2022-08-02 21:11:21
ሐምሌ26/2014 ዓ.ም
================
በጉራጌ ዞን የቡኢ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሚዩኒኬሽ ጉዳዮች ጽ/ቤት የከተማው ህብረተሰብ የንባብ ባህል ለማጠናከርና ማንባብ እየፈለጉ መጽሐፍትን በቀላሉ ማግኘት የማይችሉ አንባብያን ችግር ለመቅረፍ የመጽሐፍት ውሰት አገልግሎት መጀመሩን አስታወቀ።
ከተለያዩ ግለሰቦችና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች ባሰባሰብናቸው መጽሐፍቶች በቋሚነት ብዙ የንባብ ደንቦኞችን መፍጠር ችለዋል። ይህ ሁኔታ የበለጠ እንድንሰራ ስንቅ ሆኖናል።
በትምህርት ገበታ ላይ የነበራችሁ ተማሪዎች የእረፍት ጊዜ በመሆኑ ጊዜያችሁን በንባብ ታሳልፉ ዘንድ ጽ/ቤታችን ውስጥ ከ300 በላይ የተለያየ ይዘት ያላቸው የታሪክ፣ የፍልስፍና የሳይኮሎጂና ልብ ወለድ መፅሃፍቶች ስላሉን በውሰት ወስዳችሁ ማንበብ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።
አድራሻ፦ ከዋርካው ጀርባ በሚገኘው የመሰብሰቢያ አዳራሽ ግቢ ያለ ቢሮ ውስጥ ዘወትር ከሰኞ እስከ አርብ ያገኙናል።
ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል!!
የቡኢ ከተማ አስተዳድር መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት
379 viewsዘፀአት የዘጌ ገቾ, 18:11