2022-10-07 14:36:21
መስከረም 27/2015 ዓ.ም
በከተማው ውስጥ የቱሪዝም አገልግሎት ሰጪ ተቋማት መገንባት ለዘላቂ የቱሪዝም ልማት ትልቅ ሚና እንደሚኖረው ተገለጸ።
በቡኢ ከተማ ላይ በአርቲስት ጸጋዬ ሲሜ የተገነባው" ኦሴባሳ ጥላ "ሆቴል መስከረም 28/2015 ዓ.ም ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት እንደሚሆን ተጠቁሟል።
የቡኢ ከተማ አስተዳደር ባህል እና ቱሪዝም ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተሻለ ነገሰ በከተማው ውስጥ እንደዚህ ዓይነት የቱሪስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት መገንባት ለዘላቂ የቱሪዝም ልማት እና ሥራ ዕድል ፈጠራ ትልቅ ሚና እንዳላቸው ተናግረዋል።
በአካባቢያችን ካለው እምቅ የቱሪዝም ሀብት አኳያ የዘርፉ አስተዋጽኦ ሲታይ አመርቂ እንዳልሆነ እና ለዚህም ምክንያቱ የቱሪስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ጥራት እና ብዛት በሚፈለገው ልክ ያለመሆኑ እንደሆነ አብራርተዋል።
ጽ/ቤቱ እየጨመረ የመጣውን የቱሪስት ቁጥር ለማስተናገድ እና የአገልግሎት ጥራት ለማጎልበት ለአገልግሎት ሰጪ ተቋማቱ ልዩ ልዩ የድጋፍ ሥራዎች እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
አሁን በከተማችን በአርቲስት ጸጋዬ ሲሜ የተገነባው" ኦሴባሳ ጥላ "ሆቴል እንደ ሀገር እየተነቃቃ ለመጣውን የዘርፉ እንቅስቃሴ ከፍተኛ አስተዋጽዖ ይኖረዋል ብለዋል።
ወደ ከተማው መጥተው በዘርፉ ለመሠማራት ለሚፈልጉ ሌሎች ባለሀብቶች እንደ መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚደረግላቸው ገልጸዋል።
የሆቴሉ ባለቤት አርቲስት ጸጋዬ ሲሜ የሆቴሉ ግንባታ ከተጀመረ ረጅም ጊዜ እንደሆነ የገለጸ ሲሆን ለዚህም ምክንያቱ በሙያው ላይ እራሱ እንደተሳተፈበት እና ያለው የገበያ ሁኔታ እንደሆነ ገልጽዋል።
ሆቴሉ ለሥራ አጥ ዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር ረገድም ትልቅ ፋይዳ እንደሚኖረው እና ከ30 በላይ ሠራተኞች እንደሚኖሩት ተመላክቷል። የመኝታ ፣የመዝናኛ እና የሆቴል አገልግሎት እንደሚሰጥ ተገልጿል።
እንደ ቡኢ ከተማ ብዙ የእንግዳ ማረፊያ ባለመኖሩ እና ችግር ለመቅረፍ የበኩሉን አስተዋጽዖ ለማበከተ በማሰብ በዘርፉ ትኩረት እንዳደረገ እና የተሻለ ነገር ለመስራት እንደሞከረ አብራርቷዋል።
ከተማዋ እጅግ ሰላማዊ እንደሆነች እና እስከ ዛሬ ድረስ ምንም ዓይነት የጽጥታ ችግር እንዳላገጠመው እና ለዚህም የከተማው ማህበረሰብ እና ፖሊስ ትልቅ ምስጋና አቅርበዋል።
ለሌሎች ባለሀብቶች እና የአካባቢው ተወላጆች በዚች እጅግ ሰላማዊ በሆነች ከተማ እንደ እኔ ኑና ኢንቨስት በማድረግ በጋራ እናልማት ሲሉ አርቲስት ጸጋዬ ሲሜ ጥሪውን አስተላልፏል።
መረጃው የቡኢ ከተማ አስተዳደር ነው
አዳብና መልቲ ሚዲያ Telegram ሊንኩን በመንካት ይቀላቀሉ። https://t.me/Adabnamidea
አዳብና You tube like share subscribers
በማድረግ ባህላችንን ቅርሶቻችንን እናሳድግ ።
አዳብና ሚዲያ ዩቱብ https://youtube.com/channel/UCbihhwTdI6hy-e7Kj6T_J8g
309 views11:36