2024-05-12 11:03:33
ነገሩ ይበልጥ ግልፅ ሆኗል!
ለእነ አልቡርሃን መሳሪያ የሚያቀብለው ባለሀብት ታስሯል። የትህነግ/ህወሓት ባለስልጣን ሚስጥር ያወጣብን ጌታቸው ረዳ ነው ሲል ከስሷል።
1) ሰሞኑን ታደሰ ወረደ ቀርቦ በተናገረበት ሚዲያ ከሶስት ወር በፊት ጌታቸው ረዳ ከስልጣን ያባረረው የህወሓት አመራርም ቀርቦ ጌታቸው ሚስጥር እንዳወጣ ጠቁሟል። ሚዲያውም ርዕሱን በግልፅ ጌታቸው ለአረብ ኢሜሬትስ ባለስልጣናት መናገሩን በሚገልፅ መልኩ ነው ያስቀመጠው።
2) የህወሓት ባለስልጣን የሆነው አባዲ ዘሙ ልጅ ዳዊት ገብረእግዚያብሔር የሚባለው የሞንጆሪኖ ወንድም በሌላ አገር በኩል ወደ ትግራይ ሲገባ የተቀበለው ጌታቸው ረዳ እንደሆነና ከእነ ጌታቸው አሰፋ ጨምሮ ከትህነግ/ህወሓት አመራሮች ጋር መምከሩን ሰሞኑን ፅፎ ነበር። ይህ ባለሀብት በትህነግ የስልጣን ዘመን ለመከላከያ ጭምር መሳሪያ ደላላ የነበረ ሲሆን ከትህነግ/ህወሓት ጋር በነበረው ጦርነት ለትህነግ በሱዳን በኩል በአልቡርሃን ድጋፍ መሳሪያ አስገብቷል። ከአረብ አገር የመሳሪያ ደላላዎች ጋር የሚሰራ ሰው ነው። በጦርነቱ ወቅት ከትግራይ በጀት መዳቢዊ እህቱ ሞንጆሪኖ ነበረች። በአንድ ግምገማቸው ሞንጆሪኖ ወደ ሱዳን የላከችው የፀረ ድሮን መግዢያ መበላቱ ታምኖበታል። ዳዊትና እህቱ በሱዳን በኩል በአልቡርሃን እገዛ መሳሪያ ሲገዙ የከረሙ ናቸው። አሁንም ለአልቡርሃን መሳሪያ ማስገባታቸውን መቀጠላቸው ተሰምቷል።
3) የኤርትራ ደህንነት መስሪያ ቤት መረጃ የሚሰጠው አንድ ሁነኛ የኤርትራ ሚዲያ ደግሞ ባለሀብቱ በቅርቡ የሱዳን ጦርነት ወቅት ለአልቡርሃን መሳሪያ እያስገባ እንደሆነ ተደርሶበታል ብሏል። በዚህ ምክንያት ሰሞኑን ባለሀብቱ የታሰረው በአረብ ኢሜሬትስ ሲሆን አረብ ኢሜሬትስ የፈጥኖ ደራሹ ደጋፊ፣ ትህነግ በእነ ዳዊት በኩል ለአልቡርሃን መሳሪያ አድራሽ ሆነው የጥቅም ግጭት ውስጥ እንደገቡ ተፅፏል። የኤርትራው ደህንነት ምንጭ ዳዊት የተያዘው ከመቀሌ በወጣ ሚስጥር እንደሆነ ገልፆአል።
4) የትህነግ/ህወሓት አክቲቪስቶች ደግም ባለሀብቱን ያስያዘው ጌታቸው ረዳ ነው ብለው እየፃፉ ነው።
5) ለአልቡርሃን መሳሪያ የሚያቀርበው የሞንጆሪኖ ወንድም በህገወጥ መንገድ ድንበር አቆራርጦ ትግራይ ገብቶ ከትህነግ/ህወሓት አመራሮች ጋር መነጋገሩ ከዚህም ከፍ ያለ አላማ መኖሩን ያሳያል። ሰሞኑን የታሰረው ጅቡቲ ውስጥ ነው ወዘተ የተባለው ከትግራይ በጅቡቲ በኩል ሲሸኙት ይሁን ደጋግሞ ሲመላለስ አልታወቀም። ነገር ግን ወደ ትግራይ የተመላለሰበትን አላማ ለመደበቅ "ጅቡቲ ያለውን ፕሮጀክቱ ሲጎበኝ ተያዘ" እያሉ ለመሸፋፈን ጥረዋል።
አጠር ሲል!
1) ትህነግ ከታጣቂ አልፎ በትጥቅም ከአልቡርሃን አቅርቦት በማገዝ ጋር መሆኑን አመራርና አባላቱ አምነዋል።
2) እነ ጌታቸው ረዳ ከትህነግ/ህወሓት አላማ ስለተለዩ ሳይሆን በአካሄድ ልዩነትና ስልጣን ጉዳይ በሱዳን ጦርነት መሳተፋቸውን ያመኑ መሆኑን።
3) በጊዜያዊ ስልጣን ከጌታቸው ረዳ ጋር ልዩነት ያላቸው ጌታቸው ረዳ አሳልፎ ሰጠን ማለታቸውን
4) የትህነግና የአልቡርሃን ጉዳይ የዓለም አቀፍ መሳሪያ ዝውውርንም የሚጨምር፣ በዚህ ጉዳይ በተጨባጭ የተሳተፈው ባለሀብት መታሰሩንም የሚያሳይ ነው።
5) ባለሀብቱ ለሱዳኑ ጀኔራል መሳሪያ ከማቅረብ አልፎ በህገወጥ መንገድ ድንበር አቆራርጦ ትግራይ ድረስ መጥቶ ከእነ ጌታቸው አሰፋ ጋር የመከረው መቀሌ ናፍቃው ሊሆን አይችልም።
17.0K views08:03