀውን ጨምሮ በርካታ ህዝብ መታወቂያ ተሰጥቶት እናሰፍራለን እያሉ ነው።

አንድም የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ግዴታውን ሳይወጣ፣ በስምምነቱ መሰረት በአማራ ክልል እንዲቆዩ የተደነገገላቸውን አካባቢዎች አሳልፎ ለመስጠት በተሰራው ደባ የልብ ልብ የተሰማው ትህነግ ለአካባቢዎቹ በህገወጥ ማህተምና ደረሰኝ የሚጠቀም ሙሉ መዋቅር አዘጋጅቷል። ብልፅግና ይህን ያውቃል። ወንጀል ግን አይመስለውም። የህዝብ አስተዳደር የሚያፈርሱት ግን ለዚህ ህገወጥ ቡድን አሳልፎ ለመስጠት ነው!
19.7K views08:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-10 18:06:16 ከአንተ ኢሳያስ አፈወርቂን ይቅር ቢሉት ይቀላቸዋል!

ኤርሚያስ ለገሰ ትህነግ "ይቅር" ይለኛል ብሎ የትህነግ የወልቃይትና ራያ አስመላሽ ኮሚቴ ሆኖ ከርሟል። ሰሞኑን በይፋ አብይን ደግፎ ተናግሮ ተናደውበታል። በሙዚቃ አቀናብረው ያስቀመጡትን እያወጡለት ነው። ለጊዜው በከፈሉህ ትሰራለህ እንጅ መቸም አይለቁህም። አንተን ከሚምሩህ ኢሳያስን በቀላሉ ይቅር ይሉታል።
14.9K views15:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-08 17:30:09 ይለይላችኋ! ምን አገባን!

የፖለቲካው አሰላለፍ ሲለይለት ግልጥ እያለ ይመጣል! ቴድሮስ ፀጋዬ ኤርሚያስ ከኦሮሞ ብልፅግና ጋር ሲገናኝ ደርሶበት ካባረረው ቆይቷል። ለኤርሚያስ ቴድሮስ ነበር ከህወሓት ጋር መገናኛ ገመዱ፣ አሁን አማራጭ ፍለጋ የትግራይ አክቲቪስት በየቀኑ ያቀርባል። ያም ሆኖ ኤርሚያስ አልተረፈም። ፖለቲካው ከረር ሲል የኦሮሞ ብልፅግና አጀንዳውን ሲያመጣ ፀቡ ግልፅ እየወጣ ነው።

በነገራችን ላይ ኤርሚያስ "አንተምኮ ወገን አለህ" ተብሎ የኦሮሞ ብልፅግናን በይፋ ከወገነ ቆይቷል። ትህነግን ደግሞ ለጥቅም። ዞሮ ዞሮ ይለይላችሁ! የሚያገባን ነገር የለም!
14.2K views14:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-07 14:06:14
13.1K views11:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-07 14:05:56 የጠለምት አማራ አደባባይ ወጥቶ የሰሞኑን አስተዳደር ማፍረስና ህዝብ ለዳግም የትህነግ ባርነት አሳልፎ መስጠት ሴራ "አንቀበለውም" ብሏል። "አማራ ነን አልን እንጅ አማራ እንሁን ብለን አልጠየቅንም" ሲሉ ሰልፈኞቹ ተቃውሞ አሰምተዋል።
12.8K views11:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-05 16:43:46
17.7K views13:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-05 16:43:36 የታሰበው ይህ ነው!

የብልፅግና የሴራ ውሳኔ በአደባባይ የተገለጠበት የትህነግ መግለጫ!

ብልፅግና ያለ ምንም በጀት ከህዝብ ገንዘብ ሰብስቦ ልማት ሲሰራ የከረመውን የወልቃይት አስተዳደር ለማፍረስ ከወሰነ ሰንብቷል። ትህነግ/ህወሓት ደግሞ "ከብልፅግና ጋር በተስማማሁት መሰረት" ብሎ ለወልቃይትና ጠለምት አመራር አዋቅሮ እነዛን ወደር የለሽ ጨፍጫፊዎች ሊመለሱ ዝግጅት ላይ ናቸው ብሏል። የወልቃይት አማራ ከቀየው እንዲወጣ በይፋ በመግለጫው የዘር ፍጅት ማስጠነቀቂያ ጨምረውበታል።

ትህነግ ዛሬ በፌስቡክ ገፁ ባጋራው፣ ሚዲያዎቹ በዘገቡት ከብልፅግና ጋር ተስማምቸበታለሁ ብሎ ያዋቀረው የወልቃይትና ጠለምት አመራር ነኝ ባይ መግለጫ እስከ ቀበሌ ድረስ አደረጃጀቶችን አዋቅሬያለሁ ብሏል። ብልፅግና አስተዳደሩን አፍርሸ በገለልተኛ ወዘተ እያለ ቢቀልድም አላማው ትህነግ አመራር አዋቅሮ እንዲረከበው ማድረግ ነው። ከሌላ የተሰማ አይደለም። ትህነግ በይፋ ገልፆታል። የወልቃይትና ጠለምት ጉዳይ ላይ የተደረገው ለራያና አበርገሌም ተመሳሳይ ነው።

ብልፅግና በጓዳ ስምምነቱ መሰረት የአማራ ግዛቶችን ለትህነግ/ህወሓት አሳልፎ ለመስጠት በወሰነው መሰረት ትህነግ በይፋ ለግዛቶቹ እስከ ቀበሌ አመራር አደራጅቶ እየጠበቀ መሆኑን በመግለጫው አሳውቋል። በስብሰባዎቹም ብልፅግና ጋር በተስማሙት መሰረት የተደረገ እንደሆነ መግለፃቸው ታውቋል። የተፈለገው ይህ ነው።

በሰላም ስምምነቱ መሰረት የመጀመሪያው ቅድመ ሁኔታ የትህነግ ታጣቂ ትጥቅ መፍታት ቢሆንም ያ ጨፍጫፊ ታጣቂም ትህነግ ለአማራ ግዛቶች አዋቅሬዋለሁ ያለው አስተዳደር አካል ሆኖ ለመግደል እንደሚላክ ተገልፆአል። በቅርብ ብልፅግና ቀስ በቀስ ህዝብን ለማለማመድ በአክቲቪስቶቹ ባሰራጨው ውሳኔ የማይካድራ ጨፍጫፊዎች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንደሚመለሱ ገልፆአል። አላማውም ትህነግ ያዋቀረውን አመራር ተከትለው ጨፍጫፊዎቹ ከእነ ትጥቃቸው ስለሚገቡ ነው። ብልፅግና ሰሞኑን በውሳኔ ስም ውስጥ ለውስጥ ያሰራጨው አላማም ለዚህ የትህነግ ገዳይ ቡድን መደላድል መፍጠር ነው። በአደባባይ ትህነግ የገለፀው፣ በመግለጫ ያወጀው እውነት ነው!

ብልፅግና በጓዳ የተዋዋለውን ትህነግ ትግርኛ የሚችል የሌለ ያህል እየተሰማው በአደባባይ ያጋልጠዋል። ይህ መድረክም የብልፅግና የሴራ ውሳኔ በአደባባይ የተጋለጠበት ነው።
16.2K views13:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ