Get Mystery Box with random crypto!

ዘማሪ ዲ/ን ፍፁም ከበደ

የቴሌግራም ቻናል አርማ zdfitsumkebe — ዘማሪ ዲ/ን ፍፁም ከበደ
የቴሌግራም ቻናል አርማ zdfitsumkebe — ዘማሪ ዲ/ን ፍፁም ከበደ
የሰርጥ አድራሻ: @zdfitsumkebe
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 22.71K
የሰርጥ መግለጫ

ዘማሪ ዲያቆን ፍፁም ከበደ

Ratings & Reviews

5.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 23

2022-09-27 08:10:06
✞ የፍቅሩ ምልክት ✞

የክርስቶስ የድል አድራነቱ እና የፍቅሩ ምልክት የሆነው መስቀል የሚሰራበት ቁስ ለመልካም አገልግሎት ስለዋለ ክብር ይገበዋል ፤ ማንኛቸውም ፍጥረታት ለመልካም አገልግሎት ሲውሉ ይከብራሉ ። የዮሴፍ ታሪክ ለዚህ ምሳሌያዊ ማሳያ ሆኖ በክርስትና ሊቃውንት ይቀርባል ። በመጽሐፍ ቅዱስ የያዕቆብ ልጆቸ ወንድማቸውን ዮሴፍን በምቀኝነት ወደ ግብፅ በባርነት ከሸጡት በኋላ አውሬ የበላው በማስመሰል ለሽማግሌው አባታቸው ለያዕቆብ የዮሴፍን እጀ ጠባብ (ልብስ) ደም ቀብተው ሰጡት ። ያዕቆብ ልጁን በግብፅ ንጉስ ሆኖ እሲኪ ያገኘው ድረስ ይህችን ልብስ ይዞ ለልጁ ያለውን ፍቅር ይገልጥ ነበር ።

የዮሴፍ ልብስ ያዕቆብን ልጁን ዳግም እስኪ ያገኘው ድረስ በሐዘን  ለተጎዳው ያዕቆብ  መጽናኛ ሆኖ ስለነበር ያዕቆብ በክብር ጠብቆታል። ክርስቲያኖችም ክርስቶስ ዳግም እሲኪመጣ ድረስ የመምጣቱ ምልክት የሆነውን መስቀል ይዘው ይኖራሉ ፤ ያዕቆብ የልጁን መታሰቢያ የሆነችውን ልብስ እንዳ ከበራት ክርስቲያኖችም የክርስቶስ ምልክት የሆነውን መስቀል እና የተሰራበትን ቁስ ያከብራሉ ፤ በመስቀል አንጻር የሚያመልኩት ግን ክርስቶስ ነው፤ማክበርና ማምለክ ፈጽሞ የተለያዩ ነገሮች ናቸውና።


የቻናሌ ቤተሰቦች እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ አደረሳቹሁ *


ዘማሪ ዲያቆን ፍፁም ከበደ 


https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
817 views✞£iŧsûm✞, 05:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-27 04:27:21
.

ለፕሮፋይል ፒክቸር የሚሆኑ መንፈሳዊ ፎቶዎችን ማግኘት ይፈልጋሉ መልሶት አዎ ከሆነ ከስር ያለውን ሊንክ በመጠቀም ማግኘት ይችላሉ


https://t.me/+YkS5xznutqNjZTE0
https://t.me/+YkS5xznutqNjZTE0
https://t.me/+YkS5xznutqNjZTE0
149 views✞£iŧsûm✞, 01:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-26 22:25:12 እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳቸሰሁ



◌ አዳዲስ ዝማሬዎች

◌ የበዓላት ዝማሬዎች

◌ ቆየት ያሉ ዝማሬዎችን እና

◌ ሙሉ የማኅቶት ቲዩብ ዝማሬዎችን

በ ኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ መዝሙሮች የቴሌግራም ቻናል ማግኘት ይችላሉ ሊንኩ

      @Orthodox_Mezmure
      @Orthodox_Mezmure
      @Orthodox_Mezmure



እንዲሁም የመስቀል ዝማሬዎችን ከአሁኑ ማግኘት የምትፈልጉ ሊንኩ

      @Yemeskel_Mezmuroch
      @Yemeskel_Mezmuroch
      @Yemeskel_Mezmuroch
385 views✞£iŧsûm✞, 19:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-26 11:26:12 ✞ የመስቀሉ መቀበር ✞

አይሁድ ግን ቅዱስ መስቀሉ በፈታቸው ልዩ ልዩ ተአምራትንና ብዙ ምልክቶችን ሲያደርግ እያዩ ማመን ተሳናቸው ቀደም ሲል ጌታ በመካከላቸው በሕይወት /በአካል/ እየተመላለሰ በሽተኞችን እየፈወሰ ሙታንን እያስነሳና
ኅብስት አበርክቶ እየመገበ ብዙ ተአምራት እያደረገ ቢያስተምራቸው ቀንተው ተመቅኝተው ገርፈውና ሰቅለው እንደገደሉት ሁሉ ይህንም ቅዱስ መስቀል ወደ ቆሻሻ ቦታ ከመጣላቸውም በላይ መሬት ቆፍረው ቀብረውት ነበር።

አይሁድ ንጹሐን መሰቀል በቆሻሻ ሲቀብሩ ከነጭራሹ ስመዝክሩ እንዲጠፍ ተረስቶ እንዲቀር ለማድረግ ከሁሉ በታች የጌታ መስቀልን አድርገው ሁለቱ ሽፍቶች ፈያታዊ ዘየማንና ፈያታዊ ዘጸጋም አብረው የተሰቀሉባቸው መስቀሎችንም አከታትለውና ደርበው ከቀበሩት በኃላ የከተማውን ቤት ጥራጊ ሁሉ በላዩ እንዲደፍ ዓዋጅ በማስነገር ተራራ እስኪያህል ድረስ በቆሻሻ አስደፍነው ነበር ።
በዚህ ዓይነት ከሁለት መቶ ዓመት በላይ ዘመን በማስቆጠርና ተከታታይ ትውልድን በማሳለፍ እየተረሳና ደብዛው እየጠፍ ከመሄድ በስተቀር የሚያስታውሰውና የሚያውቀው አልነበረም ። አይሁድ ይህንን ማድረጋቸው ኢትዮጵያዊው ቅዱስ ያሬድ <<መስቀል መልዕልተ ኩሉ ነገር>> መስቀል ከሁሉ በላይ ነው ሲል እንደተናገረው የማያቋርጥ የእግዚአብሔር ኃይል መገለጫ መሆኑን ባለመገንዘባቸው ነበር ።

ይሁን እንጂ ጌታ በቅዱስ ወንጌሉ << እስመ አልቦ ክዱን ዘኢይትከሰት ወአልቦ ኅቡዕ ዘኢይትዐወቅ>> የማይገለጥ የተከደ የማይታወቅ የተሰወረ ምንም የለምና ሲል አስቀድሞ እንደተናገረውና ሁሉ (ማቴ 1.፥26 ሉቃ 12፥2) ከሰው ኃይል ይልቅ የእግዚአብሔር ኃይል ከሰው ጥበብ ይልቅ የእግዚአብሔር ጥበብ ይበልጣልና እነሱ በሚገለጽባቸው ተአምራት ምልክቶች የተሰወረ እንዲወጣ ፈቃዱ በመሆኑ ለዚህ ምክንያት የሚሆኑትን ንጉስ ቆስጠንጢኖስን ቅድስት እሌኒን የቅዱስ መስቀልን እና መገኘት ምክንያት አድርጎ አስነሳ ።


( ፍኖተ ስብከት ሊቀ ስዩም አዲሱ ላቀው)


ዘማሪ ዲያቆን ፍፁም ከበደ


https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
271 views✞£iŧsûm✞, 08:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-26 07:29:22 ✞ የመስቀል እንቅፍት ተወግዷል ✞
(ገላ 5፥11)
የዓለምን መድኃኒት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን አይሁድ በምቀኝነት ሰቅለው ፤ከገደሉት በኃላ ሕግ መተላለፍቸውንና አንዳች በደል ያልተገኘበትን ጌታ በመግደላቸው ሕግ ተላልፈው ጻድቁን ገደሉት ይሉናል በማለት እና የመስቀሉን ተአምራት በማየት ክርስቲያኖችን እንዳይድኑበት መሰቀሉን ጉድጓድ ቆፍረው ቀበሩት። ጌታችን ክብር ምስጋና ይድረሰው እና በደል ሳይኖርበት ዓለምን ለማዳንና የሰው ልጅ ሁሉ ከኃጥያት እና ከበደል ነፃ ለማድረግ ሲል እንደ በደለኛ ከአመፀኞች ጋር ተቆጥሮ አይሁድ በግፍ በሰቀሉት ጊዜ ክቡር አካሉ ያረፈበትን እጅ እግሩ በችንካር ጎኑ በጦር ተወግቶ ደሙ የፈሰሰበት መበሆኑ ከዕፀዋት ሁሉ የላቀ ክብርና ሞገስ ያለው ቅዱስ ነው ።

የክብር ባለቤት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በክቡር ደሙ ያከበረው በቅዱስ ስጋው የቀደሰውና መለኮታዊ ኃይሉና ባሕርያዊ ሕይወቱ ያረፈበት ስለሆነ ኃይልና የጥበቡ መገለጫ ነው ። ጌታ ከትንሳኤውና ከዕርገቱ በኋላ ድውያንን በመፈወስ ሙታንን በማስነሳት አንካሶችን ዕውራንን በማዳን ተአምራቱንና ኃይሉን መግለጽ የጀመረውም በቅዱስ መስቀሉ ነው። ከዚህ የተነሳ የዳኑትና ይህን ድንቅ ተአምር የተመለከቱ ሁሉ ሕይወትና ቤዛ የመሆን ጸጋ የተሰጠው መሆኑን እያመኑ መስቀል ኃይላችን መስቀል ቤዛችን የነፍሳችን መድኃኒት ነው እያሉ የጸጋ የአክብሮት ስግደት የሚሰግዱለት ሁነዋል ።

( ፍኖተ ስብከት ሊቀ ስዩም አዲሱ ላቀው)



ዘማሪ ዲያቆን ፍፁም ከበደ


https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
732 views✞£iŧsûm✞, 04:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-25 13:07:00 የጥያቄ መልስ

ጌታ በተሰቀለበት ዕለት የቤተ መቅደስ መጋረጃ መቀደድን ፦

የቤተ መቅደሱ መጋረጃ መቀደድ ጌታችን በተሰቀለበት ዕለት ከተፈጸሙት ሰባቱ ድንቆች አንዱ ነው ። መናፍቃን መገራጃው መቀደዱን ጠቅሰው የቤተ መቅደስ አገልግሎት ተሽሯል ይላሉ ። ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ደግሞ የመጋረጃው መቀደድ ሚስጥሩ በጌታ መከራና ሞት የጥል መጋረጃ መቀደዱን ፣ በአዳም እና በአዳም ፈጣሪ መካከል ዕርቀ ሰላም መደረጉን ያሳያል ብለዋል ። 133 በዕለተ ዓርብ ጌታ ሲሰቀል ከመጋረጃ መቀደድ በተጨማሪ ፀሐይና ጨረቃ ብርሃናቸውን አጥተው በምድር ሁሉ ጨለማ ሆና እንደ ነበር ተጽፏል (ማቴ 27፥45) የመጋረጃው መቀደድ የታቦት እና የመቅደስ ዘመኑ ማብቃቱን ያሳያል ከተባለ በወቅቱ ብርሃናቸውን ያጡ ፀሐይና ጨረቃም የአገልግሎት ዘመናቸውን ማብቃት ነበረበት ። ነገር ግን ፀሐይና ጨረቃ ዛሬም ድረስ ስራቸውን እየሰሩ አሉ ።

ሐዋርያትም ከጌታ ዕርገት በኋላ ኃይለ መንፈስ ቅዱስን ለመቀበል ጌታ የነገራቸውን ተስፍ የጠበቁት በቤተ መቅደስ አንደ ነበር ተጽፎልናል ።
" እነርሱም ፤ ሰገዱለትና በብዙ ደስታ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ ፥ ዘወትርም እግዚአብሔርን እያመሰገኑ እና እየባረኩ በመቅደስ ኖሩ " እንዲል ሉቃ 24፥52-53። ሐዋርያት በበዓለ ኅምሳ መንፈስ ቅዱስን ተቀብለው መንፈሳዊ አገልግሎት ከጀመሩ በኋላም ዕለት ዕለት ለጸሎት ወደ ቤተ መቅደስ ይሄዱ እንደ የበር ተጽፏል። "ጴጥሮስ እና ዮሐንስም በጸሎት ጊዜ በዘጠኝ ሰዓት ወደ መቅደስ ይወጡ ነበር " እንዲል (ሐዋ 3፥1 ) ። ለምን ከተባለ በመቅደሱ የሚጸለየውን ጸሎት ለመስማት እግዚአብሔር ለቀደሙት አባቶች ቃል ኪዳን ገብቶላቸውልና ። "በዚህ ስፍራ ለሚጸለይ ጸሎት ዓይኖቼ ይገለጣሉ ፥ ጆሮቼም ያደምጣሉ ። አሁንም ስሜ ለዘላለም በዚህ ይኖር ዘንድ ይህን ቤት መርጫለሁ ቀድሻለሁም ዓይኖቼ ልቤም ዘወትር በዚያ ይሆናሉ " እንዲል (2ኛ ዜና 7፥15-16) ። ታዲያ ቤተ መቅደስ ተሻረ የሚሉት ምን ማስረጃ ይዘው ነው ? ምላሹን ለመናፍቃኑ ትቻለሁ ።


( "እውነተኛ ክርስትና" ተስፍዬ ምትኩ )


ዘማሪ ዲያቆን ፍፁም ከበደ


https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
745 views✞£iŧsûm✞, edited  10:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-24 12:38:23
እንኳን ደስ አሎት አባታችን

ክብር ዶክተር ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ


https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
2.1K views✞£iŧsûm✞, 09:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-24 10:48:59
"ባሕርዳር ገብተዋል ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ"

የክብር ዶክተር ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የተበረከተላቸውን የክብር ዶክትሬት ለመቀበል ባሕርዳር ከተማ ገብተዋል።

ዛሬ ረፋዱን ወደ ባሕርዳር ሲገቡ ብፁዓን አባቶች፣ ሊቃውንት፣ የመንግስት ከፍተኛ አመራሮችና የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራሮች በባሕር ዳር ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ተገኝተው ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

ከደቂቃዎች በኋላ በባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ ተገኝተው በደማቅ ሥነ-ሥርዓት የክብር ዶክትሬታቸውን ይቀበላሉ።

ምንጭ ፦ ባሕርዳር ዮንቨርስቲ


https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
2.1K views✞£iŧsûm✞, edited  07:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-24 08:12:49 ✞በዓለ መስቀል✞

ቤት ከነጉልላቱ ቅጽር ከነማዕዘንቱ መውረስ የሚችለው በኩር ነው፡፡ ሀገራችን የብሉይም የሐዲስም በኩረ አሚን ናትና የጽላት እና የመስቀል ወራሽ ናት፡፡
መስቀል ከመስከረም 10ቀን ተቀጸል ጽጌ ጀምሮ እስከ መስከረም 25ቀን በበዓልነት መስቀል ይከበራል፡፡
ይኸውም ወደኢትዮጵያ ከገባበት ከ ሦስት ዓመት ከሦስት ወር ባርኮተ ኢትዮጵያ በሁዋላ ግሸን አንባ እስከተቀመጠበት ድረስ ያለውን ያሳያል፡፡
መስቀል ለእኛ ለኢትዮጵያውያን ድርብ በዐል ነው በእሌኒ የተፈጸመው ታሪክ እና ወደሀገራችን የመጣበት ሲደመር በሰንበት ላይ ደብረ ዘይት ነው፡፡
ንዑስ ደመራ የህዝብ ነው ዐቢይ ደመራ ግን አጤ ደመራ ይባላል፡፡
1 ሕጨጌ ደመራ ፦የአቡኑ
2 ሐጤ ደመራ ፦የንጉሡ
3 እቴጌ ደመራ ፦የንግሥት
4 ባለጌ ደመራ ፦ የባለጊዜ ነው፡፡
በዋዜማው የሚቃጠለው ህዝበ ደመራ ይባላል በየመንደሩ የሚደረግ ህዝቡ በአቅራቢያው የሚያከብረው ነው፡፡ይህ ሥርዓት በሁሉም ቦታዎች ያለ ቢሆንም ይልቁንም በጎንደር እንደተጠበቀ ይገኛል፡፡
በ17ጧት አጤ ደመራ ይባላል ሁሉም በአንድነት ከንጉሥ ደመራ በመገኘት የሚከበር ነው፡፡
ደመራው ከተቀጸል ጽጌ ገብረ መስቀል ሐጼጌ ጀምሮ ለዘመናት በቅዱስ ቅብብሎሽ ነው የመጣው፡፡በተቀጸል ጽጌ የጌታ አክሊለ ሦክ አምሳል በጉንጉን አበባ ለንጉሡ ይሰጣል አሁን የንጉሡ አክሊለ ሶክ ተቀጸል ጽጌ ማረፊያ ቢያጣ በደመራው ይቀመጣል፡፡
ደመራ ትናንትን የምናይበት እውነት ነው
ዛሬም የምኖርበት አሁን ነው
ለነገም የምንመለከትበት ፍኖተ ህሊና ነው፡፡
ትናንት መሠረት፣ዛሬ ግድግዳ፣ ነገ ጣራ ነው፡፡ትናንት የሌለው ዛሬ የለውም፡፡ዛሬ የሌለውም ነገ ምናብ ነው፡፡
ደመራ፦ ወድሙር ኩሉ ንዋዮሙ፡፡

(መምሕር ገብረ መድኅን እንየው )

https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
2.2K views✞£iŧsûm✞, 05:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-24 02:10:38 እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳቸሰሁ



◌ አዳዲስ ዝማሬዎች

◌ የበዓላት ዝማሬዎች

◌ ቆየት ያሉ ዝማሬዎችን እና

◌ ሙሉ የማኅቶት ቲዩብ ዝማሬዎችን

በ ኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ መዝሙሮች የቴሌግራም ቻናል ማግኘት ይችላሉ ሊንኩ

      @Orthodox_Mezmure
      @Orthodox_Mezmure
      @Orthodox_Mezmure



እንዲሁም የመስቀል ዝማሬዎችን ከአሁኑ ማግኘት የምትፈልጉ ሊንኩ

      @Yemeskel_Mezmuroch
      @Yemeskel_Mezmuroch
      @Yemeskel_Mezmuroch
10 views✞£iŧsûm✞, 23:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ