Get Mystery Box with random crypto!

አዳብና መልቲ ሚዲያ

የቴሌግራም ቻናል አርማ adabnamidea — አዳብና መልቲ ሚዲያ
የቴሌግራም ቻናል አርማ adabnamidea — አዳብና መልቲ ሚዲያ
የሰርጥ አድራሻ: @adabnamidea
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 817

Ratings & Reviews

1.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2022-12-04 10:49:48
ሚስ ዪምር ዪምር ቀጣዩ ፕሮግራማችን ነው።
**
ማህበራችን የአዳብና በክስታኔ ዓለም አቀፍ ወጣቶች ማህበር ድንቅ ፣ጥንታዊ ከሆነውና ከገና በዓል ጋር ተያይዞ በልጃገረዶች የሚከበረው የዪምር-ዪምር ባህል ለማስተዋወቅ ሰፊ ፕሮጀክት ነድፎ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል።

ማህበራችን ለገና በዓል ከያዛቸው ፕሮግራሞች መካከል
ሚስ ዪምር-ዪምር ባህላዊ የቁንጅና ውድድር
ልዩ የገና ፌስቲቫል:-ዪምር ዪምር፣እንዞሪቴ፣የገና ጫወታ(አንቃት)ና የፈረስ ጉግስ ያካተተ ፕሮግራም
የገና የቴሌቪዥን ዶክመንተሪ ፊልም የሚጠቀሱ ናቸው።

ለሚስ ዪምር ዪምር መወዳደር የምትፈልጉ ከነገ ህዳር 16 ጀምሮ ምዝገባ ይጀምራል።

የውድድር ዘርፎች

1ኛ:-በአካል መድረክ ላይና ከመድረክ ውጪ በሚዘጋጁ ውድድሮች በመሳተፍ ዪምርዪምርን ማሳየት
2ኛ :-በቡድን በመሆን በቪዲዮና በፎቶ ዪምር ዪምርን መግለፅ
3ኛ :-ባሉበት ቦታ በፎቶ መወዳደር
4ኛ:-ለተወዳዳሪዎች የባህላዊ ልብስ ዲዛይ ውድድር


የምዝገባ መስፈርቶች
ማንኛው ፍላጎት ያለውና ባህሉን ጠንቅቆ ማሳየት የሚችል
በአካል ለምትወዳደሩ ቁመት 1.5m በላይ
ለሁሉም ተወዳደሪዎች ዕድሜ ከ30 ዓመት በታች

የምዝገባ ጊዜ ከህዳር 15-ህዳር 30

የየዘርፉ አሸናፊዎች ዳጎስ ያለ ሽልማት ይጠብቃቸዋል።

ስልክ ቁጥር
0910186703
0910337765
341 views07:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-04 10:49:30 ሚስ ዪምር ዪምር ቀጣዩ ፕሮግራማችን ነው።
**
ማህበራችን የአዳብና በክስታኔ ዓለም አቀፍ ወጣቶች ማህበር ድንቅ ፣ጥንታዊ ከሆነውና ከገና በዓል ጋር ተያይዞ በልጃገረዶች የሚከበረው የዪምር-ዪምር ባህል ለማስተዋወቅ ሰፊ ፕሮጀክት ነድፎ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል።

ማህበራችን ለገና በዓል ከያዛቸው ፕሮግራሞች መካከል
ሚስ ዪምር-ዪምር ባህላዊ የቁንጅና ውድድር
ልዩ የገና ፌስቲቫል:-ዪምር ዪምር፣እንዞሪቴ፣የገና ጫወታ(አንቃት)ና የፈረስ ጉግስ ያካተተ ፕሮግራም
የገና የቴሌቪዥን ዶክመንተሪ ፊልም የሚጠቀሱ ናቸው።

ለሚስ ዪምር ዪምር መወዳደር የምትፈልጉ ከነገ ህዳር 16 ጀምሮ ምዝገባ ይጀምራል።

የውድድር ዘርፎች

1ኛ:-በአካል መድረክ ላይና ከመድረክ ውጪ በሚዘጋጁ ውድድሮች በመሳተፍ ዪምርዪምርን ማሳየት
2ኛ :-በቡድን በመሆን በቪዲዮና በፎቶ ዪምር ዪምርን መግለፅ
3ኛ :-ባሉበት ቦታ በፎቶ መወዳደር
4ኛ:-ለተወዳዳሪዎች የባህላዊ ልብስ ዲዛይ ውድድር


የምዝገባ መስፈርቶች
ማንኛው ፍላጎት ያለውና ባህሉን ጠንቅቆ ማሳየት የሚችል
በአካል ለምትወዳደሩ ቁመት 1.5m በላይ
ለሁሉም ተወዳደሪዎች ዕድሜ ከ30 ዓመት በታች

የምዝገባ ጊዜ ከህዳር 15-ህዳር 30

የየዘርፉ አሸናፊዎች ዳጎስ ያለ ሽልማት ይጠብቃቸዋል።

ስልክ ቁጥር
0910186703
0910337765
345 views07:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-03 12:31:26 ለጓደኞቹ፣ ለስራ ባልደረቦቹ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹና ለቤተሰቦቹ መፅናናትን እንመኛለን።
==
# አዳብና በክስታኔ ዓለም አቀፍ ወጣቶች ማህበር

ዜና እርፍት

ወጣት ኢንጂነር ይስሃቅ ታደሰ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

ወጣት ይስሃቅ ከአባቱ አቶ ታደሰ ገለቱ ከእናቱ ወ/ሮ ፈለቀች መገርሳ በ1980 ዓ.ም ቡኢ ከተማ ውስጥ ተወለደ። ዕድሜው ለትምህርት ሲደርስ የ1ኛ ደረጃ ትምህርቱን በቡኢ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የሁለተኛ ደረጃና መስናዶ ትምህርቱን በሶዶ ቡኢ ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ከተከታተለ በኃላ ከፍተኛ ውጤት በማምጣት በአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ በሜካኒካል ኢንጂነሪንግ የትምህርት መስክ የከፍተኛ ትምህርቱን ተከታትሏል።

ወጣት ይስሃቅ የከፍተኛ ትምህርቱን በከፍተኛ ውጤት በማዕረግ ካጠናቀቀ በኋላ በኢትዮጵያ መርከብ ትራንስፖርት ድርጅት በመቀጠር አገሩን አገልግሎዋል። ባጋጠመው የጤና ዕክል ድርጅቱን በመልቀቅ ወደተውለደበት አካባቢ በመመለስ በቡኢ ከተማ አስተዳደር መንገድ ትራንስፖርት ፅ/ቤት በአሽከርካሪ ተሽከርካሪ ፍቃድ ማረጋገጫ ዋና ስራ ሂደት የአሽከርካሪ ፍቃድ ማረጋገጥ ባለሙያ በመሆን ህይወቱ እስካለፈበት ድረስ በቅንነት ሲያገለግል ነበር።

ወጣት ይስሃቅ ከአለማዊ ህይወቱ በተጨማሪ በመንፈሳዊ ህይውቱም በቡኢ ደብረ ሰላም ቅዱስ ባለወልድ ቤተክርስቲያን ከልጅነቱ ጀምሮ ቤተክርስቲያኒቱን በድቁና አገልግሎዋል።

ወጣት ይስሃቅ በትምህርቱ እጅግ የተዋጣለት በባህሪው ሰው አክባሪ በስራው ትጉህና ታታሪ ወጣት ነበር።

ወጣት ኢንጂነር ይስሃቅ ታደሰ በቀን 22/03/2015 ዓ.ም ባጋጠመው ድንገተኛ ህመም ህይወቱ አልፎዋል። የቀብር ስነ ስርዓቱም በቡኢ ደብረ ሰላም ቅዱስ ባለወልድ ቤተክርስቲያ በቀን 24/03/2015 ዓ.ም በዕርገት ይፈፀማል።

የቡኢ ከተማ አስተዳደር በወጣት ኢንጂነር ይስሃቅ ታደሰ ህይወት እልፈት የተሰማውን ጥልቅ ሃዘን እየገለፀ ለጓደኞቹ፣ ለስራ ባልደረቦቹ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹና ለቤተሰቦቹ መፅናናትን ይመኛል።
468 views09:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-03 12:31:23
436 views09:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-01 21:01:17
ጆሎምባ
ቆራንቲ
ጄነቶ
ሻሜ
ኩኩታ
ዚህ  ኣምስቲ ምን ቃይ ነኸም ?  ለምንሽ የክስታኔ ጉራጌ ማህበረሰብ ዪገለገልቦት ?
577 views18:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-01 06:29:34
ቀን 21-03-2015 ዓ.ም

የሶዶ ወረዳ ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ጽ/ቤት የተሻለ አፈፃፀም በማስመዝገብ ከዞኑ 1ኛ ደረጃ በመውጣት የዋንጫና ሰርተፍኬት ተሸላሚ ሆነ።

የማህበረሰብና የተቋም የዲጂታልቴክኖሎጂ ተጠቃሚነትን በማረጋገጥ የተሻለ አፈፃፀም በማስመዝገብ ውጤቱ ማምጣት እንደታቻለ ተገልጿል።

የሶዶ ወረዳ ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አዳነ ተሰማ እንደተናገሩት ምቹ የምርምር የፈጠራና ስነ ምህዳር በመፍጠርና በት/ቤቶች በመስራት የዲጂታል ቴክኖሎጂ አገልግሎት አጠቃቀምና አቅርቦት ለተቋማት በማሳደግ ውጤታማ መሆናቸውን አስታውቀዋል።

አክለውም አቶ አዳነ ተሰማ እንዳመላከቱት ውጤታማ የሆኑ የቴክኖሎጂ ሀርድዌሮችና ሶፍትዌሮችን ተደራሽነትን በማላቅና የካይዘን አሰራርን በመተግበር ምቹ የስራ ቦታ በመፍጠር የ2014 ዓ.ም ተሸላሚ መሆን ችለናል ብለዋል።

በቀጣይም የመረጃ ችግሮችን ለመቅረፍ ወረዳዊ ዌብሳይት ለማልማት ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ አስታውቀው ለዚህ ውጤት መምጣት ትልቅ አስተዋጽኦ ላበረከቱት ለወረዳው አስተዳደርና ባለ ድርሻ አካላት እንዲሁም ሲተጉ ለነበሩት ለጽ/ቤቱ ሰራተኞች ምስጋና ማቅረባቸውን የዘገበው የሶዶ በረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።
554 views03:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-01 06:24:07
ገና ዪምር ዪምር ክፍል፪ በተስፉ አበበ https://www.tiktok.com/@tesfu2almaz?_t=8Xms533ny6M&_r=1
506 views03:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-28 19:35:08
የ"ዪምር ዪምር" ቱሁፊታዊ አመጣጥ
ሙሉውን በአዳብና ሚዲያ በዩቱብ ቻናል ይመልከቱ።



214 views16:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-28 11:44:55 የገና አከባበርና ትውፊታዊ ክንውኖች በክስታኔ ቤተ-ጉራጌ (ሶዶ ጉራጌ)
*****
ክፍል አንድ(በዘፀአት ቱቼ)
*

የክስታኔ ማህበረሰብ ገና እንዴት እንደሚከብርና ሃይማኖታዊ ትውፊቱና ባህላዊ ዳራው ለመተንተን ከመሞከራችን በፊት ስለማህበረሰብ ስያሜና ማንነት በጥቂቱ መጥቀሱ እጅግ በጣም ጠቃሚ ነገር ይሆናል።ከስያሜው ስንነሳ ክስታኔ ማለት ክርስቲያን ማለት ሲሆን በዓለም ህዝብ በክርስቶስ ስም የሚጠራ ብቸኛ ህዝብም ጭምር ነው።
የክስታኔ ማህበረሰብ ክስታኔተብሎ ከመጠራቱ በፊት አይመለል ተብሎም ተጠርቷል።አይመለል ማለት የማይደፈር የታፈረ አማኝ ህዝብ ማለት ነው።ክስታኔና አይመለል በሚሉት ቃላቶች መካከል ይሄን ያህል የትርጉም ልዩነትም የላቸውም(ክስታኔ =ክርስቲያን =አይመለል =አማኝ)
የክስታኔ ማህበረሰብ ልክ እንደስያሜው በአብዛኛው የክርስትና እምነት ተከታይ ሲሆን ባህሉና አኗኗሩም ከክርስትና ሃይማኖት ጋር እጅግ በጣም ጥብቅ ቁርኝት ያለው ነው።በመሆኑም የክስታኔ ማህበረሰብ ባህልና ማንነት ጠለቅ ብለን ስንመረምርና ስናጠና በአብዛኛው ከክርስትና ሃይማኖት ትውፊት ጋር ተያይዞ እናገኘዋለን።ለአብነትም አዳብና ፣ኬርታ ዪምር ዪምርና ሌሎችም ባህላዊ ክንውኖች ከባህላዊ ይዘታቸው በተጨማሪ ጠለቅ ያለ ከክርስትና እምነት ጋር የተያያዘ ሃይማኖታዊም ይዘት ያላቸው ናቸው።
በአጠቃላይ ስለክስታኔ ማህበረሰብ ባህልና አኗኗር ስንፅፍም ስናነብም በዚህ አውድና ክስታኔዎች ልክ እንደስያሜያቸው ክርስትናን ባህላቸው አርገው ለዘመናት የኖሩ መሆናቸው መረዳት በጣም አስፈላጊ ነገር ነው።

ስለማህበረሰቡ ይችን ታክል ፍንጭ ሰጥተን ወደ ተነሳንበት ዋና ርዕሰ ጉዳይ ስንመለስ ክስታኔዎች ገናን እንዴት ያከብሩታል? በገና ወቅት ምንምን አይነት ሃይማኖታዊና ባህላዊ ክንዋኔዎች ይከወናሉ?ሃይማኖታዊና ባህላዊ ትውፊታቸውስ ምንድነው?የሚሉትን አንኳር ነጥቦች ማንሳት ግድ ይለናል።

የገና በዓል በክስታኔ ጉራጌ ዘንድ በአብዛኛው በኢትዮጵያውያን ዘንድ የተለመደው ሃይማኖታዊና ባህላዊ የገና አከባበር እንዳለ ሆኖ ነገር ግን በክስታኔዎች ዘንድ ሌሎች ሃይማኖታዊ ትውፊት ያላቸው ባህላዊ ክንዋኔዎች አሉ። ከእነዚህም ውስጥ ዪምር ዪምር፣፣አንቃትና፣እንዞሪቴ የሚጠቀሱ ናቸው።

በክስታኔ ቤተ-ጉራጌ ገና ላይ ከሚከውኑ ባህላዊ ክንውኖች አንዱ ዪምር ዪምር ነው።ዪምር ዪምር በአንድ መንደር የሚኖሩ ልጃገረዶችና ወጣቶች የገና ዕለት ወንፊት ፣ጠላ በጣሳና በቂቤ የታሸ የገብስ ቆሎ ይዘው በመንደሩ ቀጣይ በምታገባው ልጃገረድ ግቢ ውስጥ ባለ መስክ ላይ በሰብስበው ያያዙትን ወንፊት ወደ ፀሀይ አቅጣጫ (ወደ ምስራቅ) በማንሳትና ፊታቸውን በያዙት ወንፊት በመሸፈን "ዪምር ዪምር አንድ፣ ዪምር ዪምር ሁለት... "እያሉ እስከ 12 ጊዜ ከቆጠሩ በኋላ የያዙትን ወንፊት ወደ መሬት ወርውረው በመጣል ወጣቶች የሚያከብሩት ስነስርዓት ነው።በመቀጠል ወጣቶቹ እስከ 12 ጊዜ ዪምር ዪምር ካሉ በኋላ የያዙትን ወንፊት ወርውረው ይጥሉታል።በመቀጠልም እያንዳንዳቸው ይዘው የመጡትን ጠላና በቂቤ የታሸ ቆሎ አንድ ላይ በማደባለቅ ቆለው እየበሉ ጠላውን እየጠጡ ጫወታቸው ይቀጥላሉ። በመጨረሻም ዪምር ዪምር ብቅ ቤል የዳኮኛ(የሚትኛ) ጠላት ጠክ ቤል" በማለት የዪምር ዪምር ስነስርዓታቸው ያጠናቅቃሉ።

ነገርግን የልጃገረዶቹ ጫወታ በዚህ ብቻ አያበቃም በድጋሚ ማታ ላይ እያንዳንዳቸው ከየቤታቸው እንጀራ በወጥ በመያዝ በሚቀጥለው ጥር ወይም መጋቢት ላይ በምታገባው ልጃገረድ ቤት ማታ ማታ በመሰብሰብና በማደር እስከ ጥር ድረስ የተለያየ ጨዋታ ይጫወታሉ። ማታ ማታ ልጃገረዶቹ ሲሰበሰቡ የአካባቢው ጎረምሶችም የተሰበሰቡበት ቤት ድረስ ሄደው አብረዋቸው ይጫወታሉ ።ነገር ግን ጎረምሶቹ ማደር አይችሉም ተጫውተው በጊዜ ወደየቤታቸው መሄድ ይጠበቅባቸዋል።

የዪምር ዪምር ትውፊታዊ አመጣጥ
በክስታኒኛ(ጉራጊኛ) ቋንቋ ዪምር ማለት ፀሀይ ወይም ኮከብ ማለት ሲሆን ዪምር ዪምር ማለት ደግሞ ፀሀይ ፀሀይ ወይም ኮከብ ኮከብ ማለት ነው።
የዪምር ዪምር ጥሬ ትርጉሙ ይሄ ከሆነ የልጃገረዶችና ወጣቶቹ ወደ ፀሀይ አቅጣጫ በመዞር ፊታቸውን በወንፊት በመጋረደ "ዪምር ዪምር አንድ ..." እያሉ 12 ጊዜ መቁጠራቸው ትርጉሙ ምንድነው የዪምር ዪምር ስነስርዓት ከገና በዓል ጋር ያለው አጠቃላይ ስዕልና ቁርኝት እንዲሁም ሃይማኖታዊ ዳራው ለመረዳት እጅግ ጠቃሚ ነገር ነው።
የልጃገረዶቹና የወጣቶቹ ፊታቸውን ወደ ፀሀይ አቅጣጫ በማዞርና በወንፊት በመጋረድ 12 ጊዜ "ዪምርዪምር አት፣ ዪምር ዪምር ኪት፣ዪምር ዪምር ሶስት..." እያሉ መቁጠራቸው ሰባሰገል የክርስቶስን መወለድ ያበሰራቸው የምስራቅ ከከብ ተከትለው እየሱስ የተወለደበት ስፍራ ለመድረስ ያደረጉትን ፍለጋ የሚያሳይ ነው በማለት የአካባቢው የአይማኖት አባቶች እና ሽማግሌዎች ይናገራሉ። ሰባ ሰገል(ሰባሰገል ማለት በግዕዝ የጥበብ ሰዎች ማለት ነው) ከምስራቅ ተነስተው ወደ እየሩሳሌም ከመድረሳቸው በፊት እንደመፅሐፍ ቅዱስ ገለፃ የምስራቋ ኮከብ አንዳንዴ ትሰወርባቸው ነበር።ሰባሰገሎችም ጎዞቸው ለመቀጠል ሰማይ ላይ ካሉት እልፍ አህላፍ ከዋክብት የምስራቋን ኮከብ ፈልገው ማግኘት ግድ ይላቸው ነበር።

ክፍል ሁለት ይቀጥላል።
389 views08:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-28 11:44:47
352 views08:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ