Get Mystery Box with random crypto!

አዳብና መልቲ ሚዲያ

የቴሌግራም ቻናል አርማ adabnamidea — አዳብና መልቲ ሚዲያ
የቴሌግራም ቻናል አርማ adabnamidea — አዳብና መልቲ ሚዲያ
የሰርጥ አድራሻ: @adabnamidea
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 817

Ratings & Reviews

1.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 8

2022-11-01 13:16:25 የስራዋ ልዕልት
ጊስት (እማሆይ) ዘምዘም ገርቢ
----------------
ድንቅ በጎ ስራ ለሰሩ፣ አርአያ ለሆኑ እና ለታታሪ ሴቶች የሚሰጥ“ጊስት” የሚባል ማዕረግ ከጉራጌ ህዝብ በክብር ተሰጥቷቸዋል፡፡ የስራ ልዕልት እንደማለት ነው፡፡
ዘምዘም ገርቢ፡፡ በኋላም መንኩሰው “እማሆይ” ተብለዋል፡፡
ልክ እንደ ዶ/ር ካትሪን ሀምሊን፣ ክብርት ዶ/ር አበበች ጎበና የማይረሳ በጎ ስራ የሰሩ ብርቱ ሰው ናቸው፡፡ ነገር ግን የስራቸውን ሩብ እንኳን ያልተነገረላቸው፡፡
በልጅነታቸው ትምህርት የመማር ከፍተኛ ፍላጎት ነበራቸው፡፡ ነገር ግን በተወለዱበት ጉራጌ ክፍለሀገር አማውቴ አካባቢ ትምህርት ቤት ባለመኖሩ የሚመኙትን ትምህርት ሳያገኙ የልጅነት ጊዜያቸው አለፈ፡፡ በዚህ በተፈጠረባቸው ቁጭት እና ከአምላክ በተቸራቸው የዓላማ ፅናት ትምህርት ቤት ለመመስረት ተነሱ፡፡ ተሳክቶላቸውም ከ1ኛ እስከ 6ኛ ክፍል አስጀመሩ፡፡ በ1964 ዓ.ም፡፡
ምን ይሄ ብቻ መንደራቸውን ከዋና መንገድ የሚያገኛኝ የ20 ኪ.ሜ የጥርጊያ መንገድ አሰሩ፡፡
በንግዱ ዓለምም ከሁለት ብር መርፌ ንግድ ተነስተው የትላልቅ የንግድ መደብሮች እና የሆቴሎች ባለቤት ለመሆን በቁ፡፡ ከገነቧቸው ሆቴሎች መርካቶ የሚገኘው “አስፋውወሰን ሆቴል” ይጠቀሳል፡፡ በዚህ ስኬታማ ስራቸው በወቅቱ የነበሩ ነጋዴዎች “በለጠች” በሚል ቅጽል ስም እንዳወጡላቸው መረጃዎች ያስረዳሉ፡፡
በቀደማዊ ኃይለ ስላሴ ዘመነ መንግስት በበጎ ስራቸው የሚታወቁ ሴት ስራ ፈጣሪ እና ባለፀጋ ነበሩ፡፡ በታታሪነታቸውም ልዩ ሽልማት አግኝተዋል፡፡
እነዚህ ድንቅ ስራዎቻቸው ለህዝብ አሸጋግረው በተወለዱ በዘጠና ዓመታቸው በ1992 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ፡፡
በጊስት ዘምዘም የተመሰረተው ትምህርት ቤት ከ30 ዓመታት በኋላ በአካባቢው ተወላጆች ጥረት ሁለት ክፍሎችን ጨምሮ እስከ እስከ ስምንት አደገ፤ ቀጥሎም በቅርቡ ወደ ሃይስኩል ከፍ አለ፡፡ አሁን ደግሞ 11 እና 12ኛ ክፍል ለማስጀመር ጥቅምት 29/2013 ዓ.ም ቀን ተቆርጦለታል፡፡ እማሆይ ዘምዘም ዕድሜ ሰጥቷቸው የመሰረቱት ትምህርት ቤት እዚህ ደረጃ ላይ ደርሶ ቢያዩት ምኞቴ ነበር፡፡ አለመታደል ሆኖ ይህንን ለማየት አልታደሉም፡፡
ከትምህርት ባሻገር እማሆይ ዘምዘም ስማቸው በስፋት የሚነሳው ከእንሰት ጋር ተያይዞ ነው፡፡ በወቅቱ የነበሩ የመንግስት ባለስልጣናት እንሰትን በግብታዊ ውሳኔ ሊያጠፉት ሲነሱ “ይሄማ እንዴት ይሆናል“ ብለው የባለስልጣናቱን እንሰት የማጥፋት ሃሳብ አሳምነው ያስቀየሩ ስመጥር ሰው ናቸው፡፡
እኚህ ብዙ ያልተነገረላቸው እማሆይ ግለ-ታሪካቸው ለሌሎች አስተማሪ እና አነሳሽ በመሆኑ በፕሮግራም ወይም በዶክመንታሪ መልክ መስራት የምትፈልጉ የሚዲያ ባለሙያዎች ብታናግሩን እና ብንተጋገዝ መልካም ነው፡፡
ከ48 ዓመታት በፊት በአንድ ሰው ይህ ሁሉ ከተሰራ ከተባብረን ምን እንደምንሰራ መገመት አያዳግትም፡፡ በዚሁ አጋጣሚ እማሆይ ለመሰረቱት ትምህርት ቤት መፃህፍት የመስጠት ፍላጎቱ ያላችሁ የቀድሞ ተማሪዎችና ይህን በጎ ዓላማ መደግፍ የምትፈልጉ ወዳጆች በሙሉ በውስጥ መስመር አናግሩኝ በተቀናጀ ሁኔታ ለማገዝ አንዳንድ ስራዎችን ጀምረናል፡፡
እማሆይ ይህን ትምህርት ቤት ባይመሰርቱት አሁን ያለሁበት ደረጀ መድረስ እስል ነበረ ወይ?! ማሰብ አልፈልግም ብቻ እንኳንም መሰረቱት፡፡
አርአያ የሆኑ መንፈሰ ጠንካራ ሴት የመሰረቱት ትምህርት ቤት በመማሬ እድለኛ እንደሆንኩ ይሰማኛል፡፡
ጋሻው ታደሰ ነው ያቀረበው


ባህላችን ለዓለም እናሰተዋውቅ!
ቅርሶቻችን በአንድነት እንጠብቅ!

አዳብና  መልቲ ሚዲያ Telegram ሊንኩን በመንካት ይቀላቀሉ። https://t.me/Adabnamidea

አዳብና You tube like share subscribers
በማድረግ ግዴታችን እንወጣ።

አዳብና ሚዲያ ዩቱብ https://youtube.com/channel/UCbihhwTdI6hy-e7Kj6T_J8g
415 viewsedited  10:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-01 13:16:21
ባህላችን ለዓለም እናሰተዋውቅ!
ቅርሶቻችን በአንድነት እንጠብቅ!

አዳብና  መልቲ ሚዲያ Telegram ሊንኩን በመንካት ይቀላቀሉ። https://t.me/Adabnamidea

አዳብና You tube like share subscribers
በማድረግ ግዴታችን እንወጣ።

አዳብና ሚዲያ ዩቱብ https://youtube.com/channel/UCbihhwTdI6hy-e7Kj6T_J8g
334 viewsedited  10:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-01 02:00:53 አንድ ደራሲ ሊመዘግብ የሚችለው በዓይኑ የተመለከተውን ፥ የሰማውን ፥ ገጠመኙንና በነበረበት ዘመን ተከብረውና ታፍረው ወይም ተነቅፈው የነበሩትን ሁኔታዎች መሆኑ አይካድም። አዘጋጂው የደራሲውን አመለካከት እንዳለ በመቀበል አንዳንዱ ነገር ሳይንሳዊ አይደለም ይህኛው ቢጨመር ያኛው ቢቀነስ ለማለት አልፈለገም። በጽሑፉ አቀማመጥና በአርዕስቶች ቅደም ተከተል በኩል ግን መጠነኛ ለውጥ አድርጓል።

መጽሐፉ በስድ ንባብ ፥ በግጥም በአማርኛና በክስታኒኛ ቋንቋዎች ተጽፏል። ሁለቱንም ቋንቋዎች የሚያውቅ አንባቢ የደራሲውን የቋንቋ ጥራትና የሥነ-ጽሑፉንም ውበት ለመገምገም ከመቻሉም ባሻገር ፥ ከሁለቱም ክፍል በማውጣጣት ስለ አይመለል ክስታኔ ሕዝብ ማንነት የበለጠ ዕውቀት ለመቅሰም ሰፊ ዕድል ይኖረዋል።

ሰነፎችን ለማረሚያና ትጉሀንን ለማበረታቻ በአጠቃላይ የሰዎችን ዓለማዊና መንፈሳዊ ሕይወትን የሚዳስሱት የደራሲው የክስታኔ መጣፍ (ምክር አዘል ጽሑፍ) እንዳለ የገባ ሲሆን ፥ በአማርኛና በክስታኒኛ የተዘጋጁት ግጥሞች ብዙ ስለነበሩ ለጊዜው ጥቂቶቹ እንዲካተቱ ተደርጓል። የቀሩት በጅምር ላይ ካሉት የደራሲው ጽሑፎች ጋር ተቀነባብረው ለወደፊቱ የሚቀርቡ ናቸው።

ደራሲው አቶ ተስፋ ገብረየስ ይህን የታሪክ ፥ የባህል ፥ የቋንቋ ፥ የማህበረሰብ ወግና ሥርዓት እንዲሁም የሥነ ጽሑፍ መዘክር መዝግበው “የታሪክ ማስታወሻ” እንዲሆን ያቀረቡበትን ምክንያት እንዲህ ሲሉ ገልጸውታል።

“ምንጊዜም ሰው እንደ ፍሬ ከዛፍ ፥ እንደ ጠጠር ከወንዝ የተለቀመ አይደለም ፤ የወጣበት ሀገር ፥ የወረደበት ሀረግ ይኖረዋል። ዘር አይፋቅም ፥ ሥራ አይናቅም። መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጊዜና ዕድል እንደመራው በምሥራቅና በምዕራብ ፥ በሰሜንና በደቡብ በያዘው መሬት ሰፍሮ የተራራቀ ቢመስልም ፥ በሥራና በአኗኗር ሂደት ከሥፍራ ወደ ሥፍራ እየተዘዋወረ በመኖር እርስ በርሱ እየተቀላቀለ በዘር የተደባለቀ መሆኑን በታሪክ ከሚነገረውም በላይ በአኳኋኑ ሁሉ መረዳት ይቻላል።

ይሁን እንጂ ማንኛውም ጐሣ ሆነ ግለሰብ ከየት እንደመጣና ከማን እንደ ተወለደ ለማወቅ የራሴ ነው የሚለውን ኅብረተሰብ ቋንቋና ባህሉ ፥ የአኗኗር ስልትና ልማድ ተከትሎ ማንነቱን አውቆ ለመጠበቅና ለሚቀጥለው ትውልድ ለማስተላለፍ ከፍተኛ ፍላጐት እንዳለው የታወቀ ነው። ይህ የአይመለል ጉራጌ (ሶዶ ጐርደና) አጭር የታሪክ ማስታወሻ የተዘጋጀው የተጠቀሰውን ፍላጐት እንደ ሚያሟላ በማሰብ ነው። በመሆኑም የክፍሉ ተወላጅ የሆነ ሁሉ ህልውናውንና ማንነቱን የሚያረጋግጥበትን ታሪኩን እንዲያውቅ ይህቺን አጭር የታሪክ ማስታወሻ እንዲያነብና ባህሉን አዳብሮ ለመጭው ትውልድ እንዲያስተላልፍ አደራዬ የጠበቀ ነው።”

ሁኔታዎች ለትምህርት ፣ ለምርምርና ለደራሲነት ሙያ ምቹ ባልነበሩበት ወቅት ተወልደው በኖሩበት ጊዜ ውስጥ ከፈጣሪያቸው በተሰጣቸው የዕውቀት ብርሃን ተመርተው ከፍ ባለ ትጋትና አስተዋይነት ያከናወኑዋ ቸውና በጅምር ላይ ያሉት መንፈሳዊና ዓለማዊ ድርሰቶች የደራሲውን የአቶ ተስፋን ምሁርነትና ታላቅነት የሚያረጋግጡ ሆነው እናገኛቸዋለን።

ይህ መጽሐፋቸውም የዛሬውም ሆነ የወደፊት የሶዶ ጐርደና ወጣቶች በየትምህርት ቤታቸው ቀርቦላቸው ቢያነቡት ከሥር መነሻው ዕውነተኛውን የትውልድ ሀገራቸውን ታሪክና ባህል ለማወቅ እንደሚ ረዳቸው ይታመናል።

በመጨረሻም ኢትዮጵያ ከኢጣሊያ ፋሽስት የጭካኔ አገዛዝ ተላቃ ነጻነትዋን ካገኘች በኋላ የሶዶ ጐርደና ተወላጆች የዘመኑን ሥልጣኔ ተከትለው የትውልድ ሀገራቸውን ለማልማት ያደረጉትን ጥረት ባጭሩ የሚያስገነዝብ መግለጫ በእኔ ተዘጋጅቶ በአማርኛው ክፍል መጨረሻ ላይ “ተጨማሪ - ሶዶ ጐርደና ክስታኔ / በልማት ላይ” በሚል ርዕስ ቀርብዋል። የዚህም ማብራሪያ ዋና ዓላማ አቶ ተስፋ በጽሑፋቸው የገለጹት የሶዶ ጐርደና ሕዝብ ታታሪነትና የትውልድ ሀገሩን ለማልማት የሚያደርገው ያላሰለሰ ጥረት በተግባር ላይ እየታየ መሆኑን ለማስረዳት ሲሆን በተጨማሪም በመካሄድ ላይ ያለው የልማት እንቅስቃሴ በተጠናከረ መልኩ እንዲቀጥል ለማበረታታት ነው።

የመጽሐፉ አዘጋጅ ወርቁ ተሥፋ ገብረየስ - ግንቦት 1987 ዓ.ም.

‖ ‖፧፨፧‖ ‖‡∺∺∺‡‖ ‖፧፨፧‖ ‖
‖፧፠፧‖ MULER Design & Art - Photographer MULER ‖፧፠፧‖
152 views23:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-01 02:00:53 ‖※‖፧፠፨፠፧‖ ▬ አ ይ መ ለ ል ▬ ‖፧፠፨፠፧‖※‖

ደራሲ፦ ተሥፋ ገብረየስ ዘምድረ-ከብድ
አዘጋጅ፦ ወርቁ ተሥፋ
አርትዖት፦ ነጋሽ ገብረማርያም /ጋዜጠኛ/

የአይመለልን (ሶዶ ጐርደና) ብሔረሰብ ባህልና ታሪክ የሚመለከት መግለጫ በሚዘጋጅበት ወቅት ከሁሉ አስቀድሞ የታሪኩ ምንጭ የሆኑት ቃላት ማለት አይመለል ፥ ጉራጌ ሶዶ ፥ ክስታኔ ፥ ጐርደና ምንን እንደሚያመለክቱና ግንኙነታቸው ምን እንደሆነ መረዳት ጠቃሚ ይሆናል።

ከታሪክ እንደምንረዳው አይመለል በደቡብ ኢትዮጵያ የአዋሽን ወንዝ ተሻግሮ ከሰሜን ወደ ደቡብ መሀከሉ እንደ ሠንሠለት በተያያዘ ተራራ አገምግሞ የሚታየውና ከደጋው ቀጥሎ ወይናደጋው ከዚያም ቆላው በተዋረድ በእንሰት ልምላሜ አሸብርቆ የተንጣለለው ሀገር ነበር። ይህ ሀገር በአሁኑ አጠራር ሶዶ አውራጃ በመባል ይታወቃል። ዛሬም ቢሆን ታሪክን የምታስታውሰን አይመለል ተብላ የምትጠራ ትንሽ አምባ በሶዶ ጐርደና ከደጋው ላይ ትገኛለች።

ጉራጌ ማለትም የጉርዓ ሰዎች ሰብአ ጉራጌ ማለት ነው። ይኸም ጥንተ-ስሙ ጉራዕ ሲሆን ጐንደር ብሎ ጐንደሬ ፥ ወሎ ብሎ ወሎዬ እንደሚባለው ሁሉ ጉራዕ ብሎ ጉራዕጌ ተባለ። ዛሬ ሶዶ ጐርደና በመባል የሚታወቀውን ወረዳ የሚያቅፈው ሰፊ ሀገር የጉራጌ ነገድ ወደዚህ ክፍል ከመምጣቱ በፊት አይመለል ተብሎ ይጠራ ነበር። ይኽንንም ታሪክ የጉርዓ ሰዎች ከጉርዓ ተነስተው በአይመለል ተሠሩ በማለቱ መረዳት ይቻላል። ጉራጌ የነገዱ ስም ሲሆን ፥ አይመለል የሀገሩ ስም ነው። ከረጅም ጊዜ ጀምረው በአይመለል የሚኖሩት ሕዝቦች ክስታኔ ተብለው ይጠራሉ። ክስታኔ ማለትም “ክርስቶስን የተቀበለ ፥ ክርስቲያን” ማለት ነው።

የአይመለል መሬት ቅድመ-ሥሪቱ የጉራጌ ቢሆንም ከግራኝ ወረራና ከዚያም በፊት በተለያየ ጊዜ ከተለያዩ አቅጣጫዎችና ሀገሮች እየፈለሱ ወደ ተጠቀሰው ሀገር እየገቡ ፥ የሰፈሩባቸውን ቀበሌዎች በጐሳዎቻቸው ግንድ አባቶች ስም እንዲጠሩ እያደረጉ በመኖር እስከ ዛሬ የሚገኙ ነገዶች ብዙዎች ናቸው ፥ ከነዚህም አንዱ ሶዶ የተባለው ነው።

ሶዶ የሚለው ቃል በአንድ በኩል የሀገር ስም ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ የነገድ ስም ነው። ሶዶ በምሥራቅና በሰሜን ከጂዳና ከአቡ ገላን ፥ በምዕራብ ከሜጫና ከበቾ እየተካለለ በጉራጌ ሰሜን ይገኛል። የሶዶ ብሔ ረሰብ ከነገደ ኦሮሞ የቦረና ልጅ ነው። አንዳንድ ታሪክ ሶዶን ከበርቱማ የወረንሻ ልጅ ያደርገዋል። የሶዶ ልጆች ግን ከቦረና የወረዱ የዳጪ ልጆች እንደሆኑ ይተርካሉ። ሰዴን ሶዶ ተብለውም ይጠራሉ። ይህም ሦስቱ ሶዶ ማለት ነው። እነሱም ቱምኤ ፥ ሊበንና ኦዲቱ ናቸው።

ጐርዶና ማለት በአንድ ዓይነት ወግና ሥርዓት የሚተዳደሩትን ኅብረተሰቦች የሚያቅፍ አንድነትን ፥ ሕብረትንና ጥንካሬን የሚያመለክት የጥቅል ስም ነው።
የአይመለልን (ሶዶ ጐርደና) ሕዝብ ታሪክ በምናነሳበት ወቅት በአጠቃላይ ስለ ጉራጌ ብሔረሰብ የተነገሩትንና የተጻፉትን ግንዛቤ ውስጥ ማስገባት ተገቢ ነው። ስለ ጉራጌ ብሔረሰብ ታሪክ ጥቂቶች ኢትዮጵያውያንና ቁጥራቸው በርከት ያለ የውጭ ሀገር ምሁራን ያሠፈሩት ጽሑፍ ይገኛል። አብዛኞቹ ደራሲያን ለሚጽፉት ታሪክ መነሻ ያደረጉት በሀገሩ ውስጥ ይገኙ ከነበሩት ሽማግሌዎች የሰበሰቡትን አፈ-ታሪክ ነው።

ስለ ጉራጌ ብሔረሰብ ታሪክ ከጻፉት ደራሲያን መካከል አለቃ ታዬ ፥ አቶ ሰይፉ ድባቤንና እንዲሁም ሌሎችንም ኢትዮጵያውያን ለአብነት ያህል መጥቀስ ይቻላል። ከውጭ ሀገር ደራሲያን መካከል በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ ስለ ጉራጌ ሕዝብ ማንነት የጻፉት ጥቂቶች አይደሉም። በኪንግሃምና ሐንቲንግ ፎርድ ፥ ፊልፕ ሌብል ፥ እርነስት ኦግስትጋት ፥ ዊሊያም ሻክና ሌሎችም እንደ ኮንት ሮሲኒ ያሉት ምሁራን መጥቀስ እንችላለን። ውልፍ ሌስሎ ፥ ማርጆሪ ፔርሃምና ሌሎችም በአጭሩ ጠቅሰውታል።

የአይመለል ጉራጌ ታሪክ በጉራጌ ሕዝብ ታሪክ ውስጥ የታቀፈ ቢሆንም የራሱ የሆነ የተለየ ታሪክ አለው። ከዚህ በላይ እንደ ተመለከተው አንዱ ደራሲ የሚጽፈው ሌላውን በመጥቀስ መሆኑ ባይካድም አብዛኞቹ ደራሲያን የሚስማሙበት አንድ አቢይ የሆነ ነጥብ አለ ይኸውም በ1327 ዓ.ም. ገደማ በዓፄ አምደ ጽዮን ዘመነ-መንግሥት በአዝማች ስብሀት መሪነት ከአካለ ጉዛይ አውራጃ ከጉራዕ ቀበሌ የተንቀሳቀሰ የንጉሡ ጦር አይመለል በተባለው ሥፍራ እንደሠፈረ የሚተርከውን ታሪክ ነው።

ከዓፄ ኢያሱ አድያም ሰገድ እስከ ንጉሥ ሣህለ ሥላሴ መንግሥት በነበረው ዘመን የነገሥታቱ ኃይል እየተዳከመና ከሕዝቡ እየራቀ በመሄዱ በአካባቢው ሰላምና ጸጥታ ታጥቶ ነበር። ሕዝቡም ከየጐሣው አማካሪ መርጦ በእነዚህ አማካሪዎች አማካይነት አዝማቾች ፥ አበጋዞች ፥ ዳኞች ሊቀ-ካህናቶች ፥ ቃዲዎች ለተወሰነ ጊዜ እየሾመ ራሱን በራሱ ሲያስተዳድር ኖሯል። በዚህ አካባቢ ሠላም የተገኘው ዓፄ ምኒልክ ኢትዮጵያን አንድ አድርገው በአካባቢው ሕግና ሥርዓት ከሰፈነ በኋላ መሆኑ የትናንት ታሪክ ነው።

ከንጉሥ ሣህለ ሥላሴ በተለይም ከዳግማዊ ምኒልክ ዘመነ መንግሥት ጀምሮ የአይመለል ጉራጌና ሶዶ በስም ፥ በጋብቻ ፥ በሃይማኖት ፥ በባህል ፥ በቋንቋ በመዋሃድ አንድ ሕዝብ በመሆኑ ለረጅም ጊዜ “ጉራጌ ሶዶ” “ሶዶ ጉራጌ” ተብሎ ሲጠራ ቆይቷል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሶዶ አውራጃ ተብሎ በአንድ ስም እንደሚጠራ ማስተዋል ያስፈልጋል።

የአይመለል ጉራጌ ብሔረሰብ ሁለት ቋንቋዎች ይናገራል። አብዛኛው ሕዝብ የሚናገረው ክስታኒኛ (የአይመለል ጉራጌኛ) ሲሆን ሁለተኛው ኦሮምኛ ነው። ክስታኒኛው ከአማርኛና ከግዕዝ የቅርብ ግንኙነት ያለው ሲሆን ቋንቋው የቃላት ስፋት ያለው በመሆኑ የአማርኛው ቃል በሚያጥርበት ጊዜ በክስታኒኛ ተብራርተው የሚገለጹ ጉዳዮች (ቃላት) መኖራቸው በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ተገልጿል።

ደራሲው አቶ ተስፋ ገብረየስ የዛሬ 50 ዓመት ገደማ የጻፉት ይህ መጽሐፍ የጉራጌን ሕዝብ ታሪክ በስፋትና በጥልቀት ለመግለጽ የተጻፈ በአንድ ርዕስ ላይ ያተኮረ መጽሐፍ አይደለም።
ይህ ሁለገብ የሆነ መጽሐፍ የጉራጌን ሕዝብ በተለይም የአይመለል ጉራጌን (ሶዶ ጐርደና) ሕዝብ ለአንባቢ የሚያስተዋውቀው በታሪኩ ላይ ብቻ በማተኮር ሳይሆን ፥ ባሕሉን ወጉን ፥ ሥርዓቱን ሃይማኖቱንና ቋን ቋውን ግንዛቤ እንዲያገኝ በማድረግ የጉራጌ ሕዝብ ማንነት ከአዲሱ ትውልድ ተሰውሮ እንዳይቀር ለማድረግም ጭምር ነው።

አቶ ተስፋ ገብረየስ በመንፈሣዊ ትምህርት የበሰሉና ለነበሩበት ዘመን ቀድመው የተፈጠሩ ምሁር በመሆናቸው ዘመን ተለውጦ ትውልድ ሲተካ ሊዘነጉ ይችላሉ ብለው ያሰቧቸውን የጉራጌን ሕዝብ የኢኮኖሚ ፥ የማህበራዊና የፖለቲካ ሕይወት በአጭር በአጭሩ አስቀምጠውታል።
ይህ መጽሐፍ ሳይታተም ቢዘገይም ፥ የተጻፈው ረዘም ካለ ጊዜ በፊት በመሆኑ የጂኦግራፊ ወሰኖች ፥ የሥፍራ ስሞች * የአነጋገር ፈሊጦች ተለውጠው ይሆናል። መጽሐፉ የደራሲውን ማንነትና የወቅቱን የአነጋገር ዘይቤ ፥ ወግና ሥርዓት እንዲፈነጥቅ ስለ ተፈለገ አዘጋጁ መሠረታዊ የሆኑትን ነገሮች ለማረም አልሞከረም። ቢሞከርም ችሎታው ላይኖር ይችላል።
138 views23:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-01 02:00:49
133 views23:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-30 12:07:06
ሚስ አዳብና
*
ማህበራችን የአዳብና በክስታኔ አዳብናንና የማህበረሰባችን ባህልና እሴት ለማስተዋወቅ የሚስ አዳብናን ሀሳብ በማመንጨትና ሙሉ ወጪው በመሸፈን እንዲሁም በማስተባበር ከእኛ ጋር መስራት ሌሎች አካላቶችንም በማካተት ለመጀመሪያ ጊዜ ሚስ አዳብና/የአዳብኒ መልካማ ከአዳብና ፌስቲቫል ጋር በማያያዝ እንዲካሄድ አድርጓል።

ማህበራችን ይሄንን የሚስ አዳብና ሀሳብ ሲያመነጭና በተግባር ላይ ሲያውለው ዋና ዓላማው አዳብናንና የማህበረሰባችንን ባህልና እሴት ማስዋወቅ ነው።

ማህበራችን የሚስ አዳብና ውድድር አጋዥ አካላቶችን በመጨመር በሰፊውና በልዩ ሁኔታ የሚሰራበትና ባህላችን ማስተዋወቁ የሚቀጥል ይሆናል።

በቅርቡም የ2016ዓ.ም የሚስ አዳብና ውድድር አካሄድና መስፈርቶች እንዲሁም እቅዶችን ኢፋ የምናደርግ ይሆናል።
326 views09:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-23 17:48:15
ልጆቻችን በሃገር አቀፍ ደረጃ አቢሲኒያ ባንክ አክሲዮን ማህበር አዲስ ዓመትን አስመልክቶ ባዘጋጀዉ ባህልን የማስተዋወቅ ውድድር ላይ በሺዎች ከሚቆጠሩ ተወዳዳሪዎች ጋር ተወዳድረው ባመጡት አመርቂ ውጤት እጅግ ኮርተናል።
ማህበራችን የአዳብና በክስታኔ ማህበርና አባላቱ ላደረግነው ጥቂት ድጋፍ የአቢሲኒያ ባንክና የውድድሩ ተሳታፊዎች ስላከበራቹን እንጅግ አርገን እናመሰግናለን ።

ባህላችን ለዓለም እናሰተዋውቅ!
ቅርሶቻችን በአንድነት እንጠብቅ!

አዳብና  መልቲ ሚዲያ Telegram ሊንኩን በመንካት ይቀላቀሉ። https://t.me/Adabnamidea

አዳብና You tube like share subscribers
በማድረግ ግዴታችን እንወጣ።

አዳብና ሚዲያ ዩቱብ https://youtube.com/channel/UCbihhwTdI6hy-e7Kj6T_J8g
678 views14:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-22 15:16:26
ምስጋናና ክብር ለአመራሮቻችን
ለሶዶ ወረዳ አስተዳዳሪ ደሱ አበጋዝ
ለደቡብ ሶዶ ወረዳ አስተዳዳሪ መሰለ ጫካ
ለቡኢ ከተማ ከንቲካ ይሽልጌታ በላይነ

የ2015 የአዳብና ፌስቲቫል ትኩረት ሰጥታቹት አዳብና ተመልሶ እንዲያንሰራራ አቅጣጫና አመራር በመስጠት ባህሉ በደመቀ መልኩ እንዲከበር ስላደረጋቹ እንዲሁም ከማህበራችን ጋር ቁጭ ብላቹ በመወያየት ባህሉ የሚከበርበት ምቹ ሁኔታ ስለፈጠራቹ ማህበራችን የአዳብና በክስታኔ ዓለም አቀፍ ወጣቶች ማህበር ትልቅ ክብር ምስጋና አለው።

በዚህ አጋጣሚ በቀጣይ አዳብና ከዚህ በተሻለ እንዲያንሰራራና በፌስቲቫል ደረጃ እንዲታወቅ እንዲሁም በማይዳሰስ የዓለም ቅርስነት እንዲመዘገብ በመንግስት በኩል በቂ ትኩረት ተሰጥቶት ከባለድርሻ አካላት ጋር ተቀናጅቶ በሰፊው እንዲሰራበት ምቹ ሁኔታዎችና ተናቦ መስራት እንደሚያስፈልግ እናምናለን።
650 views12:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-22 12:49:31
ልዩ ምስጋና #ለጉራጌ_ዞን_አስተዳደር_ፅ/ቤት

ለሰጣቹን ፈጣን ምላሽና እገዛ ማህበራችን የአዳብና በክስታኔ ዓለም አቀፍ ወጣቶች ማህበር ታላቅ ምስጋና ያቀርባል።
በተለይም የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ኢጂነር መሃመድ ጀማል ላሳዩን ቅንነትና ቀና ትብብር ምስጋናችን ወደር የለውም።
544 views09:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-12 12:39:49
ሚስ አዳብና ያዳብኒ መልካማ : ባህልን ጠባቂ፣ ታሪክን ጠያቂ፣ ጠይቆም ሚረዳ፣ ለቀጣይ ትውልድ የበኩሉን አላፊነት ሚወጣ ጠያቂ እና  ባህሉን ሳይለቅ የዘመነ ትውልድን የመፍጠር አላማን አንግቦ የተነሳ ትልቅና የሁሉም የኔነት ስሜት ሚፈልግ ሀሳብ ነዉ።

           ሚስ አዳብና ሌላው አላማው ከቤት የጀረውን ወደ አካባቢው ቀጥሎም ለሀገር እያለ ለአለም ይዞት ሚወጣው: ውብ ባህልን ፣ መገልገያ ቁሶችን፣ አልባሳትን፣ መዋቢያ ጌጣጌጦችን፣ ባጠቃላይ የአኑዋኑዋር ዘያችንን እና ግብረ ገብነትን ጨምሮ ያልጠቀስኳቸው ቱባ ባህል እና ታሪክን በአለም መድረክ ከፍ አድርገጎ ማሳየት ነው ።

      ብዙ ከራሳችን አልፈው አለምን እጁዋን በአፋዋ ሊያስጭን የሚችል ድንቅ እና በታሪክ ቀደምት የሆነ ብዙ ትውፊት አለን። ለዚህም ነው ባህላችንና ታሪካችን ለትውልድ ሳይደበዝዝ እንዲተላለፍ እንዲሁም ለአለም ተደራሽ እንዲሆን የድርሻችንን እንወጣ እያልኩ መልክቴን አስተላልፋለሁ።


ከሞዴል መነን ዳንኤል

ባህላችን ለዓለም እናሰተዋውቅ!
ቅርሶቻችን በአንድነት እንጠብቅ!

አዳብና  መልቲ ሚዲያ Telegram ሊንኩን በመንካት ይቀላቀሉ። https://t.me/Adabnamidea

አዳብና You tube like share subscribers
በማድረግ ባህላችንን  ቅርሶቻችንን እናሳድግ ።

አዳብና ሚዲያ ዩቱብ https://youtube.com/channel/UCbihhwTdI6hy-e7Kj6T_J8g
320 views09:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ