Get Mystery Box with random crypto!

ዘማሪ ዲ/ን ፍፁም ከበደ

የቴሌግራም ቻናል አርማ zdfitsumkebe — ዘማሪ ዲ/ን ፍፁም ከበደ
የቴሌግራም ቻናል አርማ zdfitsumkebe — ዘማሪ ዲ/ን ፍፁም ከበደ
የሰርጥ አድራሻ: @zdfitsumkebe
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 22.71K
የሰርጥ መግለጫ

ዘማሪ ዲያቆን ፍፁም ከበደ

Ratings & Reviews

5.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 26

2022-09-10 23:34:30

ወትባርክ አክሊለ ዓመትከ
ወይፀግቡ ጠላተ ገዳም
ወይረውዩ አድባረ በድው።

" በቸርነትህ ዓመትን ታቀዳጃለህ ምድረ በዳውም ስብን ይጠግባል።" መዝ 65÷11


እንኳን አደረሰን! ፳፻፲፫




1.7K viewsማኔ ቴቄል ፋሪስ, 20:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-10 22:08:19 እንኳን ለዐዲሱ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ!!!

ዐዲሱ ዓመት ሕሊና አበውን ገንዘብ የምናደርግበት ዘመን እንዲሆን የአባቶቻችን አምላክ ይርዳን!
1.6K viewsወሰንየለው ባህሩ, 19:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-10 21:23:00 +++ "የእኛ የጥፋት ውኃ የሚጎድለው መቼ ነው?" +++

በኖኅ ዘመን የነበሩት ሰዎች አመጸኞች ሆኑ። የእግዚአብሔርን የምሕረት ጥሪ እምቢ ብለው መንገዳቸውን በፊታቸው አበላሹ። ምድሪቱንም በግፋቸው ሞሏት። ስለዚህም እግዚአብሔር ከትውልዱ ጻድቅ የነበረው ኖኅና ቤተሰቡን አስቀርቶ ሌሎቹን ከምድር ጋር ያጠፋቸው ዘንድ የጥፋት ውኃን አዘነመ። የታላላቅ ቀላያት ምንጮች ሁሉ ተነደሉ። የሰማይ መስኮቶችም ከፈቱ። ምድር በአምላክ የቁጣ ውኃ ተጥለቀለቀች። በመርከቢቱ ከነበሩት በቀር ምድር አንዲት  ነፍስ አልቀረላትም።

እግዚአብሔር ከዚህ ሁሉ ቁጣ በኋላ በመርከቡ የነበሩትን ኖኅንና እንስሳት አራዊቱን አሰበ። በምድርም ላይ ነፋስን አሳለፈ። የቀላያቱን ምንጮች የሰማዩንም መስኮቶች ደፈነ። ዝናሙንም ከሰማይ ከለከለ። ሞልቶ የነበረውም ውኃ ቀስ በቀስ እየጎደለ መጣ። በመጽሐፈ ኩፋሌ እንደ ተቀመጠው በውኃ ተጥለቅልቃ የነበረችው ምድር ግልጥ ሆና የታየችው በመጀመሪያው ወር መባቻ ላይ ነበር።(ኩፋ 7፥1)

ባለ ዘመኖቹ እኛ ልክ በኖኅ ጊዜ እንደ ነበሩት የቀድሞ ሰዎች ክፋታችን ተካክሏል። መንገዳችንን በእግዚአብሔር ፊት አበላሽተናል። ምድርን በግፋችን ሞልተናታል። ስለዚህ እግዚአብሔር በእነርሱ ላይ ያወረደው የጥፋት ውኃ ለእኛም ይገባን ነበር። እኛ ግን እርሱ እስኪቀጣንም አልጠበቅንም። እርስ በእርሳችን እየተጋደልን ምድራችንን በጥፋት ደም አጥለቀለቅናት። ወንድም ወንድሙን በጥይት ነደለ፣ በስለትም ሰውነቱን ከፈተ። የቁጣው ደም ከሰው እየመነጨ ምድርን ሸፈነ።

ታዲያ በዚህች ጎስቋላ ምድራችን ላይ የፈሰሰውን ደም የሚያደርቅ የይቅርታ ነፋስ መቼ ይነፍሳል? እንደ ውኃ ያጥለቀለቀንስ ደም መቼ ይጎድላል? የምንሰማው መጨካከንስ እያደር እያደር የሚቀለው መቼ ነው? አሁን እኮ የመጀመሪያው ወር (መስከረም) መባቻ ነው። ምድራችን የሸፈናት ጥላቻ እና መገዳደል ተገፍፎላት ዳግመኛ ግልጥ ሆና አናያትም?

የእኔ የአዲሱ ዓመት ስእለቴ ይህ ነው። የእናንተስ?

ዲያቆን አቤል ካሳሁን


https://t.me/akanim1wasen2
1.8K viewsወሰንየለው ባህሩ, 18:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-10 14:37:30 ዘመኖችህ አያልቁም


አሮጌውን አሮጌ ማለት ሚቻለው አዲስ ነገር ሲኖር ብቻ ነው አዲሱን ኪዳን ከእግዚአብሔር ስንቀበል የቀደመውን ኪዳን አሮጌ ብለነዋል ። ይህችን ሰማይ እና ይህቺን ምድር አሮጌ ብለን በአዲስ ሰማይ እና በአዲስ ምድር የምንተካበት ጊዜ ሊመጣ እንደሚችል ደግሞ ዮሐንስ ወንጌላዊ በራእዩ ይመሰክራል። ራዕ 21:1 ዘመንን ዘመን ሲተካው አዲስ ብለን የተቀበልነውን ዓመት ጥቂት ዓመት ወራት ካሳለፍን በኋላ አሮጌ ብለን ስንሸኘው መኖራችን የተለመደ ተግባር ነው ። ሌላው ቀርቶ ሰው ያህል ታላቅ ፍጡር እንኳን የሚተካው በመሆኑ ማርጀት አንዱ የሰው ልጆች መገለጫ ነው ሆኗል። ሶስት ነገሮች ብቻ በእርጅና ሳይለወጡ ፀንተው ይኖራሉ።

ለባሕርይው እርጅና የማይስማመው አምላካችን
ሰባቱ ሰማያት
ቅዱሳን መላእክት

ዘመን የማይቆጠርለት እና ከዘመናት በፈት የነበረው ኃያሉ አምላካችን እግዚአብሔር ዘመናትን የሚያስረጅ እንጂ ዘመናት የሚያስረጁት አይደለም በምንም ሆነ በማንም አይተካም ፣ አይለወጥም ፣ ሁል ጊዜ አዲስ ሆኖ ይኖራል እንጂ ታላቁ የእግዚአብሔር ሰው ይህን ታላቅጌታ የገለፀበት ቃል ምንኛ ድንቅ ነው። " አንተ ግን ያው እንተ ነህ ዘመኖችህም አያልቁም " (መዝ 101፥26-27) ነበር ያለው ። ሁሉን አሳልፎ እርሱ ግን ለዘላለም አዲስ ሆኖ ይኖራል። ከሁሉ በፈት እርሱ ነበረ ፣ የዛሬ ታላቅነቱ በትላንት ትንሽነት የተጀመረ አይደለምና ሁል ጊዜ "ዐብይ እግዚአብሔር እየተባላ ሲመሰገን ይኖራል።

ሰባቱ ሰማያት እና ቅዱሳን መላእክት ምንም እንኳን ከዘመናት መፈጠር በኋላ የተገኙ ፍጥረታት ቢሆኑም ከሌሎቹ ፍጥረታት ልዩ የሚያደርጋቸው ጸጋን የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር አጎናፅፏቸዋል። እርሱም የማያረጁና ኃይላቸው በድካም የማይለወጥ መሆኑ ነው ። የዚህም ሚስጥሩ በመላእክት ዘንድ እና በከተሞቻቸው ውስጥ ዘመን የማይቆጠር መሆኑ ነው ። ሁል ጊዜ በሰማይ ዛሬ እንጂ ትላንት እና ነገ የሉም። እድሜአቸው ቀናቸው የሚለካው ጨለማ ፀሐይ በሚያፈራርቀው በኢየሱስ ክርስቶስ መሆኑ ነው።


(ሊቀ ሊቃውንት ስምዓ ኮነ ከሕይወተ ማርያም መጽሐፍ የተወሰደ።)


የቻናሌ ቤተሰቦች እንኳን ለዘመነ ሉቃስ ለ2015 ዓ.ም አደረሰን

ዘማሪ ዲያቆን ፍፁም ከበደ



https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
2.3K views✞£iŧsûm✞, 11:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-10 07:44:52 አውደ ዓመት

፭ቱ ዘማርያ

JOINE JOINE


https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
2.2K views✞£iŧsûm✞, 04:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-10 07:43:37 አውደ ዓመት


ዘመን መጣልን ዘመን አዲስ ዓመት
ዘመን ተሰጠን ዘመን ዓዲስ አመት
ምስጋና ለእርሱ ለእግዚአብሔር
በሰማይ ቢሆን ደግሞ በምድር
ለዚህ ላበቃን አልፎን በፍቅር


አዝ

ደስ ብሎን መጣን ደስ ብሎን በምሕረቱ ምሮን
አምናን አሳልፎን
ቸርነቱ ደንቆን
ዘንድሮን ታግሶን
አበባዮሽ ለምለም (2)


ዘመን የሚሰጥ የሚጨምር
እርሱ ነውና እግዚአብሔር
ተመስገን በሉት አመስግኑት
ያላየ አለ ዛሬን በእውነት
ምስጋና ላደረሰን ለዚህ ቀን
ይባቤ ለጠበቀን እስካሁን

ደስ ብሎን መጣን ደስ ብሎን በምሕረቱ ምሮን
አምናን አሳልፎን
ቸርነቱ ደንቆን
ዘንድሮን ታግሶን
አበባዮሽ ለምለም (2)

ምድር አጌጠች ባደይ አበባ
የምድር ንጉስ ሆኖላት አንባ
ውበት የላት ካላንተ በቀር
ቀን የሚያወጣ የሚያሳምር
አኮቴት ላደረሰን ለዚህ ቀን
አንክሮ ይገባዋል ለአምላካችን

ደስ ብሎን መጣን ደስ ብሎን በምሕረቱ ምሮን
አምናን አሳልፎን
ቸርነቱ ደንቆን
ዘንድሮን ታግሶን
አበባዮሽ ለምለም (2)

ፍሬዋን ባርከህ አስደስታት
ወንዞቿ ይሙሉ ያለጉድለት
መሻቷን ፈፅም ትልሟንም ሙላ
ብልፅግናዋ አንተ ነህ ጌታ
ምስጋ ላደረሰን ለዚህ ቀን
አንክሮ ይገባዋል ለአምላካችን


ደስ ብሎን መጣን ደስ ብሎን በምሕረቱ ምሮን
አምናን አሳልፎን
ቸርነቱ ደንቆን
ዘንድሮን ታግሶን
አበባዮሽ ለምለም (2)

ያንሳል ማመስገን እርሱን በዘመን
ጭጋጉን ገፎ ብርሃን ላሳየን
የሁሉ ጌታ ባለቤት ነው
አይሾሙት ንጉስ በላይ ያለው
ምስጋና ላደረሰን ለአውድ ዓመቱ
በኛ ላይ ዘላለም ነው ምሕረቱ

ደስ ብሎን መጣን ደስ ብሎን በምሕረቱ ምሮን
አምናን አሳልፎን
ቸርነቱ ደንቆን
ዘንድሮን ታግሶን
አበባዮሽ ለምለም (2)

እጅሽን ዘርጊ በእምነት በተስፍ
ነገ ይነጋል ዛሬ ቢከ
ኪዳንሽ ይጠበቅ እንደ ትላንቱ
ሳይናድ ክብርሽ እንደ ትላንቱ
ሳይናድ ክብርሽ ያመሰረቱ
ኢትዮጵያ አመስግኚ በፅናት
የመጣው ያልፍልሻል በፀሎት
እርዳታሽ ከሰማይ ነው ካምላክሽ
እንባሽን ያብሰዋል ፈጣሪሽ

ከብረው ይቆዩ ከብረው
ከእግዚአብሔር ታርቀው
ንስሐ ገብተው ፀንተው
ለቅዱስ ቁርባን በቅተው
ከብረው ይቆዩ ከብረው(2)

እግዚአብሔር ይመስገ
ለዚህ ያበቃን
ላመት ያድርሰን
ፀንተን በእምነት



ዘማሪያን
ሊቀ ዲያቆናት ነብዩ ሳሙኤል
ዘማሪ ዲያቆን አቤል መክብብ
ዘማሪ ዲያቆን ሳምሶን ነጋሽ
ዘማሪት ምርትነሽ ጥላሁን
ዘማሪት ኢንጂነር ፍሲካ ፍስሐ
2.3K views✞£iŧsûm✞, 04:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-09 10:06:39 ዘመናትን የሚያስረጅ


ዘመናትን የሚያስረጅ
እርሱ ግን ማያረጅ
ሁሉንም ሲያሳልፍ
እርሱ ነው የማያልፍ

አዝ

የእጅህ በረከት ተዋበች በእድሜ
ምድርም በአበባ ፈክታ በልምላሜ
የምህረት ዓመት የምህረት ዘመን
ያቀዳጀህን ክበር ተመስገን

አንተ ነህ አልፍና ኦሜና
ምታድል እድሜ ሽበት ፀጋ
ዘላለም በዙፍንህ ኗሪ
ያከበረህን አክባሪ


አዝ


በቸርነትህ ነጋልን አዝማን
በምድሪቱም ላይ ወቷል ብርሃን
እድሜን ጨምረህ አቆምከን በክብር
ተቀኘን ለስምህ ላንተ ለእግዚአብሔር

አንተ ነህ አልፍና ኦሜና
ምታድል እድሜ ሽበት ፀጋ
ዘላለም በዙፍንህ ኗሪ
ያከበረህን አክባሪ


አዝ

የምድር ሃያላን ነገስታቱም ሁሉ
ትተውት ሄደዋል ዓለሙን በሙሉ
ባለፀጋም ሆነው ዓለሙን የገዙ
ትተውት ሄደዋል ምኑንም ሳይዙ

አንተ ነህ አልፍና ኦሜና
ምታድል እድሜ ሽበት ፀጋ
ዘላለም በዙፍንህ ኗሪ
ያከበረህን አክባሪ

አዝ

ለምህረት ሆኖ የሰማዩ ውሃ
ሳንጠፍ እንዳደልከን እድሜ ለንሰሃ
ከተጠሩት ብቻ ሆነን እንዳንቀር
ለመመረጥ እርዳን በመልካሙ ግብር


አንተ ነህ አልፍና ኦሜና
ምታድል እድሜ ሽበት ፀጋ
ዘላለም በዙፍንህ ኗሪ
ያከበረህን አክባሪ



ዘማሪ ዲያቆን እንዳለ ደረጀ

JOINE


https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
3.1K views✞£iŧsûm✞, 07:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-08 06:55:26 ጳጉሜ 3 ቅዱስ ቅዱስ ሩፍኤል


በቁስል ላይ የተሾመው ከከበሩ መላእክት አንዱ ቅዱስ ሩፋኤል ነው ሄኖ 6+3

መላእክት በተለያየ ተግባራት ላይ የተሾሙ ናቸው

መላእክት ስንል በሁለት ይከፈላሉ

ቅዱሳን መላእክትና ርኩሳን አጋንንት ተብለው

ቅዱሳን መላእክት በስራቸው ተቀድሰዋል ከብረዋል

ርኩሳን መላእክት በስራቸው ረክሰዋል ተዋርደዋል

ስራ ያረክሳል ስራ ይቀድሳል

የወደቁ መላእክት ርኩሳን እንላቸዋለን

የተቀደሱ መላእክትን ቅዱሳን እንላቸዋለን

ቅዱሳኑ በረቂቁ ዓለም ላይ ይኖራሉ መላእክት ረቂቃን ስለሆኑ በረቀቁ ሰማያት ላይ ይኖራሉ

ግዙፍ በግዙፍ ቦታ ይኖራል ረቂቅ በረቂቅ ቦታ ይኖራል ሰማያት ረቂቃን ናቸው ብሩሃን ናቸው መላእክትም ረቂቃን ብሩሃን ናቸው በሰማያት ይኖራሉ በመላእክት ዘንድ ጨለማ የለም
መጋቤ ሐዲስ ሄኖክ ፈንቴ
ፀሐይ ከሰማይ በታች ላሉ ፍጥረታት ታበራለች ለመላእክት አታበራም መላእክት ራ ሳቸው ብርሃን ናቸው ብርሀን ለጨለማ እንጅ ለብርሃን አይጠቅምም

አጋንንት ረቂቃን ቢሆኑም ቦታቸውን መዓርጋቸውን ክብራቸውን አጥተው ከመኖሪያቸው ከሰማያት ተባረው በጨለማው ዓለም ላይ ይኖራሉ ጨለማ ከጨለማ ጋር ተደምሮ ይኖራል
የእያንዳንዱ መልአክ የስራ ድርሻ አለው

አጋንንትን ደል በመንሳት ላይ የተሾመ መልአክ አለ

መካኖችን በማብሰር የተሾመ መልአክ አለ

መባርቅትን በማዘዝ የተሾመ መልአክ አለ

ደመናትን ውሃ አዝለው እንዲያዘንሙ የተሾመ መልአክ አለ

ዝናማትን መጥኖ በማዝነም የተሾመ መልአክ አለ

እጽዋት እንዲያለመልሙ እንዲያብቡ የተሾመ መልአክ አለ

ነፋሳት በምሕረት እንዲነፍሱ የተሾመ መልአክ አለ

ወንዞች ያለ ልክ ሞልተው ምድርን እንዳይደመስሱ የተሾመ መልአክ አለ

ሰው ያለጊዜው እንዳይጠፋ የተሾመ መልአክ አለ

በእንስሳት ላይ የተሾመ መልአክ አለ

በአራዊት ላይ የተሾመ መልአክ አለ

በአእዋፋት ላይ የተሾመ መልአክ አለ

ምድር የዘሩባትን እንድታበቅል የተሾመ መልአክ አለ

ቋንቋ ለመግለጥ የተሾመ መልአክ አለ

ሀገር ለመጠበቅ የተሾመ መልአክ አለ

ሕጻናትን በመጠበቅ ላይ የተሾመ መልአክ አለ

ቤተ ክርስቲያንን በመጠበቅ የተሾመ መልአክ አለ

በትዳር በማኅጸንና በቁስል ላይ የተሾመው መልክ ቅዱስ ሩፋኤል ነው

ሩፋኤል ማለት እግዚአብሔር ሐኪም ነው ማለት ነው

ቅ ሩፋኤል

መልአከ ከብካብ ይባላል
ሳራ ወለተ ራጉኤልን እና ጦብያ ወልደ ጦቢት አጋብቷልና

ፈታሔ ማኅጸን ይባላል
በሰይጣን የተዘጋው የሳራን ማኅጸን ፈቷልና ወላዶች ሲወልዱ በምጥ ጊዜ ማህጸንን የሚፈታ መልአክ ነው

ሰዳዴ አጋንንት ይባላል
አስማንድዮስን ከሳራ ጭን አውጥቶ አባሮታልና

, ፈዋሴ ዱያን ይባላል
የቆሰሉ ቁስለኞችን ይፈውሳልና

ምእራገ ጸሎት ይባላል
የዓመቱን ሁሉ ጸሎት የሚያሳርገው ቅዱስ ሩፋኤል ነውና

ከሳቴ አእይንት ይባላል
የታወረው የጦቢትን ዓይን አብርቷልና

❖ቅ ሩፋኤል ጳጉሜን 3 አራት መሰረታዊ ነገሮችን የፈጸመበት ዕለት ነው

1 አስማንድዮስን ከሳራ ጭን ድል ነስቶ ጦብያና ሳራን ያጋባበት የጦቢት እና የራጉኤልን ቤት የረዳበት ቀን ነው
አስማድዮስ የተባለው ሰይጣን ጸረ ትዳር ነው ሳራ ስታገባ ባሏን ይገልባት ነበር በየጊዜው ስታገባ እየገደለባት 7 ባሎች ሙተውባት በጭንቀት ትኖር ነበር ከዚህ በሇላ መልአኩ ቅ ሩፋኤል የአሳ ጉበት እጣን ጨምሮ ጦብያ እንዲያጥናት አዞት ጦብያ ሲያጥናት ከጭኗ አድሮ ቧሎቿን የሚገድልባት ሰይጣን አስማድዮስ እየጮኸ ከላዯ እንዲዎጣ ያደረገበት ቀን ነው

2 የታወረው የጦቢትን ዓይን ያበራበት ዕለት ነው
ጦቢት ደግ ሰው ነበርና የሞተ ሳይቀብር አይበላም ነበር ከዕለታት አንድ ቀን አንድ ሰው ተገሎ ዛፍ ስር ተጥሎ አየ ይህ ሰው የተገደለው በንጉሥ ነው

ነገሥታት ሥልጣናቸውን ለማቆየት ሲሉ የሚቃዎማቸውን ይገድላሉ እነሱ ለመኖር ሌላ ይገላሉ ንጉሡም እሱ በሥልጣን ለመኖር ነበር የገደለው

ሰው ፈርቶ መቅበር አልቻለም የከፍዎች ነገስታት ጭካኔ ከገደሉ በሇላ እንዳይቀበር ይከለክላሉ

ይህ ሰው እንዳይቀበር አዋጅ ወጥቶ ነበር ያን ጌዜ ጦቢት አጥቦ ሲገንዘው ወደላይ ቀና ሲል ወፍ ኩሷን ከዓይኑ ላይ ጥላበት ዓይኑ ጠፍቶ ነበር

መልአኩ ሩፋኤል የጦቢትን ልጅ ጦብያን ዓባትህን የአሳውን ሐሞት ዓይኑን ቀበው ብሎ አዞት ሲቀበው ዓይኑ በርቶለታል

3 በውሃ ላይ የታነጸችውን ቤተ ክረርስቲያኑን ያጸናባት ዕለት ነው

የቅዱስ ሩፋኤል ቤተ ክርስቲያን ከባህር ላይ ተሰርታ

አሳ አንበሪው ሊገለብጣት ሲል መልአኩ አሳ አንበሪውን በረምሁ ወግቶ እንዳትንቀሳቀስ ቁም ብሎ

በአሳ አንበሪው ላይ ቤተ ክረርስቲያኑ ጸንታ እንድትኖር ያደረገበት ዕለት ነው

4 የዓመቱን ጸሎት ወደአምላክ የሚአሳርግበት ዕለት ነው

ለአንድ ዓመተ ሙሉ የተጸለየው ጸሎት ቅድመ እግዚአብሔር የሚደርሰው ጳጉሜን ሶስት

በመልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል ነው

ቀኑም ርኅወተ ሰማይ ይባላል የሰማይ መከፈት ቀን ማለት ነው ነገር ግን ሰማይ የሚዘጋ የሚከፈት ሁኖ አይደለም የተጸለየው ጸሎት ሰማያትን አልፎ ቅደመ እግዚአብሔር ስለሚደርስ ነው እንጂ

ጳጉሜን 3 ቅዱስ ሩፋኤል ከደረጋቸው ተዓምራት መካከል እነዚህ ናቸው የቅዱስ ሩፋኤል አማላጅነት አይለየን

(መጋቤ ሐዲስ ሄኖክ ፈንቴ)


የቻናሌ ቤተሰቦች እንኳን አደረሳቹ።

ዘማሪ ዲያቆን ፍፁም ከበደ


JOINE JOINE


https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
484 views✞£iŧsûm✞, 03:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-07 22:09:30                       
                      
                      
                      
         ️
        
                      
                      
                       ️
                      
                      
                      
▬ ▬ ▬ ▬ ይ ላ ሉን። ▬ ▬ ▬ ▬
239 viewsማኔ ቴቄል ፋሪስ, 19:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-07 20:48:28 አባቶች ይህንን ይመክሩናል
እኛ የአባቶቻችን ልጆች ነን
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን

ለኦርቶዶኮስ አማኞች ብቻ የተከፈተ ቻናል ።
ክርስትናችን እንዳንኖረው የሚያደርጉን ምክንያቶች በእውኑ ታውቋቸዋላችሁ?
ለዚህ ችግር አባቶች ምን አሉ? የምትፈልጉትን ለማግኘት ወደ ቻናላችን ተቀላቀሉ

ይህ ምክረ አበው ነው ሁላችሁም ተቀላቀሉ ትጠቀሙበታላችሁ open የሚለውን በመንካት ይቀላቀሉን
ⓄⓅⒺⓃ
ⓄⓅⒺⓃ
ⓄⓅⒺⓃ
528 viewsማኔ ቴቄል ፋሪስ, 17:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ