Get Mystery Box with random crypto!

ዘማሪ ዲ/ን ፍፁም ከበደ

የቴሌግራም ቻናል አርማ zdfitsumkebe — ዘማሪ ዲ/ን ፍፁም ከበደ
የቴሌግራም ቻናል አርማ zdfitsumkebe — ዘማሪ ዲ/ን ፍፁም ከበደ
የሰርጥ አድራሻ: @zdfitsumkebe
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 22.71K
የሰርጥ መግለጫ

ዘማሪ ዲያቆን ፍፁም ከበደ

Ratings & Reviews

5.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 25

2022-09-17 06:52:56 | አንዳንድ ጊዜ የእግዚአብሔር ቃል |

አንድ ሰው መፍትሔ የሌለው የሚመስል መከራ ሊገጥመው ይችላል ። በዚህ ጊዜ የእግዚአብሔር ድምፅ መከራው የገጠመው ጥቂት ኃጢአቶችን ስለ ፈጸመ መሆኑን ከማስጠንቀቂያ ጋር ይነግረዋል ። አንዳንድ ጊዜ ደግሞ ቃሉ ንስሓ ከገባህ መከራው ፍጻሜ ያገኛል እያለ ውስጡን ሲመክረው ይሰማል ። ከዚህ በኋላ እግዚአብሔር ስለ ንስሓው ሲል ለሰውየው ይራራለታል ።

የእግዚአብሔር ድምፅ አንድ ሰው ሲ
ታመም ወይም እርሱ የሚወደው ሌላ ሰው ሲታመም ሊመጣ ይችላል ። በዚህ ጊዜ እንዲጸልይ ወይም ስእለት እንዲሳል የሚመክረውን ድምፅ ከውስጡ ይሰማል ይህ ድምፅ የእግዚአብሔር ድምፅ ነው ።


የዮሴፍ ወድሞች እህል ሊገዙ ወደ ግብጽ ከወረዱ በኋላ በዚያ ችግር ሲገጥማቸው እርስ በእርሳቸው እንዲህ በማለት ተነጋግረው ነበር ፦ " በእውነት ወድማችንን በድለናል እኛን በማማጠን ነፍሱ ስትጨነቅ አይተን አልሰማነውና ። ስለዚህ ይህ መከራ መጣብን ።"/ ዘፍ 42*21/ ። ከዚህ በኋላ ለዮሴፍ እንዲህ ብለውታል ፦ " ለጌታዬ ምን እንመልሳለን ? ምንስ እንናገራለን ? ወይስ በምን እንነጻለን ? እግዚአብሔር የባሪያዎችህን ኃጢአት ገለጠ ..."/ዘፍ 44*16/ ኃጢአታቸውን እንዲያስታውሱ ኀላም እንዲገሰጹ ያደረጋቸው የእግዚአብሔር ድምፅ ነው ።
ነቢዩ ዳዊት የጌራ ልጅ በሆነው በሳሚ ሲሰደብ የእግዚአብሔር ድምፅ ውስጡን ስላለፈ ኃጢአቱ  እየወቀሰው መሆኑን አዳምጧል ። ስለሆነም በዙሪያው ለነበሩ ሰዎች " "እግዚአብሔር ዳዊትን ስደበው ብሎታልና ይርገመኝ ። / 2ኛ ሳሙ 16*10/ በማለት በግልጽ ተናግሯል ።


ረሀብና የመሬት መንቀጥቀጥ በዓለም ሲደርስ የእግዚአብሔር ድምፅ በመላው ዓለም ውስጥ ይሰማል ። በዚህ ጊዜ የእግዚአብሔር ድምፅ የሚናገረን " ወደ እኔ ተመለሱ እኔም ወደ እናንተ እመለሳለሁ ።" / ሚል 3*7/ እያለ ነው ። ይህ ድምፅ በረሀቡ ወይም በመሬት መንቀጥቀጡ ጉዳት ለደረሰባቸው ሀገሮች የሚሆን የእርዳታ ጥሪ ለማሰማት ወይም ሌሎቹ ከእነርሱ ትምህርት በመውሰድ ንስሓ እንዲገቡ ለማድረግ ወይም ከእግዚአብሔር ጋር ለመገናኝት ዝግጅት እንዲያደርጉ ነው ።

ስለዚህ ማንኛውም ዓይነት መከራ ውስጥ ስትገቡ ከውስጣችሁ ያለውን የእግዚአብሔር ድምፅ አድምጡት እርሱ ለእናንተ ሊነግራችሁ የሚወደው ምን እንደ ሆነ ታውቃላችሁና ።

| ቅዱስነታቸው አቡነ ሺኖዳ ፫ኛ |

https://t.me/akanim1wasen2
3.5K viewsወሰንየለው ባህሩ, 03:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-16 15:08:05
ሀገራዊ ቀውስ ፤ ቤተ ክህነታዊ ንቅዘት ሰሞነኛ ክስተቶች ብቻ አይደሉም። አዝማናት የባጁት ጭምር እንጂ ። የዛሬውንም ኾነ የነገውን ቤተ መንግስታዊ እና ቤተ ክህነታዊ ቁመናዎች የመወሰን ዐቅም የአላቸው ቀውሶች የሚወለዱት ከዛሬው ብቻ ሳይኾኑ ፥ ከትላንት የጥፍት ማድጋዎችም ጭምር ነው ። ዛሬን እና ነገን ለመፈወስ ትላንትን በመገነዛዘብ ፣ ዛሬን በማከም ፣ ነገን በማበጃጀት ብቻ ነው ።

ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ለአንጾኪያ እና ለአንጾኪያ ቤተ ክርስቲያን ከአደረጋቸው በርካታ ውለታዎች ውስጥ አንዱ ደግሞ ፥ አንጾኪያውያን የትላንት ታሪካዊ ቁርሾን በመገነዛዘብ አንዲዘጉ ፣ ዛሬን እና ነጌን ማከም ማበጃጀት የሚያስችላቸውን አእምሯዊ ስሪት እና ስነ ስነ ልቦናዊ ውቅር ማምጣት መቻሉ ነበር።

" አእምሯዊ ስሪቱ እና ስነ ልቡናዊ ውቅሩ ታሪካዊ ቁርሾ በተሳከረ ትርክት የተቃኘ ትውልድ ፥ ሀገርን ያፈርሳል ፤ ማኅበረሰብ ያቃቅራል ፤ ብሎ የሚያምነው ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ዕድሜ ዘመኑን የአዋለው አእምሮን እና ስነ ልቡናን በመስራት በመገንባት ላይ ነበር ።


(ዲያቆን ታደሰ ወርቁ ጽዋዔ ገጽ 192)



https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
4.1K views✞£iŧsûm✞, 12:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-14 15:59:02 በቅርቡ  የብዙች ጥያቄ

እራሳቸውን መርጌታ ደብተራ ብለው
በመጥራት ትውልዱን የሴጣን ባርያ
በማድረግ በማሕበራዊ ሚዲያ በቴሌግራም በፌስቡክ ከክርስትና ሕይወት እና አስተምሕሮ ውጪ ሰማያዊውን ሕይወት በማጉደል የምድር ሙላትን ፈላጊዎችን በጥንቆላ በመተት  እንሞላላቹሀለን  እያሉ ብዙዎችን እያሳቱ ክርስቶስ ካስተማረው ሕይወት እያወጡ ይገኛሉ ።

በዚህ ዙራያ  መጽሐፍ ቅዱሳዊው አስተምሕሮ ምን ይመሳል ይፈቅዳል ? ካልተፈቀደስ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ሕይወት ውስጥ ለነበሩ የተሰጡትን ተግሳፃት  ትምሕርታዊ ፁሑፍ  ብታስተላልፍ ያለቹሁኝ  ምእመናን ። መምሕር ጠይቄ በዚህ ዙሪያ አስተማሪህ መካሪ ፁሐፍ ተዘጋጅቷል
በቅርቡ ይጠብቁኝ ።

                   
  የጥያቄውን የፁሑፍ መልስ ለቀረበለት ጥያቄ

       (መምሕር ዲያቆን ወሰንየለው በሐሩ)

                እንደፃፈው!!

ይዤላቹ መጣለሁ በቅርቡ ይጠብቁኝ ።



ዘማሪ ዲያቆን ፍፁም ከበደ
5.0K views✞£iŧsûm✞, edited  12:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-14 07:11:41

3.7K viewsማኔ ቴቄል ፋሪስ, 04:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-13 14:13:46  ብዙ ሰዎች እንዲህ ናቸው ደግ መስለው ከደጋግ ሰዎች የማይጠቀሙ። ለመዳን መስማት ብቻ በቂ አይደለም። “ቃሉን የሚሰማ የማያደርገውም ቢኖር የተፈጥሮ ፊቱን በመስተዋት የሚያይን ሰው ይመስላል”በእኛም ቤተ ክርስቲያን ድግስ ደጋሽ፤ እንግዳ ተቀባይ፤  ጉባኤ አዘጋጅ ሆነው ነገር ግን  አይቆርቡም ከክፋት አይመለሱም። ይቀድሳሉ እንጂ አይቀደሱም። 

ሔሮድስ የሚገስጸውን አስገደለ። ሰው እንዴት መካሪውን ይገድላል። ዛሬ ዜጎቻችንንን ንጹሐንን የሚገድሉ ወንበር ላይ ይቀመጡ እንጂ ሕሊናቸው እንደከሰሳቸው ነው።  ብዙ ጊዜ የሚገስጸንን  አንወድም በጠላትነት እንነሳበታለን። ቅዱስ ዮሐንስ ግን በክብር አረፈ አንገቱ እየዞረች አስተማረች።

የቅዱስ ዮሐንስ በረከት ምልጃ አይለየን

መ/ር ንዋይ ካሳሁን

https://t.me/akanim1wasen2
https://t.me/akanim1wasen2
4.7K viewsወሰንየለው ባህሩ, 11:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-13 14:13:46 ፍኖተ አበው ዘኦርቶዶክስ (መ/ር ንዋይ ካሳሁን):
“መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ”

ጢባርዮስ ቄሳር ከ 14 -37 ዓ.ም ድረስ የሮማ ንጉሥ ነገሥት ነበር። ጢባርዮስ ቄሳር የነገሠበት አስራ አምስተኛው ዓመት ወደ 28 ኛው ዓ.ም ላይ ቅዱስ ዮሐንስ አገልግሎቱን ጀመረ። 

ከአይሁድ ነቢያት ሁሉ በጣም ኃያሉ ነበር። “እውነት እላችኋለሁ፥ ከሴቶች ከተወለዱት መካከል ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ አልተነሣም፤ በመንግሥተ ሰማያት ግን ከሁሉ የሚያንሰው ይበልጠዋል ” ማቴ .11:11 ትኅትናው የተለየ ነው ። ራሱ ሲናገር "በኋላ የሚመጣውን መሲህ የጫማ ማሳሪያ እንኳ ልፈታ አይገባኝም" ይል ነበር። ባሪያዎች እንኳ የጌታቸውን ጫማ አይፈቱም ነበር። ባርያ የማይሰራውን ስራ እንኳ አልችልም አለ።

 ከሴቶች ከተወለዱ ሁሉ የሚበልጠው ዮሐንስ ግን የጌታችንን ጫማ ክር ለመፍታት የበቃሁ አይደለሁም አለ። ይህ ትኅትና ቀርቶ አንጥፍጣፊ አለን ይሆን። እኛ ሁሉን አዋቂ፡ ብዙ የምንበልጣቸው እንዳሉ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ አድራጊ ፈጣሪ እንደሆንን እናስብ የለ። 

እግዚአብሔር ለሰው ደኅንነት ወደ ዓለም መምጣቱ በብዙ ምሳሌዎች ተገልጧል። ከነዚኽም ጉልህ ሆኖ የሚታየው በዮሐንስ የደረሰው ነገር ነው። ዮሐንስ የካህን ልጅ ነው። ምንም የምድራዊ ክብር ያልፈለገ ሲሆን ቢፈልግ ኖሮ በሔሮድስ አንቲጳስ ከፍተኛ መፈለግ ነበረው።

 ዮሐንስ ቅዱስና ጻድቅ ስለነበረ ሔሮድስ ይፈራው ነበር። ክፉዎች ጥሩዎችን ይፈራሉ። እግዚአብሔርን የማይወዱ ሃይማኖትን ይጠላሉ። ምክንያታቸው ደግሞ ኅሊናቸው እንዲነካ አይፈልጉም። “ሄሮድስ ዮሐንስ ጻድቅና ቅዱስ ሰው እንደ ሆነ አውቆ ይፈራውና ይጠባበቀው ነበር፤ እርሱንም ሰምቶ በብዙ ነገር ያመነታ ነበር” ማር.6:20

የዮሐንስ  ስብከት ለአይሁዳውያን እንግዳ ነበር። ምክንያቱም ንሰሐ መግባት መጠመቅ  አለባችሁ ይል ነበር። አይሁዳውያን አሕዛብን ያጠምቁ ነበር እንጂ እነርሱ አይጠመቁም ነበረ። አስፈላጊ እንደሆነ አያምኑም ነበር። እግዚአብሔር ለራሱ የመረጣቸው የአብርሃም ወገኖች በመሆናቸው ራሳቸውን የሚመለከቱት እንደ ጻድቅ ነው። ነገር ግን የንሰሐ ፍሬ እንዲያፈሩ ነገራቸው። ዮሐንስ ለፈሪሳውያን ለሕዝቡ ለወታደሮች ማድረግ ያለባቸውን ነገራቸው።

 “ቀራጮችም ደግሞ ሊጠመቁ መጥተው፦ መምህር ሆይ፥ ምን እናድርግ? አሉት። ከታዘዘላችሁ አብልጣችሁ አትውሰዱ አላቸው። ጭፍሮችም ደግሞ፦ እኛ ደግሞ ምን እናድርግ? ብለው ይጠይቁት ነበር። እርሱም፦ በማንም ግፍ አትሥሩ ማንንም በሐሰት አትክሰሱ፥ ደመወዛችሁም ይብቃችሁ አላቸው ” ሉቃ.3:10

እንደ ሄሮድስ ያሉ ዓለማውያን፣ አዋቂዎች አልያ የተማሩ ሰዎች አዲስ ነገር ብቻ መስማት ይፈልጋሉ። ኑሮን የሚነካ ነገር ከተነሳ ሌላ ሐሳብ ወደ ልባቸው ይገባል።” አግሪጳም ፊስጦስን፦ ያንንስ ሰው እኔ ዳግም እኮ እሰማው ዘንድ እወድ ነበር አለው። እርሱም፦ ነገ ትሰማዋለህ አለው።”  ሐዋ.25:20

 ማንም ቢሆን የልቡን ሲነግሩት ቁስሉን ሲነኩት ማኩረፍ ይጀምራል። ተሰደብን፣ ተደፈርን ይላል። እግዚአብሔር ተናገረን የሚል ጥቂት የእግዚአብሔር ሰው ይኖራል።   ስለዚኽም ሔሮድስ ከዮሐንስ አድናቆት የሚፈጥረውን ስብከት መስማት ይፈልግ ነበር። ቅዱስ ዮሐንስ ግን ሌላውን ነገር ትቶ ወደ ሔሮድስ ሕሊና ዓላማ አድርጎ አስተማረ።

 የትምህርት ዓላማው ሰውን ማሳቅ ማስደሰት አይደለማ ። ወደ ሕሊና ጓዳ መግባት ይጠይቃል። ዛሬ ዛሬ ስብከቱም ትምህርቱም ሰው የሚወደውን ጊዜ የሚወልደውን ብቻ ሆኗል። እነ አንቶኔን ለማስደሰት አልያ መድረክ ላይ ለመሞጋገስ ብቻ ይመስላል። የሰውን ሕሊና ምንም ሳያገኙ ሲያስጨበጭቡ ያመሻሉ። 

ሔሮድስ በዮሐንስ ስብከት አልተደሰተም። ዮሐንስ በሔሮድስ መሞገስን ፈልጎ ቢሆን ኖሮ የወንድሙን ሚስት ማግባት ክፋት መሆኑን መናገር ባላስፈለገው ነበር። ነገር ግን ሥራው እግዚአብሔርን ማስደሰት ብቻ ስለነበር ለሔሮድስ ነፍስ አስቦ ገሰጸው። ስለዚህ ሳይፈራ እውነቱን ገለጸ። “ዮሐንስ፦ እርስዋ ለአንተ ትሆን ዘንድ አልተፈቀደም ይለው ነበርና ” ማቴ 14:4

ሔሮድያዳ ወዲያው የሔሮድስን ልብ  ይዛ ስለ ነበር  ወደ ወኅኒ አስጋዘችው። ዮሐንስ ታሰረ ቃሎቹ ግን አልታሰሩም ነበር። ድምጹ ዝም ቢል እንኳ በሕሊና ይናገራል።
ዮሐንስ ታስሮ ብዙ ወራት ቆየ። ከደቀ መዛሙርቱ ጠርቶ ሁለቱን ወደ ኢየሱስ ላካቸው። “ዮሐንስም ከደቀ መዛሙርቱ ሁለት ወደ እርሱ ጠርቶ። የሚመጣው አንተ ነህን ወይስ ሌላውን እንጠብቅ? ብሎ ወደ ኢየሱስ ላከ” በመሲሁ ላይ የነበረው እምነት ታላቅ ነበር። ደቀ መዛሙርቱ ፊት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የዮሐንስን ክብር በመግለጥ ተናገረ።

ዮሐንስ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ መስክሮ ነበር አሁን ደግሞ ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ዮሐንስ መሰከረ።   ጌታችንም ምን ልታዩ ወጣችሁ ብሎ ጠየቀ። የሕዝቡ ስህተት ለማየት ብቻ   መምጣት ነበር። ዛሬም በቤተ ክርስቲያንም የምናየው ከዚህ የተለየ አይደለም የሚታይ ተአምር፣ የሚለፈልፍ ጋኔን ለማየት ተኮልኩሎ ጸሐይ ሲመታው ይውላል። አዲስ ሰባኪ መጣ ሲሉት ግር ይላል። በማግስቱ የለም። በቃ ማየት ነው ፍላጎቱ።

እግዚአብሔርን ፈቃድ  ለማወቅ የመጡ እየመሰሉ የፈለጉትን ድንቅ ነገር ለማየት ብቻ ነበር። ለመስማት ሳይሆን ለማየት ሔዱ። ዮሐንስ በሕዝብ አሳብ አልሔደም ሳይፈራ ያስተምር ነበር። የምትከተለው እውነት ከሆነ የሰው ግርግር አያስደንቅህ። እንደ አብርሐም በመስመርህ ላይ ሰዎች ባይሔዱም አንተ ያመንከውን እውነት ብቻ ተከተል። ሰዎች ደጋፊ በሞላበት ማጨብጨብ ይሻሉ። 

ዮሐንስ በነገሥታት ቤት መኖር ሲችል ምድረበዳ ኖረ። ከነቢይ የሚበልጥ ነቢይ ነበር። የእርሱ ትልቅነት በሰማያዊ ደረጃው ነው። የርሱ ትልቁ ሥራው የእግዚአብሔርን በግ ለዓለም ማስታወቅ ነበር። 

ሔሮድስ ልደቱ ሲከበር መኳንንቶቹ ተሰበሰቡ ሔሮድያዳ በዘፈን አሰደሰተችው። የፈለገችውን እንደሚሰጣት ጠየቃት እናቷን አማከረች። ዮሐንስ የተናገረው አልተረሳትም እና እርሱን በማስገደል ሕሊናዋ የሚያርፍ መሰላት። “እርስዋም በእናትዋ ተመክራ፦ የመጥምቁን የዮሐንስን ራስ በዚኽ በወጭት ስጠኝ አለችው” ማቴ 14:8 ። ሰው የሚያርፈው የተጣላውን በመታረቅ የበደለውን በመካስ ወደ እውነት በመምጣት እንጂ ራሱን በማታለል እውነትን አርቆ ስለደበቃት አይደለም። 

የዮሐንስን አንገት ለመነች። ሔሮድስ የሰው ይሉኝታን ፈርቶ በመጠጥ ኃይል ተይዞ ዮሐንስን አስገደለው። የጌታን መንገድ አዘጋጅ ገደለ "ልኮም የዮሐንስን ራስ በወህኒ አስቆረጠው” ከዚያ በኋላ ሐሮድስ ፍርሐት አስጨነቀው። ሔሮድስ የጌታችንን ዝና ሲሰማ ዮሐንስ ከሞት ተነስቷል አለ። ነገር ግን ፈሪሳዊ ስለሆነ በሙታን ትንሳኤ አያምንም ነበር። ይሁን እንጂ ሕሊናውን ፈራ። ምክንያቱም ያስገደለው  ራሱ ነበር። እርሱን ለመበቀል የዮሐንስ መንፈስ ተመልሶ የመጣ መሰለው። 

በደለኝነት መንፈስ የተሞላ አዕምሮ የተለያዩ አላስፈላጊ ፍርሃቶች ይኖሩታል።” ኃጥእ ማንም ሳያሳድደው ይሸሻል፤ ጻድቅ ግን እንደ አንበሳ ያለ ፍርሃት ይኖራል”  ምሳ.28:1 ጌታችንንን ሊያየው ይመኝ ነበር። ነገር ግን ያየው በመጨረሻ ሰዓት ነው። ሊሰማው ቢወድ እንዳይገደል ቢፈልግም ላደረገው ክፋቱ ንሰሐም አልገባ፣ ከማስገደል አላመለጠም።
4.0K viewsወሰንየለው ባህሩ, 11:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-12 13:11:59
+ + + ማስታወቂያ + + +


በዲያቆን ታደሰ ወርቁ የተዘጋጀው “ጽዋዔ” የተሰኘው መጽሐፍ፥ መስከረም 8 ቀን 2015 ዓ.ም. በዕለተ እሑድ፣ ከቀኑ 7፡00 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ ካዛንችስ በሚገኘው ኢንተር ለግዠሪ (እንተርኮንቴኔታል) ሆቴል፥ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ ተጋባዥ ምሁራንና ታላለቅ እንግዶች በተገኙበት በድምቀት ይመረቃል፡፡ እርስዎም በዕለቱ በቦታው ተገኝተው በዚህ ታላቅ የመጽሐፍ ምረቃ መርሐ ግብር ላይ እንዲታደሙ በአክብሮት ጋብዘንዎታል፡፡

Share Share

https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
4.3K views✞£iŧsûm✞, 10:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-12 11:19:52
የጌታውን እናት የሰላምታ ድምጽ ሰምቶ በማኅጸን በደስታ የዘለለውን (የሰገደውን) ጽንስ፣ በንጉሡ ፊት በክፉት የደነሰችው ልጅ አንገቱን አስቆረጠችው።

ጽንሱ ስለ ሕይወት መምጣት በጠባቡ አዳራሽ በማኅጸን ሲያመሰግን፣ የሄሮድያዳ ልጅ ግን የነቢዩን ሕይወት ስለ ማስጠፋት በሰፊው የንጉሡ አዳራሽ ዘፈነች።

አዲሱ ዓመት የኢትዮጵያ ልጆች በሄሮድያዳ ምክር የማይሄዱበት፣ ከእግዚአብሔር ዘንድ የተማሩ ሆነው የሚያድጉበት በጎ ዘመን ያድርግልን!!!


ዲያቆን አቤል ካሳሁን

JOINE JOINE


https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
3.8K views✞£iŧsûm✞, 08:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-12 07:01:43 የዐውድ አመት ራስ ዮሐንስ

መስከረም-ሁለት

ዛሬም የየራሳቸውን ጽድቅ እያቆሙ ጻድቃን ነን የሚሉ ይህን ትምክህታቸውን ትተው ወደ ጻድቃን ጥበብ ወደ ኦርቶዶክስ ጥበብ ይመጡ ዘንድ በዮሐንስ አምላክ እንጠራቸዋለን ። ዮሐንስ ለዚህ ሁሉ አገናኝ የፍቅር ገመድ ሆኗል ርእሰ ዐውድ ዓመት ዮሐንስ መባሉ ለዚህ ነው ። መንፈስ ቅዱስ ቃኝቶት ፈቃዱን የሚሰራቸው አበው የዮሐንስ ዕረፍት መሰከረም ሁለት ቀን እንዲታሰብ አድርገዋል። ሙሉ ቀንም ያው የሚቆመው የማኅሌት ቃለ እግዚአብሔር ዮሐንስን የሚመለከት ነው ። ከእነዚህ "ርዕሰ ዐውደ ዓመት ዮሐንስ ወለዴ መጥቅዕ ወአበቅቴ " የሚለው ነው ። "አበቅቴንና መጥቅዕን የምትወልድ የዐውድ ዓመት ራስ ዮሐንስ " ማለት ነው ። ይህም ሶስት መሰረታዊ ትርጓሜያት አሉት፦

የመጀመሪያው የዐውድ ዓመት ራስ የሚለው ነው ። ዛፍ ያድግ ያድግና ጫፍ ላይ ፍሬን ይቋጥራል ። ዓመቱ የአመቱ መጨረሻ ላይ መስከረም አንድ ቀን እንደ ፍሬ ይቀመጣል። የዮሐንስም ትንቢት ነብያት ሲዘራ ኖሮ ዮሐንስ በነቢያት መጨረሻ እንደ ፍሬ ተቀምጧል ።


ሁለተኛ መስከረም አንድ ቀን የዓመቱ አጽዋማት በዓላትን የሚወጡበት የሚቀመሩበት አበቅቴን መጥቀዕ የሚወጡበት ዕለት ነው ። ዮሐንስም "ዕለት ኅሪት - የተወደደች የጌታ ቀን ዓመት " በምትባለው በዘመነ ሐዲስ ለሚደረገው የጽድቅ ስር ሁሉ አበጋዝ ፈት አውራሪ ወጣኒ መንገድ ጠራጊ ቃለ አዓዲ ነውና።


ሶስተኛው መስከረም አንድ ቀን ያለፈው ዓመትና የመጣው ዓመት የሚገናኝበት ድልድይ ነው። ዮሐንስም ትንቢተ ነቢያትን ስብከተ ሐዋርያትን መሀል ላይ ያገናኘ ነውና ርእሰ ዐውድ ዓመት ተባለ።



( ርዕሰ ሊቃውንት የኔታ አባ ገብረ ኪዳን    "ጸያሔ ፍኖት")


ዘማሪ ዲያቆን ፍፁም ከበደ


JOINE JOINE



https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
13.3K views✞£iŧsûm✞, edited  04:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-11 17:55:39
የማንቂያ ደውል በመምህር ምህረታብ አሰፋ የሚቀርብላችሁ የቴሌግራም ቻናል ነው ቻናሉን በዚ ያገኙታል።

@memihr_mhretab_assefa
@memihr_mhretab_assefa
@memihr_mhretab_assefa
88 views✞£iŧsûm✞, 14:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ