Get Mystery Box with random crypto!

ዳጉ-ጆርናል/Dagu-Journal

የቴሌግራም ቻናል አርማ zena24now — ዳጉ-ጆርናል/Dagu-Journal
የቴሌግራም ቻናል አርማ zena24now — ዳጉ-ጆርናል/Dagu-Journal
የሰርጥ አድራሻ: @zena24now
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 34.42K
የሰርጥ መግለጫ

The best fiction is far more true than any journalism
📢 ተዓማኒ የመረጃ ምንጭ ፤ ለሙያው ስነምግባር ተገዢ በሆኑ ጋዜጠኞች ብቻ
👉 በፌስቡክ ገፆቻችን https://www.facebook.com/simon.dereje.56
👉 https://www.facebook.com/mik0Man

Ratings & Reviews

4.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2023-04-26 19:29:52
በሉሜ ወረዳ ልዩ ስሙ ጎዴ ዮሐንስ በተባለ አካባቢ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ11 ተሳፋሪዎች ህይወት አልፏል

ከአረርቲ ከተማ ተነስተው ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ የነበሩ ተጓዦች በሉሜ ወረዳ ልዩ ስሙ ጎዴ ዮሐንስ በተባለ አካባቢ በደረሰ የመኪና አደጋ የ11 ተሳፋሪዎች ህይወት ማለፉ ተገልጿል።

አደጋው አይሩፍ የኮድ ቁጥር ኦሮ 27600 የሆነ መኪና ተሳፋሪዎችን ጭኖ ሲጓዝ ሴራሚክ ጭኖ ከቆመ መኪና ጋር በመጋጨቱ የተከሰተ መሆኑን የአረርቲ ከተማ ከንቲባ አቶ ጌታቸው ለማ በሰጡት የሀዘን መግለጫ ገልጸዋል።

የሉሜ ወረዳ ኮሚኒኬሽን በበኩሉ አደጋው ጠዋት 11:30 ላይ መከሰቱን ጠቅሶ ወደ አዳማ ሲጓዝ የነበረ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ከቆመ IVCO TRAKAR-ET 48435 ጋር በመጋጨቱ መከሰቱን ገልጿል።

በአደጋውም የ10 ሰዎች ህይወት ማለፉንና 2ቱ ሴቶች መሆናቸውን ጠቅሷል። በተጨማሪም በሁለት ሰዎች ላይ ከፍተኛ የአካል ጉዳት እንዲሁም በአንድ ሰው ላይ ቀላል ጉዳት መድረሱን ነው የገለጸው።

የሉሜ ወረዳ የትራፊክ ደህንነት አስተባባሪ ኢንስፔክተር ተክልየ ታምሩ የአደጋው መንስኤ ከፍጥነት በላይ ማሽከርከር እንደሆነ ገልጸዋል።
#ዳጉ_ጆርናል
2.2K viewsNH, edited  16:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 16:30:38 በቤተል ከ150 በላይ ቤቶች ነዋሪዎች የኤሌክትሪክ አገልግሎት ከአምስት ቀናት በላይ ተቋርጦብናል ሲሉ ቅሬታ አቀረቡ

በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ቤተል ሰኔ 30 በተባለ የቤት ማህበር የሚገኙ ከአንድ መቶ ሀምሳ በላይ መኖሪያ ቤቶች የአሌክትሪክ አገልግሎት ከገኙ ከአምስት ቀናት በላይ መቆጠሩን የአካባቢው ነዎሪዎች ቅሬታቸውን ለብስራት ሬድዮ ተናግረዋል።

ነዋሪዎቹ ያለፈው አርብ ምሽት ጀምሮ እስከ ዛሬ ሚያዚያ 18 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ባለማግኘታቸው የተቦካ ሊጥ መድፋታቸወቁን፣ በበዓል ለፋሲካ እና ለረመዳን የተዘጋጀ ስጋ በመበላሸቱ በየቦታው ተጥለው ሽታ መፍጠሩን ተናግረዋል።

የአካባቢው ነዋሪዎች ሰኞ እለት ጉዳዩ ለሚመለከተው ቅርንጫፍ የአሌክትሪክ ሀይል ቢሮ ጉዳዩን ቢያሳዉቁም ትራንስፎርመር ተቃጥሎ ነው አሁን ትራንስፎርመር የለም የሚል መልስ እንደተሰጣቸዉ ገልጸዋል፡፡እሮብ እለት ዳግም ቅሬታቸዉን ያሰሙ ሲሆን ትራንስፎርመር ቢገኝም ክሬን ተበላሽቶብናል የሚል መልስ እንደተሰጣቸው ለጣቢያችን ገልጸዋል፡፡

ብስራት ሬድዮም ይህንኑ ተከትሎ ለአዲስ አበባ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የነዋሪዎችን ቅሬታ ያቀረበ ሲሆን የአገልግሎቱ የሪጅናል ኮሚዩኒኬሽን ሥራ አስኪያጅ አቶ በቀለ ክፍሌ ጉዳዩን በተመለከተ ቅርንጫፉ ክሬኑ ተበላሽቶ ገራጅ መግባቱን ያረጋገጡ ሲሆን ከምስራቅ ቅርንጫፍ ክሬን በማስመጣት የተቃጠለው ትራንስፎርመር እንደሚቀየር ተናግረዋል፡

በትግስት ላቀዉ
#ዳጉ_ጆርናል
2.8K viewsTrue, 13:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 15:36:46
የቀድሞ የሱዳን ፕሬዝዳንት አልባሽር ጦርነቱ ከመጀመሩ በፊት ወደ ሆስፒታል ተወስደዉ እንደነበር ተነገረ

የሱዳን ጦር እንዳስታወቀዉ የቀድሞው የሱዳን ፕሬዝዳንት ኦማር አልበሽር በተያዘዉ ወር መጀመሪያ ላይ ጦርነት ከመጀመሩ በፊት ከማረሚያ ቤት ወደ ወታደራዊ ሆስፒታል ተዛዋዉረዉ እንደነበር ይፋ አድርጓል።ባሽር በ1989 በወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት ወደ ስልጣን የመጡ ሲሆን ሱዳንን እስከ 2019 የገዙ ሲሆን በሀገሪቱ በተቀሰቀሰዉ ከባድ ተቃውሞ በመፈንቅለ መንግስት ከስልጣን መወገዳቸዉ ይታወሳል፡፡

ከስልጣን መነሳታቸዉን ተከትሎ በሙስና ወንጀል ተከሰዉ የሁለት አመት እስራት ተበይኖባቸዋል፡፡ጦሩ ባወጣዉ መግለጫ ባሽር እና ሌሎች በርካታ ሰዎች በህክምና ባለሙያዎች ጥቆማ በዋና ከተማዋ ካርቱም አቅራቢያ ከሚገኘው ኮበር ማረሚያ ቤት በፖሊስ ቁጥጥር ስር ወደሚገኘው ወታደራዊ ሆስፒታል ተወስደዋል ብሏል።

በኦማር አልባሽር ዘመነ መንግስት ሚኒስትር የነበሩት አሊ ሀሮንና አል ባሽርን ጨምሮ  ከሌሎች የቀድሞ ባለስልጣናት ጋር እስር ቤቱን ለቀው መውጣታቸውን ከተነገረ በኃላባሽር የት እንዳሉ ጥያቄ ሲያስነሳ ቆይቷል፡፡አንዳንድ ዘገባዎች ባሽር በእስር ቤቱ ላይ በተሰነዘረ ጥቃት ተፈተዉ ሊሆን እንደሚችሉ በስፋት እየተነገረ ይገኛል፡፡

ባሽር እና ሃሮን በምዕራብ ሱዳን ዳርፉር ግዛት ተፈጽመዋል በተባሉ ወንጀሎች በአለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ይፈለጋሉ።

በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል
2.8K viewsTrue, 12:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 12:40:10 56 በመቶ ለሚሆነዉ የትግራይ ክልል አካባቢዎች ነዳጅ እየቀረበ ነዉ ተባለ

የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን በትግራይ ክልል ከጦርነቱ በኋላ የነዳጅ አቅርቦት በተሟላ መልኩ እንዲሆን በመስራት ላይ መሆኑን አስታዉቋል። የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰሀረላ አብዱለሂ ለብስራት ራዲዮ እንደተናገሩት ፤ ከክልሉ አካባቢዎች 56 በመቶ ያህሉ የነዳጅ አቅርቦት ሽፋን እያገኙ መሆኑን ገልፀዋል።

እንደ ዋና ዳይሬክተሯ ገለጻ ፤ ክልሉ ከዚህ ቀደም ካለዉ የናፍጣ ኮታ እጥረት የተነሳ ለመንግስት አገልግሎት ሰጪዎች ፣ ለጸጥታ ፣ ለትራንስፖርት ሰጪዎች ፣ ለባንክ እና ሌሎች አገልግሎት ሰጪዎች ቅድሚያ ሲሰጥ የነበረ መሆኑን አንስተዉ ፤ አሁን አቅርቦቱን ለማሻሻል መቻሉን ወ/ሮ ሰሀረላ ተናግረዋል።

በተጨማሪም ባለስልጣኑ በክልሉ የሚንቀሳቀሱ የነዳጅ አዳይ ኩባንያዎችም የዱቤ አገልግሎት እንዲያገኙ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል። ለዚህም አንዳንድ የዉጭ ድርጅቶች ፖሊሲዎቻቸዉን ጭምር በመከለስ አገልግሎቱን እየሰጡ መሆኑን አክለዋል።

በሌላ በኩል መሶቦ ሲሚንቶ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን ተከትሎ የነዳጅ አቅርቦቱ ከሞላ ጎደል ተቀርፏል ብለዋል። ሌሎች በክልሉ ለሚገኙ ኢንዱስትሪዎችም የቤንዚንና ናፍጣ አቅርቦት እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

በቀጣይ በጦርነቱ የወደሙ ቀሪ የነዳጅ ማደያ ጣቢያዎችን መልሶ የመጠገን እና ወደስራ ማስገባት አቅድ አንግቦ እየሰራ መሆኑን የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰሀረላ አብዱላሂ ጨምረዉ ለብስራት ራዲዮ ተናግረዋል።

በበረከት ሞገስ
#ዳጉ_ጆርናል
2.9K viewsTrue, 09:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 12:27:09
በሰሜን ኮሪያ ላይ የተጣለውን ማዕቀብ በመጣስ ሲጋራ የሸጠው ኩባንያ 635 ሚሊዮን ዶላር ቅጣት ሊከፍል ነው

የብሪቲሽ አሜሪካን የትምባሆ ኩባንያ በሰሜን ኮርያ ላይ የተጣለውን ማዕቀብ በመጣስ ሲጋራ መሸጡን ማመኑን ተከትሎ 635 ሚሊዮን ዶላር ቅጣት ከነወለዱ ሊከፍል መሆኑ ተሰምቷል።በምህፃረ ቃሉ ቢኤቲ የተሰኘው የትንባሆ ኩባንያ እንደ ዩናይትድ ስቴትስ ባለስልጣናት መረጃ ከሆነ ከ2007 እስከ 2017 በሰሜን ኮሪያ እንቅስቃሴ ያደርግ እንደነበረተናግረዋል።

የኩባንያው ኃላፊ ጃክ ቦውልስ "በተፈጸመው በደል በጥልቅ ተጸጽተናል" ብለዋል። አሜሪካ በሰሜን ኮሪያ ላይ የኒውክሌር እና የባላስቲክ ሚሳኤል እንቅስቃሴ የተነሳ ከፍተኛ ማዕቀብ ጥለች።ኩባንያው በዓለም ላይ ካሉ ግዙፍ የትምባሆ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች አንዱ ሲሆን ከእንግሊዝ በሁሉም ዘርፍ ካሉ 10 ትልልቅ ኩባንያዎች መካከል አንዱ ነው።

የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን ከፍተኛ አጫሽ መሆናቸው ይታወቃል። ባለፈው አመት በዩናይትድ ስቴትስ አቅራቢነት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ወደ ሰሜን ኮሪያ ትንባሆ መላክን እንዲከለክል ለማድረግ ብትሞክርም በሩሲያ እና በቻይና ውድቅ መደረጉ ይታወሳል።

በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል
2.9K viewsTrue, 09:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 09:18:58 ኢትዮጲያዊን ዜጎችን ወደ ኬኒያ ለማሻገር የሞከረ አሽከርካሪ ከነረዳቱ በቁጥጥር ስር ዋለ

በህገወጥ ደላሎች ከሀገር  ለመዉጣት የነበሩት 19 ወጣት ወንዶች ናቸው

በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን በህገወጥ መንገድ ኢትዮጵያዊያን ዜጎችን ወደ ኬኒያ ለማሻገር የሞከረ አሽከርካሪ ከነ ረዳቱ በቁጥጥር ስር መዋሉን የደቡብ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የሚዲያ ክፍል ሀላፊ ምክትል ኮማንደር ታጁ ነጋሽ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።

አሽከርካሪዉ በሰሌዳ ቁጥር  ኮድ 3 -19157 ደ.ህ በሆነች አነስተኛ የህዝብ ማመላለሻ ሚኒባስ  19 ሰዎችን ጭኖ  በጂንካ ከተማ አድርጎ ወደ ኬኒያ ለመሻገር  በጉዞ ላይ ሳለ ሚያዚያ 16 ቀን 2015 ዓ.ም ከምሽቱ 2:00 ሰዓት በሐመር ወረዳ ቱርሚ ከተማ እንደደረሰ በፖሊሶች ተጠርጥሮ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገልጿል።

በህገወጥ ደላሎች ተገፋፍተዉ ከሀገር  ለመዉጣት በጉዞ ላይ የተያዙት አስራ ዘጠኙ ሰዎች ሁሉም ወጣት ወንዶች ሲሆኑ በቱርሚ ከተማ ፖሊስ ተጠልለዉ እንደሚገኙና መነሻቸዉ ከሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል ከአማራና ከአፋር ክልሎች እንደሆነ ተጠቁሟል።

ከሀገር ለመዉጣት በጉዞ ላይ የነበሩ በፖሊስ ተይዘዉ ወደ መጡበት የተመለሱ በርካቶች መሆናቸዉ የገለፀዉ የደቡብ ክልል ፖሊስ በሶስቱ ሀገራት አዋሳኝ አካባቢዎች ለሀገር ደህንነት ሲባል ጥብቅ ቁጥጥር የሚደረግ መሆኑ በመገንዘብ ወጣቱ አላስፈላጊ ወጪና እንግልት መዳረግ የለበትም ሲሉ ኮማንደር ታጁ ነጋሽ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።

የደቡብ ኦሞ ዞን የኢትዮ ኬኒያና ደቡብ ሱዳን የጋራ አዋሳኝ መሆኑን ተከትሎ ህገወጥ ደላሎች የኢትዮጵያና የኤርትራ ዜጎችን ከሀገር ለማስወጣት ተደጋጋሚ ሙከራ  ሲያደርጉ ይስተዋላሉ።

በሳምራዊት ስዩም
#ዳጉ_ጆርናል
3.2K viewsTrue, edited  06:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-25 21:29:57 አጫጭር መረጃዎች የሱዳንን ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ

የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ በተቀናቃኝ ኃይሎች መካከል ግጭት ውስጥ የምትገኘው ሱዳን የሩሲያ የግል ወታደራዊ ኩባንያ የሆነውን የዋግነር ግሩፕ አገልግሎት የመጠቀም መብት እንዳላት ተናግረዋል። ላቭሮቭ ይህንን የተናገሩት በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው።

በሱዳን ታጣቂ ሃይሎች እና በፈጣን ድጋፍ  ሰጪ ሃይሎች (አርኤስኤፍ) መካከል የ72 ሰአታት የተኩስ አቁም ስምምነት በዩናይትድ ስቴትስ አደራዳሪነት ቢደረስም በካርቱም መንትያ ከተማ ኦምዱርማን የከባድ መሳሪያ እና የተኩስ ድምጽ እየተሰማ መሆኑን ከስፍራው የሚወጡ መረጃዎች አመላክተዋል።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሱዳን ባለው ጦርነት እስከ 270,000 የሚደርሱ ሰዎች ወደ ጎረቤት ሀገራቱ ደቡብ ሱዳን እና ቻድ ሊሰደዱ እንደሚችሉ ገለፀ። በቻድ የሚገኘው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ኤጀንሲ 20,000 ሰዎች ወደ ሀገሪቱ መግባታቸውን እና እስከ 100,000 የሚደርሱ ስደተኞችን እንደሚጠብቅ ገልጿል።

በደቡብ ሱዳን የሚገኘው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ኤጀንሲ 45,000 ስደተኞች ከሱዳን ድንበር አቋርጠው መውጣታቸውንና 125,000 ደቡብ ሱዳናውያን በሁከቱ ምክንያት ሱዳንን ለቀው እንዲወጡ መደረጉን ገልጿል።

እንግሊዝ የብሪታንያ ፓስፖርት የያዙ ሰዎችን ከሱዳን የማስወጣት ተልእኮ ጀምራለች፣ከዋና ከተማዋ ውጭ ወደሚገኝ አየር ማረፊያ የብሪታንያ ፓስፖርት የያዙ ዜጎች እንዲመጡ ጠይቃለች።

የግብፅ አል አህራም ጋዜጣ እንደዘገበው በሳውዲ አረቢያ በጦር ኃይሎች አዛዥ አብዱልፈታህ አል-ቡርሃን እና በአርኤስኤፍ መሪ መሀመድ ሃምዳን ዳጋሎ መካከል የእርቅ ውይይት ለማካሄድ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ዘግቧል።

ከ10 ቀናት የከተሞች ጦርነት በኋላ የተኩስ አቁም ስምምነት ተግባራዊ በመደረጉ ፈረንሳይ 538 ሰዎችን ከሱዳን ማስወጣቷን ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ተናግረዋል። የፈረንሳይ ዜጎች ከጠቅላላው የተፈናቃዮች ቁጥር 209 ያህሉ መሆናቸውን ማክሮን በኤሊሴ ቤተ መንግስት የመከላከያ ምክር ቤት ጉባኤ ላይ ተናግረዋል።

በሱዳን በምዕራብ ዳርፉር በጄኔናም ጦርነት መቀስቀሱን ከስፍራው የወጡ መረጃዎች አመላክተዋል።

በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል
3.4K viewsTrue, 18:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-25 21:00:31 በዋግ ኽምራ ከመንግስት የሚደረገው መደበኛ ድጋፍ ከተቋረጠ ከሁለት ወራት በላይ  ማስቆጠሩ ተነገረ

    ወደ ቀያቸው የተመለሱ ከ32 ሺ በላይ የአበርገሌ ተፈናቃዮች ስጋት ላይ ይገኛሉ


በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ከአበርገሌ እና ከጣግብጂ ተፈናቅለው የሚገኙ ዜጎች ወደ ቀያቸው የመመለስ ስራ እየተሰራ  ቢሆንም መደበኛ ድጋፍ ከተደረገ ከሁለት ወራት በላይ ተቆጥሯል፡፡ከዚህ ቀደም 2 ዓመት ከ7ወር በላይ በጸጥታ እና በረሃብ ችግር ከአካባቢያቸው ተፈናቅለው ከነበሩ ተፈናቃዮች መካከል ከ15 ቀናት በፊት 32ሺ 223ቱ ወደ አበርገሌ ወረዳ እንዲመለሱ መደረጉን የአስተዳደሩ የአደጋ መከላከል የቅድመ ማስጠንቀቂያ ምላሽ ቡድን መሪ ወ/ሮ ዝናሽ ወርቁ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።

ተፈናቃዮቹ ወደ አበርገሌ ከተመለሱ 15 ቀናት የተቆጠረ ሲሆን ባሳለፉነው የትንሳኤ በዓል ድጋፉ ይደረግላቸዋል ቢባልም ምንም አይነት ድጋፍ እንዳልመጣ አክለዋል፡፡እንደ ወ/ሮ ዝናሽ ገላፃ በአበርገሌ የሚገኙ ተፈናቃዮች በአፋጣኝ የምግብ እርዳታ ካላገኙ የሰው ሕይወት ሊያልፍ  እንደሚችል እና ዳግም ከወረዳው ሊፈናቀሉ ይችላሉ ብለዋል፡፡በተጨማሪም በዋግ የሚገኙ ከ30 ሺ 154 በላይ የጣግብጂ ተፈናቃዮችን ወደ ቀያቸው ለመመለስ የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ ይገኛል፡፡

የሚመለከተው አካል ከዓመታት በኋላ ወደ ቀያቸው ለተመለሱ እና ለሚመለሱ ተፈናቃዮች አሁንም ድጋፍ የሚያሻቸው በመሆኑ አፋጣኝ ድጋፍ ሊያደርግል ይገባል ሲሉ ወ/ሮ ዝናሽ ወርቁ ጨምረዉ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።

በሳምራዊት ስዩም
#ዳጉ_ጆርናል
3.2K viewsTrue, 18:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-25 20:30:11
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን በ2024 በድጋሚ ለመመረጥ ዘመቻ ጀመሩ

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን በ2024 ድጋሚ ለመመረጥ ዘመቻቸውን በይፋ የጀመሩ ሲሆን ከሪፐብሊካን እጩ ዶናልድ ትራምፕ ጋር ለሁለተኛ ጊዜ ሊፎካከሩ በሚችሉበት የአሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ የዴሞክራቲክ ግንባር ቀደም እጩ ሆነዋል። ባይደን ዛሬ ባጋሩት የቪዲዮ መልዕክት የመጀመሪያው የተሳካ ፕሬዚዳንታዊ ምረጡኝ ቅስቀሳ ከጀመሩ አራተኛ አመት ላይ ይገኛሉ።

አብዛኛው ዴሞክራቶች ባይደንን በሚቀጥለው አመት ምርጫ ከሪፐብሊካን ተፎካካሪያቸው በላቀ ሁኔታ ይደግፋሉ ሲል በቅርቡ የተደረገ የህዝብ አስተያየት አመላክቷል። ነገር ግን ዴሞክራተ ፕሬዝዳንት በስልጣን ዘመናቸው ከነበሩት አንዳንድ ዝቅተኛ አፈፃፀም ጋር በተያያዘና ከባይደን እድሜ አንፃር ወደ ሪፐብሊካን ሊያጋድል ይችላል።

ባይደን በሁለተኛው የስልጣን ዘመናቸው ማብቂያ ላይ 86 ዓመታቸው የሚሆነው ሲሆን ከ 50 ዓመታት በላይ በዋሽንግተን ልምድ ቢኖራቸውም እድሜያቸው ስጋትን አጭሯል። የፓርቲያቸውን ሹመት በተመለከተ ግን ያለምንም ከባድ ዲሞክራሲያዊ ተፎካካሪ ለማሸነፍ ቀላል መንገድ ይሆንላቸዋል ተብሎ ይገመታል።

በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል
3.2K viewsTrue, 17:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-25 18:21:06 የኢትዮጵያ አማካኝ የቀን የነዳጅ ፍጆታዋ 2.9 ሚሊዮን ሊትር ደርሷል

25 ሚሊዮን ሊትር ነዳጅ ማከማቸት የሚችሉ ዴፖዎች ካለስራ ተቀምጠዋል


ከአመት አመት የኢትዮጵያ የቀን አማካይ የነዳጅ ፍላጎቷ በመጨመር ላይ እንደሚገኝ በንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር የሚኒስትሩ አማካሪ አቶ አህመድ ቱሳ መናገራቸውን ብስራት ራዲዮ ሰምቷል።

በ 2013 ዓ.ም ኢትዮጵያ በየቀኑ በአማካይ  2 ሚሊዮን ሊትር የነዳጅ ፍጆታ የነበራት ሲሆን ይህ ቁጥር በ 2014 ዓ.ም ወደ 2.5 ሚሊዮን ሊትር ከፍ ብሏል። በተመሳሳይ በተያዘዉ ዓመት የቀን ነዳጅ ፍጆታዋ 2.9 ሚሊዮን ሊትር መድረሱን ገልጸዋል።

የፍላጎቱ እና የፍጆታዉ ቁጥር ከአመት አመት በመጨመር ላይ ቢገኝም አሁንም ግን አቅርቦቱ በቂ አለመሆኑን አማካሪዉ ጠቅሰዋል። እንደ አቶ አህመድ ገለፃ ፤ ከጎረቤት ሀገር በዉድ ዋጋ ተጭኖ የሚመጣዉን ነዳጅ በአግባቡ ከመጠቀም አኳያም ችግር እንዳለ ተናግረዋል። በሌላ በኩል ከሚገባዉ ነዳጅ ዉስጥም በክልሎች የሚሸጠዉ አነስተኛ መሆኑን አክለዋል። ለዚህም የነዳጅ ማደያዎች የተዛባ ስርጭት አስተዋጽኦ እንዳለዉ ገልጸዋል።

በተጨማሪም ፤ በነዳጅ አከፋፋይ ኩባንያዎች የተገነቡ 25 ሚሊዮን ሊትር ነዳጅ ማከማቸት የሚችሉ ዴፖዎች ካለስራ መቀመጣቸዉን ተናግረዋል።

አሁን ወደ ሀገር ከሚገባዉ የነዳጅ አቅርቦት መጠን ከፍ ባለ መልኩ ለማስገባት ከመሰረተ ልማት አኳያም የነዳጅ ማመላለሻ ቦቴዎች እጥረት መኖሩን ተናግረዋል። በኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት 3 ሺህ የሚሆኑ የነዳጅ አመላላሽ ተሽከርካሪዎች እንደሚገኙም አቶ አህመድ ቱሳ ጨምረዉ ለብስራት ራዲዮ ተናግረዋል።

በበረከት ሞገስ
#ዳጉ_ጆርናል
3.3K viewsTrue, 15:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ