Get Mystery Box with random crypto!

....

የቴሌግራም ቻናል አርማ zemdkunbekelez — .... Z
የቴሌግራም ቻናል አርማ zemdkunbekelez — ....
የሰርጥ አድራሻ: @zemdkunbekelez
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 27.66K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የቴሌግራም ቻናሌ ግንቦት1/2011ዓም የተከፈተ ነው።
ይህ የዩቲዩብ ቻናሌ ደግሞ ሰኔ 6/2012 ዓም ከራየን ወንዝ ማዶ የተከፈተ ነው።
https://www.youtube.com/c/ZemedkunBekele?sub_confirmation=1
እንደ ፌስቡክ፣ እንደ ቴሌግራሙ ሁሉ በዚህ መንደርም ለቤተ ክርስቲያኔና ለኢትዮጵያ ሀገሬ የሚጠቅመውን ሁሉ አበረክ ዘንድ አብዝታችሁ ጸልዩልኝ።

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 133

2022-09-05 08:27:29
• ስለ ምርኮው እንጠይቅ… ?

• እኔየምለው ይሄ ሁሉ የእኛ ወታደር እንዲህ በገፍ የሚማረከው ምን ሆኖ ነው? ምንስ ጎድሎት ነው? በስልጠናው ወቅትስ ምንአይነት ሥልጠና እየሰጡት ነው እንዲህ በጀማ ክፍለጦር ሙሉ እጁን አንከርፍፎ የሚማረከው?

• ከዚህ በኋላ አሁንም ለብርሃኑ ጁላ ከጦርነቱ መልስ ደግሞ ሌላ ተጨማሪ ማዕረግ ይሰጠው ይሆን?

• ተማራኪዎቹ ሲማረኩ እንደወያኔ ተማራኪዎች መሳሪያቸውን ለወገን ጦር ትተው ነው የሚማረኩት ወይንስ ኢትዮጵያ በዕዳ በዶላር የገዛችውን መሳሪያ እንደታጠቁ ነው የሚማረኩት? እንደዚያ ከሆነ ወያኔ የጦር መሳሪያ መግዛት ምናምን አያስፈልጋትም ማለት እኮ ነው?

• እንዲህ ጦሩን ፍርስርስ አድርገው የውጊያውን ዐውድ የለወጡት የጦር መሪዎች አሁን የት ናቸው? እነሱም ተማርከዋል ወይስ ወደ አዲስ አበባ ሸሽተው ተደብቀዋል? ለፍርድ ይቀርቡስ ይሆን?

• ይሄ እንግዲህ ህወሓቶች እንደሚሉት ከሆነ እነዚህ የምታዩዋቸውን የእኛን ወታደሮች በቆቦ ግንባር ብቻ የማረክናቸው ናቸው ብለው የለቀቁት ቪድዮ ነው። 110 ሚልዮን ትርፍ ተቀያሪ ደጀን ህዝብ ከኋላ ስላለ ነው እንጂ በእነ ብርሃኑ ጁላ ሥልጠና እንኳንም ግብፅና ሱዳን አልገጠሙን። ሽንፈቱ በአስቸኳይ ይመርመር። እንዲያው ልፋ ቢለኝ እንጂ አሁን ማን ይሙት ኦሮሞ ኦሮሞን ይመረምረዋል ብዬ እኮ አይደለም።

• እስከአሁን እንዲህ በገፍ የተማረከ ፋኖ እና የዐማራ ልዩኃይል አላየሁም። ለምን ይሆን?

• በጦርነት ላይ ምርኮ ያለ ነው። በዚህ መጠን ግን ምርኮ አስደንጋጭ ነው። የጦሩን አዛዦች አስሮ መመርመር አስፈላጊ ነው። ማእረጉን ቆርጠህ በጥሰህ ጥለህ ዘብጥያ መወርወር ነው። አንተም ስህተቱን አታርምና ደግሞ ይሄን አልክ ብለህ ዘመዴ ወያኔ ነው። ጁንታ ነው በለኝ አሉህ። ገተት።

• የጦሩ መሪዎች ይመርመሩ…!!
2.7K views05:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 16:20:18 መረጃ ቴሌቭጅንን በተመለከተ…!!

"…መረጃ ቴቭ ማለት እነ ኤልያስ ክፍሌ የሳታላይት የአየር ሞገዱን ገዙና በዚያ ላይ በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ የተለየ ሃሳብ አለን የሚሉ፣ በመንግሥት የፖለቲካ ቋት ውስጥ በሚተላለፉ የአየር ሞገዶች ውስጥ ሃሳባቸውን ለመግለጽ የማይፈቅድላቸው ኢትዮጵያውያን ሃሳባቸውን በነፃነት ይገልጹ ዘንድ የተከፈተ የሳታላይት ጣቢያ ነው።

"…መረጃ ቴቪ ለትርፍ ያልተቋቋመ እና ከየትኛውም የሃገር ውስጥና የውጭ ሃገር ተቋማት የገንዘብ ድጋፍ የማይደረግለት የቴሌቭዥን ጣቢያ ነው። እናም እስከ ቅርብ ዓመታት ድረስ ሁለት ደጋግ ባልና ሚስት ኢትዮጵያውያን እስከ ግማሽ ሚልዮን ዶላር አውጥተው በአየር ላይ ለማቆየት ሙከራ አድርገዋል። ጣቢያው ሃገር ቤት ገብቶም ሥራ ጀምሮ ነበር። መንግሥት ልክ እንደነ ኢሳት የካድሬ ሥራ ካልሠራህልኝ ውጣ፣ ድራሽ አባክ ይጥፋ ብሎ አስወጥቶታል።

"…የእኔን ከዩቲዩብ መባረር ተከትሎም መረጃ ቲቪ ለእኔ የአየር ሰዓት በነፃ ሰጥቶኝ ስንቀሳቀስበት ቆይቻለሁ። ወደፊትም በህይወት እስካለን ድረስ ይቀጥላል። መረጃ ቲቪ በዩቲዩብ ላይ ብቻ የሚታዩትን ኢትዮ 360 ዎችንም በነፃ የአየር ሰዓት ሰጥቶ ይንቀሳቀሱበት ዘንድ ዕድል የፈጠረ በአይነቱ የተለየ የቴሌቭዥን ጣቢያ ነው። የእኔ ዘመዴ ነጭ ነጯም ሆነ የኢትዮ 360 ዎቹ ፕሮግራም የተፈቀደልን በነፃ ነው። በመረጃ ቴቪላይ የአየር ሰዓት ከፍሎ ፕሮግራሙን የሚሠራ የለም። በነጻ ነው። ብዙዎች መረጃ ቴቪ የሁለታችን ሁላ ይመስላቸዋል።

"…እናም ከዓመት በፊት ጀምሮ እነዚያ ባለሃብቶችን ለማገዝ በመፈለግ የአየር ሰዓትንና አንዳንዳድ የቴክኒክ ወጪዎችን ብቻ ለመሸፈን የሚያስፈልገውን ወርሃዊ ዶላር ከኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያና ከኢትዮ 360 ጋር በመተባበር በጎፈንድሚ እየተሰበሰበ ስንከፍል ቆይተናል። አሁን ባለፈው ሳምንት መከፈል የነበረበት ክፍያ ባለመከፈሉ ምክንያት የመረጃ ቲቪ ክፍያ እስኪፈጽም ድረስ ለጊዜው ተቋርጧል።

"…ምንአልባት ዛሬ እኔ፣ ሀብታሙ አያሌውና ብሩክ ይባስ በምናቀርበው የጎፈንድሚ ስብሰባ ላይ የምናገኘው ብር መረጃን ያስቀጥለዋል።

"…በመረጃ ቴቪ ለዋልድባዎች ከ23 ሚልየን ብር በላይ ተሰብስቦላቸዋል። በመረጃ ቴቪ ቅዱስ ፓትርያሪኩ የታፈነ ድምጻቸው ተሰምቶበታል። በመረጃ ቲቪ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሃሳባቸውን ገልጸውበታል። መረጃ ቲቪ ለሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ከእነ ኢቢሲ፣ ከእነ ፋናና ዋልታ በተለየ መልኩ አማራጭ የመረጃ ምንጭ ሆኖ አገልግሏል። በወለጋ የታረዱ ዐማሮችን በድፍረት ለዓለም ህዝብ ያሳየው የመረጃ ቴቪ ብቻ ነው። እናም መረጃ ማለት ለገዢው ፓርቲ ኮሶ እሬት ለህዝቡ ደግሞ አማራጭ የመረጃ ምንጭ ነው።

"…እናም የመረጃ ፕሮግራም የተቋረጠው በዚህ ምክንያት ነው። የመንግሥትም የማንም እጅ የለበትም። ባልዋሉበትማ አልከሳቸውም። ችግሩ የገንዘብ ችግር ነው። አውቃለሁ ብዙ እናቶች፣ አባቶች፣ ወንድሞች፣ እህቶች መርሀ ግብራችንን እንደሚጠብቁ። ብዙ ፖለቲከኞችም እንደሚጠብቁ። ወዳጅም ጠላትም ምን ተባለ ብሎ እንደሚጠብቅ አውቃለሁ። እንዲያውም ዛሬ የግርማ የሺጥላን የቤተሰብ አገዛዝ የምዘረግፍበት ቀንም ነበር። እናም ለዛሬ አልተሳካም። ዛሬ ባይሳካም ነገ ይቀጥላል። ይሳካልም።

"…ይኸው ነው…!!
1.6K views13:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 16:20:18
"…መረጃ ቲቪ ለምን ተቋረጠ? ማን አቋረጠው? ከታች የጻፍኳትን ማስታወሻ አንብቧት። ለመጨቃጨቁ ካነበባችሁ በኋላ የመጨቃጨቂያ ሰንዱቁን እከፍትላችኋለሁ። እኔ ሃሳብ አልፈራም። እንደ ካድሬ በሬን ቆልፌ ብቻዬን ስንበጫበጭ አልውልም። አንብቡት።
1.5K views13:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 16:20:18
ትናንት ማታ…!!

"…በሸዋ ሮቢት ትናንት ማታ የዐማራ ልዩ ኃይሉ አዛዥ ከባጃጅ አውርዶ በገዛ ሽጉጡ መትቶ የጣለው ይሄ ልጅ ነው ተብሏል። ባለፈው ከህወሓትና ከኦነግ ጋር በነበረ ጦርነት ታላቅ ጀብዱ የፈጸመ የራሳ አናብስቶች የሽርጥ ለባሾቸ የእምቧይ በረት ልጅ ነው አሉ። አልሞ ተኳሽ የፋኖ እስናይፐር ተኳሽ ነበርም አሉ። በሰላም ሃገር በተጠና መልኩ በዐማራ ልዩ ኃይል አዛዡ በኩል በትናንትናው ምሽት ባላሰበው መልኩ እነ ግርማ የጂብጥላ አስበልተውታል።

"…ቀጣዩን መጠበቅ ነው።
1.4K views13:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 16:20:18
እዩልኝ ብቻ…!!

"…ጉድእኮ ነው ይሄኛው ዘመድኩን ደግሞ ጭራሽ ከእኔ የባሰ ደንቆሮና እልም ያለ ፈጣጣ አይደለም እንዴ እባካችሁ… ሃይ ያውም በኢትዮጵያ ቴሌኮም እኮ ነው የሚጠቀመው። ምኑ ጀዝባ ነው በማርያም። ለማንኛውም እኔ  "…ከዚህ የቴሌግራም ቻናል ውጪ ሌላ የቴሌግራም፣ የፌስቡክ አካውንትም የለኝም አልጠቀምም። ላልሰማ አሰሙልኝ።

"…ዩቲዩብ እኔን አባሮኛል። በእኔ ስም ከፍተው የራሴኑ ቪድዮ ለሚጭኑ ግን ዶላር ይከፍላል? ሳመለክት ደግሞ አይሰማኝም። ክሴንም አይቀበለኝም። ለፈጣሪ ሰጥቼ ከመቀመጥ በቀር ሌላ ምን እላለሁ።

"…ፌስቡክ እንድተነፍስ ስለማይፈቅድልኝ በፌስቡክ መጻፍ ካቆምኩ መንፈቅ ሊሞላኝ ነው። ነገር ግን ቴሌግራም ላይ የምጽፈውን እየወሰደ በእኔ ስም ፌስቡክ ላይ የሚጽፍ ነፍ ሌባ አለ። ፌስቡክ እሱን ምንም አይለውም። ዩቲዩብም ፌስቡክም እኔ እንድጠቀምባቸው ለእኔ አይፈቅዱልኝም። ነገር ግን በእኔ ስም የሚጠቀሙ ሐሰተኛ ዘመድኩኖችን ምንም አይሏቸውም። ግራየገባው ነገር ነው እኮ የገጠመኝ ጎበዝ።

"…ለማንኛውም ጀርመን መኖሬ በጀኝ እንጂ ሙከጡሪ ቢሆን ኖሮ ብላችሁ አስቡት። የመዓዛ አሸናፊ ፍርድ ቤት ፍዳዬን ያበላኝ ነበር። ወደ ጀርመን ቀድሞ ያስወጣኝ አምላኬ ክብር ምስጋና ይድረሰው። እኔ የምጠየቀው በእኔ አካውንት በተጻፈ የግል ሰሌዳዬም ላይ በሰፈረ ቃል ብቻ ነው። ይሄ የሚሆነው ታዲያ በጀርመን ስትኖር ብቻ ነው። ባለፈው ጊዜ እነ ይስሃቅ እሸቱ፣ እነ ካሚል በኒውዝላንድ በሞቱ እስላሞች ላይ ተሳልቋል ብለው የጀርመን ፖሊስ የሙከጡሪ ፖሊስ መስሏቸው ከሰውኝ ነበር። አንገታቸውን ሰብሮ መለሰልኝ እንጂ አካሄዳቸው አደገኛ ነበር። በአገር ቤት ስታይል ጀርመንን ሊሸውዱ የሚሞክሩ ደፋሮች።

"…እኔ ዘመዴ ነኝ። እኔን መምሰልም፣ መሆንም አይቻልም። ገተት ሁላ…!!

"…እንቀጥላለን…!!
1.5K views13:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 14:28:31
"…ኤሪዎቹ ደግሞ ተከዜን ተሻገርን እያሉ ነው። ይሄ ደግሞ የመቼ ይሆን? አሁንስ የት ደርሰው ይሆን…? መረጃው ያላችሁ ትግሬዎችም ሆናችሁ ዐማሮች ጀባ በሉን እስኪ። ተናጋሪ ወታደሩም ወሴ ነው የሚመስለው። ውኃውም የክረምት ውኃ አይመስልም።

• እርራ በሉ…!! መለትስ ምን ማለት ነው?
2.8K views11:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 14:28:31
ይሄ ሰገጤ ደግሞ…!!

"…ተመልከታት ይሄን ወሴ… ወይ ከወንድ አይገጥም። ወይ እንደወንድ የወንድ ሥራ አትሠራ፣ እንዲሁ ብቻ እንደ ሴት፣ መልኳን አሳምራ፣ ጸጉሯን ተቆንድዳ፣ እዩኝ እዩኝ እንደምትል ኮበሌ መንደር መንደሩን እየዞረ ኔትወርክ ሲያጨናንቅ ትዊላል።

"…ይሄ አይደለም ወታደር ፊት ሚሊሻ ፊት የማይቆመው ሰገጤ ሽንታም እኮ ነው ሰላማዊ ሰዎችን፣ ገበሬና ህጻናትን እያረደ፣ ንብረት እያወደመ፣ ሰልፊ ፎቶ ተነሥቶ እንደ ወንድ፣ እንደ ጀግና ጅግና ጀግና ሊጫወት የሚሞክረው። ቁንዲፍቱ ነገር።

"…አሁን በእሱ ቤት ጀት መትቶ መጣሏ ነው አይደል? አይ ቄሮ። ምድረ ዘራፊ ሁላ።

"…እኔ የሚገርመኝ በምን ሰዓታቸው ነው ግን በየትኛው ጊዜአቸው ነው ፀጉራቸውን አሳድገው፣ በዚያ ላይ ቅቤና ቅባት እየተቀቡ ሹርባ የሚሠሩት። መንጋ ግሪሳው በሙሉ እንደሴት ተዘርፍጦ ፀጉሩን ሲቆነደድ የሚውልበትን ሰዓት ከየት አገኘው? ብዬ ለመጠየቅ ፈለግኩና ለካስ የኦሮሚያ ልዩ ኃይል ነው። ቁጥር ሁለቱ።
2.8K views11:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 14:28:31
"…በህወሓት መንደር ጥይት ያልቅብናል፣ መሣሪያ ያጥረናል፣ ተዋጊ እናጣ ይሆን እንዴ ብሎ ፍርሃት የለም። በመሣሪያ በኩል የተዘረፈውም፣ የተበረከተለትም የትየለሌ ነው። በእሱ በኩል ሽግር የብለይ። ሟቾችም በሽበሽ ናቸው። የሟች፣ የተጋዳላይ እጥረትም የሚገጥማቸው አይመስላቸውም።

"…እየተደማሰሳችሁ…!!
2.7K views11:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 13:08:34
ተመቷል…!

"…የሽዋሮቢቱን ከንቲባ የገደለው የልዩ ኃይሉ አዛዥ ኮሎኔሉ ነው የሚል መረጃ እየወጣ ነው። ሰውዬው በዘሩ ቅማንት ነኝ እያለ በሸዋ እሳት መለኮስ አለበት ባይም ነው ይባላል። ከአሁን በፊት ሽዋሮቢት እርጉዝ ሴት ከነሕፃኖቿ እንድትገደል ትእዛዝ ሰጥቶ የአገር ሽማግሌዎች ለምን እርጉዝ ሴት ከነህፃን ልጆቿ ትገድላላች? ብለው ሲጠይቁት ገና ደግሜ እገድላለሁ። ምንታመጣላችሁ? እንዳላቸው ተሰምቷል።

"…በቅርቡ በአርሶአምባ የተገደሉትን ልዩኃይሎች በአሻጥር እንዳስጨፈጨፋቸው መረጃዎች እየወጡ ነው። ትናንት ምሽት ሽዋሮቢት ከተማ ላይ አንድ ባለባጃጅ ወጣትን ከባጃጁ አስወርዶ በራሱ ሽጉጥ ተኩሶ በአደባባይ ላይ ገድሎታል። የከተማውንም ሕዝብ መደዳውን መሬት ላይ አስተኝቶ በዱላ ራሱ እየደበደበ እንደነበረ ነው ትናንት ምሽት ስሰማ የነበረው።

"…ሰውዬው ሴትየዋን ከገደለና ልዩ ኃይሎቹን በአሻጥር ካስጨፈጨፈ በኋላ ልዩ ኃይሎቹ ሊገድሉት ሲል እነግርማ የሺጥላ ወደ ጎንደር ሄዶ እንዲሸሸግ አድርገውት ነበር። አሁን በመጣ በጥቂት ቀናት ውስጥ ነው የሽዋሮቢቱ ከንቲባ በቤቱ በራፍ ላይ የተገደለው። ያውም አጅበው የወሰዱት ፖሊሶች ርቀው ሳይሄዱ።

"…ይህ ሰው ከግርማ የሽጥላ የጋራ ዓላማ ያለው ሰው ነው። አቶ ግርማ ይፋትን ለኦነግ እንደሚሰጥ በገሃድ ነው የተናገረው። "ይፋት የኦሮሞ ነው ዐማራ ምን አገባው?” ብሎ ስብሰባ ላይ የተናገረ ከሃዲ ነው። ስለዚህ ሆን ብሎ ስውዬውን ልኮ ከንቲባውን ከገደለ በኋላ ፋኖ ላይ ጦርነት ከፍቷል።

"…አሁን በደረሰኝ መረጃ ደግሞ የልዩ ኃይል ሸዋሮቢት ላይ በሽጉጥ መመታቱንና ቆስሎም ደብረብርሃን ሆስፒታል መግባቱን ሰምቻለሁ። ነገርየው እየጠነከረ ነው። የሸዋ ትግል ወደ ህዝባዊነት እያመራ ነው። የምኒልክ ልጆች ምን አስበው ይሆን? እየተከታተልኩ አቀርብላችኋለሁ።

"…ሸዋዬ…!
3.5K views10:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 12:45:38
ስለ ጦርነቱ አዲስ መረጃ…!!

"…ደመሰስናቸው" ነው የሚለት ሁለቱም። በሺዎች የሚቆጠሩ የፋሺስቱ አቢይ አሕመድን ወታደሮች በዚህ ግንባር፣ በዚያኛው ዐውደ ውጊያ ይህን ያህል ደመሰስን፣ ይህን ያህል ማረክን ይላሉ የህወሓት ልሣኖችና አክቲቪስቶች። ደመሰስን ነው የሚሉት። ደመሰስን።

"…ደርብ ይላል የዚህኛው ወገን ደግሞ። ደርቤ ውቃው ይላል። በዚህና በዚያ ቦታ በድሮን በተደረገ የአየር ድብደባ የህወሓት የጦር መሳሪያ ማስቀመጫ መጋዘን፣ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ተደመሰሰ፣ በዚህና በዚያ የህወሓት ከፍተኛ የጦር መኮንኖች እንደሆኑ የተገመቱ ሰዎች የተሰበሰቡበት ቤት በድሮን ተደበደበ፣ በዚህና በዚያ ግንባር ደመሰስን፣ ተደመሰሱ ነው የሚሉት።

"…በዚህ ግርግር መሃል አበው "ግርግር ለሌባ ያመቻል" እንዲሉ ዐቢይ አሕመድ የቤት ዕቃ ሁሉ አውጥቶ የገዢ ያለህ እያለ ነው። ወያኔ ድሮ ዘርፋ ባስቀመጠችው፣ ከሰሜን ዕዝ ገፋ በከዘነችው፣ እንደ እባብ እየተሽሎከሎኩ በአውሮጵላን ወስደው ያራገፉላትም መሣሪያ አላት። በዚያ ላይ በየግንባሩ ትተውላት የሚሸሹትን ትጠቀምበታለች። ዐቢይ ግን ካልገዛ ከየት ያመጣዋል?

"…አንድ ጥይት ሲተኮስ ዶላር ነው የሚተኮሰው፣ አንድ ታንክ ሲቃጠል፣ አንድ ኦራል ሲወድም፣ አንድ ክላሽ ሲማረክ ዶላር ነው የሚከስረው። የሚተኮሰው፣ የሚቃጠለው፣ የሚማረከው ዶላር ነው። ሃገር ደግሞ ዶላር ከየት ታምጣ? ዳያስጶራውን እንዳይለምን ባለፈው አባሳጭቶታል፣ ሃገርቤት ሰው ደክርቷል። ችግር ነው። በደኅና በሰላሙ ጊዜ ጉራው ሃገር ይያዝልኝ የሚለው ችግኝ አቢይ አህመድ አሁን በጭንቁ ቀን ተደብቋል። ትንፍሽ አይላትም። የሟች ወታደር ችግር የለም። በሽ ነው። አሁንም ሌላዙር የሟች ማስታወቂያ ወጥቷል። እናም ስለጦርነቱ አዲስ መረጃ ያለኝ ይሄው ነው። እርስ በእርስ እየተደማሰስን ነው የሚሉት።

"…እየተደማሰሳችሁ…!!
3.6K views09:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ