2022-06-20 02:00:38
አቢ አብባስ አብደሏህ ኢብኑ አብባስ ኢብኑ አብደል ሙጦሊብ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) በሀዲሰል ቁድስ ተከታዩን ተናግረዋል፡- ‹‹አላህ መልካምና ክፉ ተግባራትን ፅፏል፤ ይህንኑ አብራርቷልም፡፡ አንዲትን መልካም ተግባር ለመፈፀም ያሰበና ያልፈጸማት ልዑልና ቁድስ የሆነው አላህ ከርሱ ዘንድ አንድ ሙሉ መልካም ተግባር (የመልካም ተግባር ምንዳ) ይፅፍለታል፡፡ አስቦ ከፈፀማት ደግሞ ከ10 እስከ 700 እጥፍ፣ ከዚያም በላይ መልካም ተግባራትን ይፅፍለታል፡፡ ክፉ ተግባር አስቦ ካልፈፀማት አላህ ከርሱ ዘንድ አንድ ሙሉ መልካም ተግባር ይፅፍለታል፡፡ ግን አስቦ ከፈፀማት አንድ ክፉ ተግባር ብቻ ይፃፍበታል፡፡
ሐዲሱን ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል
‹‹ መልካም ተግባርን ለመፈፀም አስቦ (ኒያ ኖሮት) መፈፀም ባይችልምም አላህ ምንዳውን አይነሳውም፡፡
‹‹ ክፉ ነገር ለመፈፀም ኒያ ኖሮት ግን አላህን ፈርቶ ከመፈፀም የተቆጠበ አላህ መልካም ተግባር ምንዳ እንደሚፅፍለት፡፡
Share share share share share share
100 viewsቢስሚላሂ, 23:00