2022-08-31 10:35:42
"መልክ ከቤት ሙያ ከጎረቤት !!
• ጦማሯ ረጅም ናት። ርዝመቷ ግን በስልክ ስታነቧት ነው። ጨክናችሁ ውኃ እየተጎነጫችሁ፣ እያዛጋችሁ፣ እየተንጠራራችሁም፣ እያፋሸካችሁም ቢሆን እንደምንም አንብቧት። መልካም ንባብ።
"…ወዳጄ መጀመሪያ መልክ ከቤት ይስጥህ እንጂ ሙያውን ከጎረቤት ትማረዋለህ። ይሄ ደግሞ በጣም ቀላል ነው። ሙያ ከጎረቤት ለመማር ወጪ አይጠይቅም። አያደክምም። ምርምርም የለበትም። ለዐማራ በአሁን ሰዓት የሚያስፈልገው መልክ ነው። የሚወደድ፣ የሚስብ፣ ሸጋ የሆነ መልክ። በፌር ያልተነካካ፣ በኬሚካል በቀለም ያላበደ መልክ። መልክ ስልህ አይን፣ ቅንድብ፣ ከንፈር፣ ደረት፣ ዳሌ፣ ሽንጥ፣ ተረከዝ፣ ቁርጭምጭሚትና አገጭ እያልኩህ አይደለም። መልክ የምልህ ዐማራዊ መልክ። ሸዋ፣ ወሎ፣ ጎንደር፣ ጎጃም ሳይሆን አንድ ዐማራዊ መልክ። ልክ እንደ ትግሬ፣ ልክ እንደ ኦሮሞ ወንድም ጎረቤቶችህ ያለ መልክ። አዲግራቴ፣ ዓድዋ፣ ሽሬ፣ መቀሌ የሚል ታርጋ የተለጠፈበት መልክ ሳይሆን አንድ ትግሬ የሚሉት አይነት መልክ። ወለጋ፣ ባሌ፣ ጅማ፣ ሰላሌ፣ አሩሲ፣ ኢሉአባቦራ፣ ሀረርጌ፣ ሆሮጉዱር ሳይል አንድ ኦሮሞ ይሉት አይነት መልክ ይዞ አንድ ላይ ለጋራ ዓላማ እንደቆመው እንደ ኦሮሞ አይነት ይኑርህ እንጂ ሙያውን ከጎረቤት ትማረዋለህ። መልኩ ካለህ ሙያው ቀላል ነው ከጎረቤት ይቀሰማል። ይለመዳል።
"…አንዳንድ ዐማሮች እኛ እኮ በፋኖነት፣ በልዩ ኃይልነት ብንሰለጥንም መሣሪያ ግን የለንም። በምን ሠርጋችንን እናደምቃለን። ገንዘብም እኮ የለንም ሲሉ ተደብቄ እሰማቸዋለሁ። እውነት ነው ሁለቱም ላይኖርህ ይችላል። መጀመሪያ ግን መልክ ይኑርህ፣ ሰልጥን፣ በኮባም፣ በከዘራም ሰልጥን። የዐማራ አንገቱ አንድ ይሁን እንጂ ቀለብህንና መሳሪያህን የምታገኝበትን ሙያ ከጎረቤቶችህ ትማራለህ። ልምድም ትወስዳለህ። ልምድ መውሰድ እኮ ግሩም ነው። ተዘርፍጠህ፣ ተጎልተህ ተቀምጠህ መልክ ብቻ ይዘህ ሙያ ከሌለህም ዋጋ አይኖርህም። ቆሞ ቀር ሆነህ ትቀራለህ። ኧረ ጋሽ መልኬ ከጎረቤትህ ሙያ ተማር እንጂ። እህዕ? ኦነግ ገንዘብ ከየት እንዳገኘ ጠፍቶህ ነው? ሳትሰማስ ቀርተህ ነው?
"…ጃፓን እንዴት አደገች ብለህ ሩቅ ሠፈር ብትሆንም ስለ ጃፓን ሥልጣኔ ካልተመራመርክ፣ ካልጠየቅክ እንዴት ታድጋለህ? ጩጬ ሆና ሳለ እስራኤል እንዴት ጉልቤ ሆነች ብለህ ካልጠየቅ እንዴት ይገባሃል? ስለ ፑቲን የህይወት ታሪክ ሳታጠና ስለ ጃልመሮም፣ ስለ ደጺም ሳታውቅ እንዴት ፎለቲካው ይገባሃል? እህእ… መልክ ቢኖራቸውም ሙያ ስለሌላቸው ሃገር አልባ ስለሆኑት ኩርዶች እንዴት ሃገር አልባ እንደሆኑ ከወዲሁ ካልተማርክ ምን ዋጋ አለህ? አዎ መጀመሪያ መልክህን አንድወጥ አድርገህ አሳምር። ሙያው አለህ ባይኖርህም እንኳ ከጎረቤቶችህ ትማራለህ። ደግሞም ተማር። አትስነፍ።
"…ኦነግ ሸኔ እንዴት መልኩን አሳመረ ብለህ መጀመሪያ ጠይቅ? ቀጥሎ ገንዘብ ከየት አመጣ ብለህም ጠይቅ። ኦነግ ሩቅ እኮ አይደለም። በመርከብ አትሄድ፣ የሮጲላ ትኬት አያስቆርጥ፣ ቪዛ አያስጠይቅ፣ ቅርብ እኮ ነው ግድግዳችሁ አንድ የሆነ ጎረቤትህ እኮ ነው። ሳትሰንፍ ጠይቀው። እንዴት ገንዘብ አገኘህ ብለህ ጠይቀው። እሱ ባይነግርህ ግን እኔ እነግርሃለሁ። አንዳንድ ሰው ምቀኛ ነው። አይነግርህም። የምትበልጠው ይመስለዋል። ይኸውልህ ኦነግ ዲታ የሆነው ወደ 23 የሚጠጉ የኢትዮጵያ ባንኮችን በሃላል ዘርፎ ነው። እነ ዐቢይ አሕመድ፣ እነ ሽመልስ አብዲሳ ያስታጠቁት በዚህ መልክ ነው። ያውም የአንተው ገልቱዎች ደመአ መኮነን፣ ገዱ አንዳርጋቸው፣ ተመስገን ጡሩነህ፣ ዳግማዊት ሞገስ፣ አገኘሁና ላቀ አያሌው እያዩ ነው ፈረንካ ከባንክ የወሰደው። እነ ግብፅ፣ ዓረብ ሃገራት፣ ለኪስ ከሚሰጡት ውጪ በተጨማሪ ነው ኦነግ በላቡ፣ በጉልበቱ፣ በትበት ብሎ የታጠቀው። ይኸውልህ መጀመሪያ አንድወጥ ዐማራዊ መልክ ይኑርህ እንጄ ሙያ ከጎረቤት ነው መማር የምልህም ለዚህ ነው። ይሄ ሌብነት አይደለም። ይሄ በመሪዎች ቡራኬ ለኦነግ የተበረከተ ስጦታ ነው። ጥሎሽ ጭምር ነው። መሪዎች ልጆቻቸውን በዚህ መጠን ደብዳቤ ጽፈው ሰጥተው ሲያደራጁ ደስ ይላል።
"…ወያኔንም ተመልከት። መጀመሪያ ብጥስጥስ ያለውን መንደሬነት፣ ዓድዋ ሽሬ፣ አክሱም፣(ዓሽዓ) ነትን አጠፋች። አዲግራት፣ መቀሌነትንም አጥፍታ አንድ የትግሬነት መልክ ፈጠረች። መልኳን በአደስም፣ በደንደስም አሳመረች። አነ ትግራዋይ፣ አነ ተጋሩ የሚል መፈክርም ፈጥራ በዚያ መፈክር ጥላ ስር ሁሉንም ኮሎኮለች። ትግርኛ አቀላጥፎ ይናገር እንጂ ለሌላው ደንታ አልነበራትም። ወሎዬው ጌታቸው ረዳን፣ ጎንደሬውን አሉላ ሰለሞንን ፈረንካ፣ ሴትና ቡሌ አቅርባ በግድ የትግሬ መልክ አሰጠች። አንዴ ተጋሩ፣ አንዴ ባትጋሩኝ፣ እያለች ቆይታም ትግራዋይ የሚል ማንነት ፈጥራ መልኳን አንድወጥ አድርጋ አሳምራ አሰለፈች። የሚቀረው ሙያ ነበር። ሙያውን ከየት እንደተማረች ባይታወቅም ከመጀመሪያው ከመነሻዋ ባንክ በመስበር የጀመረችውን የሌብነት ሙያ አሳድጋ ለትንሽ ጊዜ የኢትዮጵያ ዕድር ሊቀመንበር በነበረች ጊዜ እድሩን ሠርቃ ከበረች። ከኢትዮጵያ ዕድር የቀራት አልነበረም ነው የሚባለው። ማንኪያ ነሽ፣ መርከብ ነሽ፣ ሮጲላ ነሽ። የቀራት አልነበረም። መከላከያውን ከነነፍሱ ትግሬ ምድር ወስዳ ተከለች። ልጆቿን በሙሉ በኢትዮጵያ ዕድር ስም በምታመጣው ብድር እና ዕዳ ዲታ አስደረገች። የኢትዮጵያን ዕድር ዘርፋ፣ በኢትዮጵያ ዕድር ሃብት፣ በኢትዮጵያ ብድር እና ዕዳ እስከ አፍንጫዋ ድረስ ታጠቀች። ግምጃ ቤቷም፣ ሊቀመንበሯም እርሷ ስለነበረች እናም ዛሬ በሰፈሩ ውስጥ እምቡር፣ እምቡር፣ ዊኒጥ፣ ዊኒጥ ስትል ትታያለች። እንዲህ በትበት ብላ ነው ወዩሂዊ ዛሬ ድረስ በቀረርቶም፣ በፉከራም እንደ ቄብ ዶሮ የምታስካካብን። መልክ ይኑርህ። አንድወጥ መልክ ይኑርህ።
"…እደግመዋለሁ እናም ዐማራ መጀመሪያ መልክ ይኑርህ። በደንብ ታጠብ። ይሄን የጎጠኝነት፣ የሰፈር፣ የመንደር ማድያትህን ፈግፍገህ አስለቅቅ። ዐማራ የሚለውን አንድ የሚያደርግህን ቅባት ደጋግመህ ተቀባ። በአናትህ ላይ ከተቀባኸው ወደ ውስጥህ ዘልቆ ይገባል። አትዘበራረቅ፣ እኔ ጎንደሬ የቴዎድሮስ ልጅ፣ እኔ ወሎዬ የንጉሥ ሚካኤል፣ እኔ ጎጃሜ የበላይ ዘለቀ፣ እኔ ሸዋዬ የምኒልክ ዘር እያልክ አራት ቦታ አትሰንጠቅ። አራት ቦታ ቆመህ አታቅራራ። በአንድ ላይ ፎክር፣ በአንድ ላይ አውራ። በአንድ ላይ ተነሥ። በአንድ ላይ ዝመት፣ በአንድላይ ድል ታደርጋለህ። የጎጥ ጭቅቅትህን በደንብ ታጥበህ ልክ እንደጎረቤትህ እንደ ትግሬና እንደ ኦሮሞ ዐማራዊ መልክህን አሳምር። ኦሮሞ ከባሌ አምጥቶ ሰላሌ ላይ ሰው ሲሾም ሰላሌ ኦሮሞ ተሾመ እንዲባል እንጂ የባሌ ሰው መጣብኝ እንዳይል ነው የደረጉት። አንተም ከእሱ ተማር። የሆነ ሰው ሲሾም ዐማራ ይሁን እንጂ የእኔ ሰፈር ሰው አይደለም ብለህ አትወብራ። መልክህን አሳምር። ሙያም ከጎረቤት ተማር። ትግሬም እንደዚያው ነው። ዓድዋ በሙሉ ትግሬ ላይ ሲሾም ትንፍስ የሚል የለም። ተማር ከትግሬ። ተማር ከኦሮሞ።
5.0K views07:35