2023-03-06 17:15:25
ከምስጋና በኋላ…
"ርዕሰ አንቀጽ"
"…የዛሬው የምስጋና ጊዜ ደግሞ እጅግ የተለየ ነው። በ20 ደቂቃ ውስጥ 1ሺ ሰው፣ በ3 ሰዓት ውስጥ 5ሺ ሰው እግዚአብሔር ይመስገን ሲል አየሁ። ከምር ይሄ ተአምር ነው። አለመደነቅም አይቻልም። ቴሌግራም በእጅህ ላይ ባለ ሥልክህ የምትጠቀመው ፕላትፎርም ነው። የምታነበውን፣ የምትሰማውና፣ የምታየውን መልእክት ሁሉ ወደህና ፈቅደህ ወደራስህ የምትጠራው ራስህ ነህ። መንደር መርጠህ የምትገባውም ራስህ ነህ።
"…በዚህም መሰረት አንተ እና አንቺ ወደኸኝም ይሁን የተለየ ሌላ ምክንያት ኖሮህ ወደ እኔ ወደ ዘመዴን ፔጅ መንደር ተንጦልጡለህ የምትመጣው አንተው ራስህ ነህ። የምጽፈውን፣ የምለጥፈውን እንድታይ በካህን አላስገዘትኩህም፣ በፖሊስ አላስገደድኩህም ራስህ በምርጫህ ወደህና ፈቅደህ ነው የምታየኝ የምታነበኝም።
"…ታዲያ ቤቴ ራሱን የቻለ የራሱ የሆነ ሕግ እና መመሪያም አለው። በቤቴ ውስጥ ወያኔም፣ ሸአቢያም፣ ብልፅግናም፣ ኦነግም፣ ኢዜማም፣ ብአዴንም ሆኖ መቀመጥ ይቻላል። ኦሮሞም፣ ትግሬ፣ ዐማራ፣ ጉራጌ፣ ወላይታ ሲዳማ ወዘተም ሆኖ መቀመጥ ይቻላል። የወሃቢይ እስላም፣ ፅንፈኛ ጴንጤ፣ እኔን ጠል ኦርቶዶክስ፣ ተሃድሶም ሆኖ መቀመጥ ይቻላል። ባለሥልጣን፣ ጀነራል፣ ኮሎኔል፣ ኢንጅነር፣ ዶክተር፣ ጋዜጠኛ፣ አንጥረኛ ሆኖ መቀመጥም ችግር የለውም። ዘፋኝ ሁን ዘማሪ፣ ቄስ ሆን ሼክ ፓስተር ለእኔ ደንታዬ አይደለም። ሃብታም ሁን ደሃ ኬሬዳሽ። ምንም ሁን ለደንታህ ነው። ለወሬ ብቻ ጠኔውን ለማስታገስ የሚቀመጥ አለ። ለመሳቅ፣ ለማልቀስ፣ ኮመንት ለማንበብም የሚመጣ አለ። እሱም ችግር የለውም።
"…ክልክሉ ነገር በቤቴ ውስጥ አዛዥ ልሁን ስትል ነው። በእኔም በባለቤቱና በመንደሬ ኗሪዎች ላይ በሌላ ቦታ የለመድከውን ክፍትአፍነትህን እዚህ እሞክረዋለሁ ያልክ እንደሆነ ብቻ ነው። ልቅነትህን እዚያው በለመድክበት። ከርዕስ ውጪ ማውራት፣ በጎንህ የታጠቅከውን ሽጉጥ እየዳሰስክ እንደ ወጠጤ በቤቴ ውስጥ በእኔም ላይ ሆነ በሌላው ላይ መደንፋት፣ ማቅራራት፣ መሸለል ፈፅሞ አይፈቀድም። ከቻልክ በሰላም፣ በጨዋ ደንብ የተጻፈው ነገር ደምስርህን ቢበጥሰውም ነርቭህን ቢነካውም፣ ጥቅምህን ቢጎዳውም ተረጋግተህ ሃሳብህን በጨዋ ደንብ መግለፅ እንጂ በባለጊዜ ነኝ ሙድ ነጭ ቂጡን የጣለ ዱርዬ ነኝ ብለህ፣ በአንጎበር አፍህ እወበራለሁ፣ የቁጭራ ሰፈር ስድብ እሳደባለሁ ማለት በፍጹም አይፈቀድም። አስነጥስህሃለሁ። እቀስፍሃለሁ። ከዚያ ፍርዬ ጋር ሄደህ በሌላ ሲም ካርድ ጨዋ ሆነህ ትቀላቀለኛለህ።
"…በእኔ ፔጅ እኔን ብቻ ልትሰድቡበት የምትችሉት የምፈቅድላችሁ ስድብም አለ። እኔን ብቻ ነው ታዲያ። ማንም የፔጄ ደንበኛ ሌላ ሰው ተሳስቶ መስደብ አይችልም። መሞገት እንጂ። በፔጄ ላይ እኔን በተመለከተ እኔን መስደብ የሚፈልግ ባህላዊ፣ ሃገር በቀል የሆነ እናትን ሳይሆን አባቴን በስሱ መስደብ ይቻላል። "አፍር ያስበላህ፣ አፈር ብላ፣ ሙት ድፍት ያድርግህ የአባቴ አምላክ፣ ምኑ ሙትቻ ነው በአላህ፣ ምናምን ማለት ይቻላል። እንዲያ ብትሉኝ ተአብ የለውም። ከምንአባክንስና፣ አፈር ደቼ ያስበላህና ከመሳሰለ ተወዳጅ ከአካባቢያችን በቀላሉ ከማንኛውም ሰው አፍ ከምናገኛቸው ሃገር በቀል ስድቦች እንጂ ከዚያ የዘለለ ስድብ በፔጄ አይፈቀድም። ባህላዊው፣ ያደግንበት፣ የምርቃት አቻ የሆነ፣ የሰፈር ሰው ሁሉ እንደ ልጁ ተቆጥቶ ሰድቦ፣ ቆንጥጦን እኛን ባሳደገበት ስድብ መሰደብ ብዙም አያመኝም። ደስስም ነው የሚለኝ። ለበዓሉ ድምቀት መኖርም አለበት። ከዚያ ያለፈው ግን አይቻልም። አይፈቀድም።
"…የእኔንም ሆነ የሌላ ሰው አይን የሚያቆሽሽ ስድብ ለሚሳደቡ ሰዎች ጥብቅና ትቆሙ ዘንድ ሳትጠየቁ በስድብ መልስ የምትሰጡ ሰዎችንም አብሬ ነው የምቀስፈው። የማያስቀስፍ ስድብ እንኳ ቢሆን ኮመንታችሁን አነሣዋለሁ። ያለበለዚያ የሚፈጠረው ምንድነው የሚሆነው እኔ ተሳዳቢውን ስቀስፈው ኮመንታችሁ ብቻውን ይቀርና ለተመልካች ግራ ስለሚያጋባ ስታወዛግቡ ስለምትገኙ ነው። ደግሞም እኔ 18 ዓመት ያለፈኝ፣ 50 ዓመት ሊሞላኝ አንድ ፈሪ የቀረኝ የሽማግሌ ፍንዳታ ነኝ። ለእኔ ተደርቦ መልስ መስጠት በፍጹም ነውር ነው። ለነውረኛ እኔ ራሴ እበቃዋለሁ።
"…በተረፈ በፔጄ ላይ የትኛውም ዓይነት ማስታወቂያ መሥራት ክልክል ነው። የታመመ ሰው ይሁን፣ የጠፋ ሰው ይሁን፣ እኔ ያመንኩበት እና ኃላፊነት የምወስድበት የቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ካልሆነ በቀር ምንም ዓይነት ማስታወቂያ መጻፍ አይፈቀድም። እቀስፈዋለሁ። የባሕል መድኃኒትም ሆነ የጉዞ መርሃ ግብር፣ የስብሰባ ጥሪ፣ የምንም ምርቃት ማስተዋወቅ ክልክል ነው።
"…ሌላው የሚያስቀስፈው የመንደሬን ነዋሪዎች በውስጥ መስመር መጎንተል ነው። እሱ ነገር ነውር ነው። ይሄም ያስቀስፋል። ጡዘታም አርፈህ ተቀመጥ። የቆንጅዬ ልጁን ፎቶ ፕሮፋይል ፒክቸር አድርጎ የለጠፈን የ60 ዓመት አባት ሴት መስላህ ስትለፋደድ ፈጣሪ ያሳይህ። የ4 ልጆቹን እናት ፎቶ የለጠፈን ባል በውስጥ መስመር መጨቅጨቅ ምን የሚሉት ሰገጤነት ነው? ይሄ ፍጥጥ ያለ ዐመዳም 100 ኪሎ ፋርነት ነው። አጠገብህ ያለችውን አብሮ አደግህን ልከፍ፣ ጀንጅን፣ ጥበስ፣ አግባ፣ ውለድ፣ ብዛ ተባዛ። መሬት ላይ አጠገብህ ያለች ሄዋንን መጀንጀን እና መጥበስ ያቃተህ ገልቱ በአየር ላይ የማታውቀውን ሰው ፎቶ አይተህ መሳፈጥ ምንሼ? ሃኣ…? እረፍ አንት ነውረኛ።
"…በተረፈ በእኔ መንደር ጠዋት ጠዋት ማንኛውም ሰው በተለይ ኦርቶዶክሳዊ የተዋሕዶ ልጅ፣ እኔን በግሌ ይጥላኝ ይውደደኝ ለደንታው ነው እግዚአብሔርን ማመስገን ግን ግዴታው ነው። ሃይሃይ፣ ኬፍኬፍ፣ ሰላምነው? እንዴት ነህ? ፒስነው? የሚሉ የእግዚአብሔርን ክብር የወሰዱ መጤ ቃላትን ለማስወገድ እና የቀደመውን የእግዚአብሔርን ክብር ለመመለስ ሲባል ጠዋት ጠዋት የጀመርነውን እግዚአብሔር ይመስገን የሚለውን ዘመቻም አጠናክረን መቀጠሉ ግድ ነው። ግድ ነው አልኳችሁ ግድ ነው። ምንአባክ እንዳትሆን። እግዚአብሔር ይመስገን ብለህ በመጻፍህ ይሄ አመዳም ሌባ ጣትህ እንዳይቆረጥ ነው። ወጨበሬያም።
"…ይሄ ግዴታ ግን እስላም ጓደኞቼን አይመለከትም። ከፈቀዱ እነሱ የእኔዎቹ እስላሞች ለመጽሐፍ ቅዱሳዊው ጥቅስ ሳይሆን ለሰላምታው አላህምድሊላህ ማለት ይችላሉ። መብታቸውም ነው። ፅንፈኛ ጴንጤ፣ ፅንፈኛ የወሃቢይ እስላም ቢል ባይል ግን ለደንታው ነው። እሱ ስድና ልቅ አፉን ጦመኛ አድርጎ አርፎ ቁጭካለ በቂ ነው። የህወሓት ዲቃሎች፣ የኦነግ ፈዳሎች፣ የብልፅግና ኩሊዎችም እግዚአብሔር ይመስገን ይሉኛል ብዬም አልጠብቅም። በፔጄ የሚበዛው የወሬ ጠኔ ያለበት ራብተኛ እንደሆነም አውቃለሁ። እኔ ከብዙው የወሬ ራብተኛ ይልቅ ጥቂት ተመሳሳይ ላባ ካለን ወዳጆቼ ጋር መብረርን እመርጣለሁ። ይኸው እየበረርኩም ነው። ለአንድ የእግዚአብሔር ሰላምታ 5ሺ ሰው ማግኘት ቀላል የሚመስለው ካለ ሞክሮ ያሳየኝ። ይሄ ፈቃደ እግዚአብሔር ነው። የትንሣኤውን ልጆች መለያ ጊንጊልቻ ነው።
"…እኔ ከእኔጋር መብረር፣ መጓዝ የሚችሉትን ጠዋት ጠዋት በእግዚአብሔር ሰላምታ እያጠራሁ፣ እየለየሁ እጓዛለሁ። ለእኔ እነዚህ አመስጋኞች ለእኔ ዋሴ፣ ጠበቃዬ፣ አማላጆቼም ናቸው። እንዲህ በኃጢአት እንደተጨማለቅኩ እንኳ ብሞት እነዚህ ጠዋት ጠዋት አምላኬን ስሙን ጠርተው እግዚአብሔር ይመስገን ብለው በድፍረት፣ ሳይሳቀቁ፣ ሳይኮሩ፣ ሳይኩራሩ፣ በደስታ የሚያመሰግኑቱ ጓደኞቼ ይዋሱኛል። ጠበቃም ይሆኑኛል። ምንአልባት ገንዘብ የማገኝበት የሚመስላቸውና ዘመድኩን ሀብታም ይሆናል ብለው ለሰላምታው ምላሽ
3.5K views14:15