Get Mystery Box with random crypto!

ዘማሪ ዲ/ን ፍፁም ከበደ

የቴሌግራም ቻናል አርማ zdfitsumkebe — ዘማሪ ዲ/ን ፍፁም ከበደ
የቴሌግራም ቻናል አርማ zdfitsumkebe — ዘማሪ ዲ/ን ፍፁም ከበደ
የሰርጥ አድራሻ: @zdfitsumkebe
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 22.71K
የሰርጥ መግለጫ

ዘማሪ ዲያቆን ፍፁም ከበደ

Ratings & Reviews

5.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 24

2022-09-23 19:17:35
.

ለፕሮፋይል ፒክቸር የሚሆኑ መንፈሳዊ ፎቶዎችን ማግኘት ይፈልጋሉ መልሶት አዎ ከሆነ ከስር ያለውን ሊንክ በመጠቀም ማግኘት ይችላሉ


https://t.me/+YkS5xznutqNjZTE0
https://t.me/+YkS5xznutqNjZTE0
https://t.me/+YkS5xznutqNjZTE0
430 views🄴🄻🄰, 16:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-23 16:44:19 ሐዘኔ ሲፀና

Sound Recorde

ሐዘኔ ሲፃና እንባዬ አብሰሽ
በእናትነት ፍቅርሽ በመዳፍሽ ዳሰሽ
አፅናናሽኝ አይዞ አልሽኝ
ኪዳነ ምሕረት የሁሉ እመቤት

አዝ
ተስፍ ስቆርጥ በሚያልፈው ነገር
የጨበጥኩት ሲበትን ያክብር
ስለሰማው ድምፅሽን
ተጋጋሁ እኔ አሁን
መመኪያዬ የኔ ደስታ
አንቺን ይዤ አልረታ (2)


ዘማሪ ዲያቆን ፍፁም ከበደ

https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
1.2K views✞£iŧsûm✞, edited  13:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-22 21:42:30 Watch " ከአክራሪ እስልምና ወደ "ክርስትና"በእውነተኛ_ታሪክ_ላይ_የተመሰረተ ክፍል 5" on YouTube


1.2K viewsማኔ ቴቄል ፋሪስ, 18:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-22 16:48:38 በየመድረኩ ስላነጫነጩኝ ፯ ነገሮች፣ ፯ ጊዜ ጮኼ ቢወጣልኝ!

(በአማን ነጸረ )
--
፩. ሁሉን ነገር ምሥጢራዊ ማድረግ (Mystification /mystifying)፡- በቤተ ክርስቲያን ምሥጢራት የተቆጠሩ ናቸው፡፡ የምሥጢረት ጉዳይ ክፍት ቢሆን እንኳ ሊቀነን የሚችለው በሲኖዶስ ነው፡፡ ንባቡንም ቊጥሩንም ምሥጢር ለማድረግና የሰማዕያን ቀልብ መሸመቻ ለማድረግ መሞከር ግን ያውካል፡፡ በዛ!
፪. ባሕልን ሁሉ የመቀደስና ሃይማኖታዊ ካባ የማልበስ ሙከራ (religious syncretism)፡- ባሕል የሰው ልጆች መስተጋብር ውጤት ነውና በራሱ ርኩስ አይደለም፡፡ ሆኖም የሃይማኖትን ሥርዓትና ዶግማ ታሳቢ ያላደረገን አካሄድ ሁሉ በትርጓሜ የሃይማኖት ቀለም መስጠት አይመከርም፡፡ ክቡራን የብሔረሰብ ሊቃውንት አደብ ግዙልን፡፡ ምኞታችሁን ለማጽደቅ ጥቅስ፣ ንባብና አመክንዮ አታባክኑ!
፫. ሃይማኖትን ከአፈታሪክ (Mythology) ማቀላቀል፡- ምናብን ሃይማኖታዊ ቀለም ቀባብቶ የነገረ ሃይማኖትና ሥርዓት አካል አድርጎ ማቅረብ፡፡ ‹‹መጽሐፉ አይልም!›› ሲባል ‹ያልበራላቸው፣ ቅናት ያቃጠላቸው፣ ጎምላላው ግመል ላይ የሚጮኹ ውሾች› እድርጎ ማቅረብ፡፡ ቸከ!
፬. ታሪክን በዐርበኝነትን ስም መበዝበዝ (Exploitation of Patriotism):- ብዙኃኑ ሕዝብ ለሀገሩ ያለው ፍቅር ይታወቃል፡፡ ያንን የሀገር ፍቅር ሃይማኖትን ታክከው ታሪክን ወደ ቅዱስ መጽሐፍ ደረጃ በማሳደግ ጥያቄ የማይነሣበት ማድረግ፡፡ ሲነሣ ‹የፈረንጅ ተላላኪ፣ አእምሮውን የታጠበ› አድርጎ መሣል፡፡ ቅሬነት! የፈረንጆችን ተንኮል እንጸየፋለን ማለት የመንደሯን ቂልነት በምትክነት እንቀበላለን ማለት አይደለም፡፡ ሀገሩ የመጽሐፍ ነው! ኢትዮጵያ የመጽሐፍ ሀገር ናት! ድንገት ተገለጠልኝ ዓይነት አሳክሮና አሳብሮ መውጫዎች አይመስጡንም!
፭. የነገረ መናፍስት (Demonology) ተንታኙ ከመናፍስቱ ሊበልጥ ነው:- ካሴቱንም፣ ክሊፑንም፣ የቴሌቪዥን ድራማውንም ከመናፍስት እያያዙ በመተንተን ማስበርገግ የትምህርትም ሆነ የሃይማኖት መመዘኛ የማያስፈልገው በብላሽ የተገኘ ምሁርነት ሆኗል፡፡ ገና ለገና ዘፈንና ተያያዥ ተግባራት በሃይማኖት አይበረታቱም ተብሎ ያለከልካይ ወጣቶቹ ላይ የሚደረገው ስድና ልቅ መናፍስታዊ ዘመቻ ይዘገንናል፡፡ ይሉኝታ ጠፋ! በታላላቅ አበው ‹ጊዜ ይተርጕመው› እየተባለ የሚታለፈው የዮሐንስ ራእይ ማንም የሚዘነጥለው ሆነ፡፡ ለሕይወት የተጻፈው አቡቀለምሲስ (የዮሐንስ ራዕይ) ገና (የመጽሐፉ) ስሙ ሲጠራ ወደ ሕሊናው ‹አውሬው፣ 666፣ ዘንዶው፣ ሉሲፈር› የሚል ምናብ የሚመጣበት ደንጋጣ ትውልድ ለመፍጠር ውድድሩ ሌላ ነው፡፡ ጩልሌነቱን የቅዱስ መጽሐፍ ትርጓሜ አስመስሎ የሚያቀርብ ዐይነ በላ በዛ!
፮. በሆነው ሳይሆን የሚቃወመውን እምነት በእርሱ ምናብ ቀድሞ በይኖ (Presupposition) በከንቱ የሚታገል በዛ፡- ስለምኖርበት ሃይማኖት ላውራ (አውቄ ነው ሃይማኖት ያልኩት! ሃይማኖት ያድናል ብዬ ስለማምን! ቃሉ ቢነገርም ስለሚያስኬድ!)፡፡ እንደውም ተውኩት፡፡ ‹ኦርቶዶክስ እንዲህ ናት› የሚልን ሰው ከአባባሉ ተነሥቼ የየትኛው እምነት ተከታይ እንደሆነ የመገመት አቅሜ ከ90 በመቶ ሳይበልጥ የቀረ አይመስለኝም፡፡ ስለ የኢኦተቤክ ማን ምንን ዓይነት አሉታዊ ነገር ሊናገር እንደሚችል እስከመገመት ደርሻለሁ፡፡ Presupposition ልቅ ሆነ! በእርግጥ ፆሩ በቤታችንም አይጠፋ!
፯. የተጋነነ የምክንያት ጉም አፈነን፡- ብዙም አላብራራውም፡፡ በሕግ ቋንቋ proximate cause የምትባል ‹አማርኛ› አለች፡፡ ምክንያትና ውጤትን በአግባቡ አገናኝቶ መናገር፡፡ እዚህ ፥ በማራቀቅ ስም ዐውድ ትደፈጠጣለች!



https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
2.1K views✞£iŧsûm✞, 13:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-21 11:23:33
የሰው ነፍስ አፈጣጠር

አባ ጊዮርጊስ ስለ ሰው ነፍስ አፈጣጠር ሶስት መንገዶች እንዳሉ ነው የሚነግረን ። መንገዶቹ፦ (1) ንፍሐት፣ (2) መሰራትና (3) ተከፍሎ ሊባሉ ይችላሉ ። የአዳም ነፍስ አፈጣጠር "ንፍሐት" ነው ። የሔዋን አፈጣጠር ያለ እናት "በመሰራት" ሆኖ ነፍሷና አጥንቷ ከአዳም ተገኝቷል። የቃየል ስጋና ነፍስ ግን "በተከፍሎ" ነው ፤ እንደ አዳም መፈጠር ፣ እንደ ሔዋን መሰራት የለበትም ። በአባ ጊዮርጊስ አንደበት ፦ ".....የሕይወት እስትንፍስን መቀበል በእናታችን በሔዋን ተቋርጧል ፤ የአዳም [በአንድ ጊዜ] የሕይወት እስትንፍስን መቀበል [ለሁሉም] በቅቷልና ፤ በእጅ መሰራት ግን ተሰራች ትወልድ ዘንድ እናት የለቻትምና። በቃየል ግን በእጅ መሰራትም የሕይወትም እስትንፍስን ከእግዚአብሔር መቀበል ተቋርጧል። አባ ጊዮርጊስ ይህን መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሐቅ ያልተቀበሉ ሰዎችን ይዘልፍቸዋል ። ሆኖም በምሳሌ ላይ ክፍ ነገር ስላልተናገሩ አይረግማቸውም።

(ወልታ ፅድቅ በአማን ነጸረ)



ዘማሪ ዲያቆን ፍፁም ከበደ

https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
2.8K views✞£iŧsûm✞, 08:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-20 21:42:25
ስብሐት ሚዲያ

የተለያዩ ድንቅ ድንቅ መንፈሳዊ መጻሕፍትን የምንዳስስበት እንዲሁም የምንጠቁምበት መርሐግብር #በቅርብ_ቀን በስብሐት ሚዲያ የዩቲዩብ ቻናል ይጠብቁን!


https://www.youtube.com/channel/UCPr3bFoG3yZ0UowJMESuCIw?sub_confirmation=1 #SUBSCRIBE
2.6K viewsወሰንየለው ባህሩ, 18:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-20 14:47:35
አቡ-ራዒጢ ጠንከር ያለ ሐሳብ ያነሳል፦

እግዚአብሔር የሰው ልጆችን ሲፈጥር በሌሎች ፍጡራን በኩል ሳይሆን ራሱ በቀጥታ ነው የፈጠራቸው ፤ ይህም አዳም እና ልጆቹ እግዚአብሔርን በሚገባ 'ፈጣሪያችን ብለው በጥልቅ ፍቅር እንዲያመልኩት ምክንያት ሆኗል፤ ተፈጥሯቸው በተዘዋዋሪ ቢሆን አምልኳቸውም በተዘዋዋሪ ይሆን ነበርና ። ሰውን እስከ ሞት ካደረሰው ውድቀት ማዳንም ሁለተኛ እንደ መፍጠር ነው ፤ እግዚአብሔር ሰዎችን በቀጥታ ሳይሆን በመልእክተኛ በኩል አድኗቸው ቢሆን በዚህ አዳኝነቱ ላይ የሚመሰረተው የምስጋና አምልኳቸውም አዳኝ ለሆነው አምላክ ቀጥታ የሚቀርብ ሳይሆን በተዘዋዋሪ የሚቀርብ ይሆን ነበር ይላል። ክርስቲያኑ አቡ - ራዒጣ ።

(በረከት አዝመራው የልቦና ችሎት)


ዘማሪ ዲያቆን ፍፁም ከበደ

https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
2.9K views✞£iŧsûm✞, 11:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-20 09:02:42

2.1K viewsማኔ ቴቄል ፋሪስ, 06:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-19 04:36:58 ትንኝን በምግብ የሚያስብ እግዚአብሔር አሰበኝ

"ለክብሩ ቀንተህ ስትጣል  ምግብ አብስሎ እንደ እናት÷ገስጾ እና መክሮ እንደ አባት  የሚያኖርህ እግዚአብሔር ለችግሮችህ መፍትሔ የሚሆኑ ሰዎችን ይልክለሀል።"

ዳንኤል በአምልኮተ እግዚአብሔር ጸንቶ እና ተግቶ በመኖሩ የነገሥታቱን ድለላና ዛቻ ጥሎ ፈቃደ እግዚአብሔርን በመጠበቁ በባቢሎን ምድር በግበ አናብስት (በአናብስት ጉድጓድ) ተጥሎ ነበር። በዛው ወራት ዕንባቆብ ደግሞ ለአጫዶች ሁሉ ምግብ አብስሎ ምሳ ይዞ ሲሔድ የእግዚብሔር መልአክ ተገልጦ "ይህን አብስለህ የያዝከውን ምሳ በአናብስት ጉድጓድ ተጥሎ ላለው ለዳንኤል ውሰደለት እርሱ አሁን ባቢሎን ይገኛል የሚል መልእክት ነገረው"። ዕንባቆብም መልሶ "ወለባቢሎንኒ ኢይአምራ" ባቢሎንን አላቃትም ቢል መልአኩ  በጸጉሩ ይዞ አድርሶታል። ከዛም እንደ ደረሰ ያበሰለውን ምግብ በተዘጋ ግንብ ገብቶ ለዳንኤለ ሰጥቶ በተዘጋ ግንብ ወጥቷል። ዳንኤልም ይህን ሲመለከት "ትንኝን በምግብ የሚያስብ እግዚአብሔር አሰበኝ" ብሎ አመሰገነ።

እግዚአብሔር በእኛ የጀመረውን ዓላማ እስኪጨርስ ድረስ ለሚገጥሙን ስብራቶች ጠጋኞችን÷ለሚፈጠሩብን ጉድጓዶች ድልድይ የሚሆኑንን ይልክልናል። እንደ ዳንኤል ለእውነት ብለህ ስትቸገር ለሌላ የታሰበውን ሲሳይ ይዘውልህ የሚመጡ ድንገተኛ ዕንባቆቦችን ያዘጋጅለሀል። እውነት የሆነ ክርስቶስን ሰቅለው ቁማር ሲጫወቱ እንዳመሹት ሳይሆን የመስቀሉን እውነት አስበው መከራ ከሚቀበሉት ወገን ለመቆጠር ቁርጠኛ ለመሆን ከተጋህ ሰዎች በማይደርሱበት ዱር ላይ ብትሆን እንኳን መፍትሔ ሊሆንህ የሚችል መውጫን ያዘጋጅልሀል።

ዳንኤል በምድር ገዢዎች ፊት ጥፋተኛ የሰማይና የምድር ገዢ በሆነው በእግዚአብሔር ዘንድ ግን እውነተኛ ሆኖ በመገኘቱ በመከራው ጊዜ ይተወው ዘንድ አልወደድም። በእግዚአብሔር  ዘንድ ትክክለኛ መሆንህን ሳታውቅ በሰዎች ዘንድ ትክክለኝነትህን ለማረጋገጥ ስትጥር የእድሜህ ማገባደጃ ላይ ትደርሳለህ። ብዙ ሰዎችን የገዛ ሐሳብ በእግዚአብሔር ዘንድ ግን ዋጋ አልባ ሊሆን ይችላል። ስለዚህ ቀላሉ መፍትሔ በእግዚአብሔር ሕግጋት ውስጥ ተመላልሰህ በእርሱ ፊት ትክክለኛ ለመሆን መድከም ነው። ያኔ ለሚደርሰብሕ መከራ መውጫውንም ያዘጋጅለሀል። መውጫውን ባያበጅልህ እንኳን ከሞት በኋላ ባለው ሕይወት አክሊልን ያቀዳጅሀል።

በናታን በኩል ዳዊትን ከኃጢአት የመለሰ እግዚአብሔር በኃጢአት ማዕበል እንዳንወሰድ የሚመልሱን ደጋጎቹን እንደሚልክ በዕንባቆብም በኩል የዳንኤልን ረኅብ እንዳስታገሰ ለሥጋዊ ሕይወታችን ረብ የሚሆኑትን ይልካል።

እግዚአብሔር ለሥጋችንም ለነፍሳችንም ያስባል።

ዲ/ን ሞገስ አብረሃም


https://t.me/akanim1wasen2
3.3K viewsወሰንየለው ባህሩ, 01:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-17 17:33:37    ተለቀቀ

የሞት መንገድ


ይሄን ርዕስ ለማንሳት ምክንያት የሆነን ዛሬ በዘመናችን ወደ ሞት ጎዳና የሚወስዱንና ፍጻሜያቸው ሞት የሆነውን፥ ብዙዎችን በሠይጣን አሰራር ውስጥ የከተተ፥ ብዙዎችን የሠይጣን ባርያ አድርጎ እና የእግሩ መረገጫ እንዲሆኑ ምክንያት የሆነውን የእርኩሳን መናፍስት አሠራር ለማጋለጥ ስለወደድን ነው። ይሄውም ጥንቆላ ወይም አስማት ይባላል። ዛሬ በዘመናችን በተለያየ መንገድ ትውልዱን ከሰይጣን ጋር የማቆራኘት ተግባራት እየተመለከትን ነው።

ሠይጣን የኔ በሚላቸው ሰዎች አማካኝነት በክርስቶስ ክርስቲያን የተባሉ እና ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ ከማኅጸነ ዮርዳኖስ የተወለዱትን ሳይቀር ለራሱ ባርያ እያደረገ በተለያየ ዘመኑን በዋጀ መንገድ መጥቷል። በተለይም እራሳቸውን "መሪጌታ" "ደብተራ" እና ሌላም መጠሪያ ስም እየጠሩ በቴሌግራም እና በፌስቡክ እንዲሁም በሌላ ማኅበራዊ ሚድያዎችን በመጠቀም ለራሳቸው ገንዘብን ለሰይጣን የክርስቶስ አካል የሆነውን ምእመን ሲገብሩ እና ሲያስገብሩ ይባስ ብለውም ሲያጭበረብሩ በተደጋጋሚ እናስተውላለን።

በዘመናችን ለዘመኑ ትውልድ እንዲመጥን ተደርጎ እየቀረበ ያለው የእርኩሰት አሰራር የሆነው ጥንቆላ እና አስማት በቤተክርስቲያንም ሆነ በመጽሐፍ ቅዱስ የተወገዘ እና በእግዚአብሔር ዘንድም የተጠላ የሞትና የጭለማ መንገድ ነው። ዲያቢሎስን የሚከተል ማንኛውም አካል ፍጻሜው ጭለማና ሞት እንደሆነ ይታወቃል።


የጥንቆላ ተግባርን ዛሬ የተጀመረ አይደለም ።


ጥንቆላ(ጠንቋዮች) በተለያየ መንገዶች የሚጠነቁሉ እግዚአብሔር ባልፈቀደው መንገድ ኃይልን፥ ሥልጣንን፥ ድኅነትን እና ፈውስን ሀብትና ነብረትን ሞገስና ክብርን በመፈለግ የሚሠራ ተግባር ነው።የጥንቆላ ተግባር ዛሬ በዘመናችን የጀመረ ሳይሆን  ከጥንት ጀምሮ የነበረ ተግባር ነው። እንዲሁም ለነገሥታት አማካሪ የነበሩ ጠንቋዮች ነበሩ። (ዘጸ 7፥8 - 12, ኢሳ 19 ፥ 3, ዳን 2፥2)
ጥንቆላ በእስራኤላውያን ዘንድ በተለይም በከነኣን ምድር ምዋርተኛ፥ ሞራ ገላጭ፥ አስማተኛ፥ መተተኛ፥ በድግምት የሚጠነቁሉ መናፍስት ጠሪዎች ሙታን ሳቢዎች ነበሩ። እነዚህ ተግባራት የተለያዩ የእርኩሳን መናፍስትን ህቡእ ስሞችን በመጥራት፥ እንስሳትን በመሰዋት እና በሌሎች አስከፊ ተግባራት ከሠይጣን ጋር ቃል ኪዳን ያላቸው ሌሎችንም የቃል ኪዳኑ ተካፋይ በማድረግ የሰይጣን ባርያ የሚያደርጉ ናቸው።

✞ የችግራችን መፍትሄ ማን ነው ።

መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚነግረን ከሆነ ለየትኛውም ችግራችን እና መከራችን ሰይጣን መፍትሔ መሆን እንደማይችል፥ ጠንቋዮች እና ሟርተኞች አማራጭ ሊሆኑን እንደማይገባ አማራጫችንና ምርጫችን እጣ ፈንታችን እግዚአብሔር ብቻ እንደሆነ ይነግረናል። "እንዲሁ ሳኦል በእግዚአብሔር ላይ ስላደረገው ኃጢአት የእግዚአብሔርንም ቃል ስላልጠበቀ ሞተ። ደግሞም መናፍስት ጠሪ ስለጠየቀ እግዚአብሔርንም ስላልጠየቀ ስለዚህ ገደለው።"(1ዜና 10፥ 13) ስለዚህ የመናፍስት ጠሪዎችን መስማት አስማተኞችን እና ጠንቋዮችን መጠየቀ እንደ ሳኦል ከእግዚአብሔር ተለይተን የሞት ተገዥዎች ሆነን በሞት ጥላ ስር የሚጥለን የሞት መንገድ ነው። ስለሁሉም ነገር መፍትሔዎ የሚገኘው ከእግዚአብሔር እና የእርሱ ከሆኑት ከቅዱሳኑ እጅ እና ደጅ ስለሆነ ሁልጊዜ እግዚአብሔር በጾም በጸሎት ደጅ መጥናት መጠየቅ ይገባል እንጂ ከሕይወት ጎዳና ለይቶ ወደ ሞት የሚወስደውን የዲያቢሎስን መንገድ መከተል አይገባም።


ማንኛውም ክርስትያን እራሱ ከእግዚአብሔር ከሚለዩት ነገሮች ፈጽሞ መራቅ አለበት መልካቸውን ቀይረው በዘመናዊ መልክ ማስታወቂያ እያስነገሩ በስመ ደብተራና የባሕል መድኃኒት ቀማሚ እራሳቸውን ሸፍነው የሰይጣንን እቅድ የሚተገብሩ የሰይጣን ሰራተኞቹ እራሳችን ልንጠብቅ ልናድን ይገባል።

✞ እናስተውል ✞

እነዚህ አስማተኞች በእግዚአብሔር የማያምንኑ ነገር ግን "ደብተራ" በሚል ስም የሚነግዱ የሰይጣን ተላላኪዎች ናቸው። በእግዚአብሔር የሚያምኑ ቢሆን ኖሮ በሐዋርያት ሥራ 19 ፥ 19 እንደምናገኛቸው በቀድሞ ሕይወታቸው ጠንቋዮች የነበሩ ካመኑ በኋላ ግን ያን ክፉ የጥንቆላ ሥራ የሚሰሩበት የነበረውን መጽሐፋቸውን ያቃጥሉት ነበር። "ከአስማተኞችም ብዙዎቹ መጽሐፋቸውን ሰብስበው በሰው ሁሉ ፊት አቃጠሉት፤ ዋጋውም ቢታሰብ አምሳ ሺህ ብር ሆኖ ተገኘ።"

ከእግዚአብሔር መንግስት የሚለይ ተግባር ።

መጠንቆልና ማስጠንቆል ከእግዚአብሔር መንግሥት የሚለይ ተግባር መሆኑን መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይነግረናል። ሐዋርያው በገላትያ መልእክት 5፥20 ላይ ከዘረዘራቸው የሥጋ ሥራዎች መካከል የተዘረዘሩት መዋርት አንዱ የጥንቆላ መንገድ ነው። የሥጋ ሥራ የሆነውን መዋርትን የሚያደርግ መንፈሳዊ የሆነችውን የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርስም።

እንዲሁም ባለራእዩ ቅዱስ ዮሐንስ አስማተኞች እና ጠንቋዮች ከእግዚአብሔር መንግሥት ውጪ እንዳሉ በራእይ ተመልክቶ ሲነግረን እንዲህ ይላል  "ውሻዎችና አስማተኞች ሴሰኛዎችም ነፍሰ ገዳዮችም ጣዖትንም የሚያመልኩት ውሸትንም የሚወዱና የሚያደርጉ ሁሉ በውጭ አሉ።" (ራእይ 22 : 15)
እንዲሁም እንዲህ ያሉ ሰዎች በሕይወታችን በጉዟችን ከእኛ መካከል እንዳይኖሩ እግዚአብሔር ሲናገር እንዲህ ይላል "ወንድ ልጁን ሴት ልጁን በእሳት የሚያሳልፍ፥ ምዋርተኛም፥ ሞራ ገላጭም፥  አስማተኛም፥ መተተኛም፥ በድግምት የሚጠነቍልም፥ መናፍስትንም የሚጠራ፥ ጠንቋይም፥ ሙታን ሳቢም በአንተ ዘንድ አይገኝ። ይህንም የሚያደርግ ሁሉ በእግዚአብሔር ፊት የተጠላ ነው፤ ስለዚህም ርኵሰት አምላክህ እግዚአብሔር ከፊትህ ያሳድዳቸዋል።" (ዘዳግም 18 : 10 -12)

እንዲሁም አምላካችን ልዑል እግዚአብሔር እንዲህ ባለ የሰይጣን ሥራ ውስጥ እንዳንሳተፍ ስያዘን "አስማት አትሥሩ" (ዘሌ 19፥26) ይለናል። ስለዚህ እኛም ከእንዲህ አይነቱ አሰራር እራሳችንን ልናርቅ የገባንም በንስሐ እራሳችን ልናድስ እና ወደ እግዚአብሔር መንገድ ወደ ሕይወት መንገድ ልንመለስ ይገባል። ዛሬ በዘመናችን እኛን መስለው ብዙዎች ትውልዱን የሰይጣን ባርያና ተገዢ እንጂሆን በማድረግ ለኪሳቸው ገንዘብ የሚሰበስቡ የጥልቁ መንፈስ አገልጋዮች በቴሌግራም እና በፌስቡክ ብዙዎችን እያታለሉ ይገኛል። ከእንደዚህ አይነቱ የሰይጣን አሰራር ርቀን በአንዱ በእግዚአብሔር ብቻ እና ብቻ ልናምን እና ልንታመን ይገባል። እንዲሁም መጽሐፈ ፈውስ፥ መፍትሔ ሥራይ እና ሌሎች ጠርተን የማንጨርሳቸው በርካታ የጥንቆላ መጽሐፍት በማሳተም ሠይጣናዊ አሰራርን የሚያስፋፉ ትውልዱን የሰይጣን ተላላኪ የሚያደርጉ ለሚመጣው የአውሬው መንፈስ መንገድ ጠራጊዎች በሊቃውንት እና በደብተራ ስም የጥልቁን መንፈስ የሚያታልሉ፥ ከቤተክርስቲያን እና ከእግዚአብሔር ጋር የተጣሉ፥ የማያምኑ የሰይጣን ባርያዎችን ልናውቅባቸው እና ልንጠነቀቅ እራሳችንን እና በዙርያችን ያሉትን ልናድናቸው ልንጠብቃቸው ይገባል። ምክንያቱም መንገዱ የሞት መንገድ ነውና።

"ሰው ወይም ሴት መናፍስትን ቢጠሩ ወይም ጠንቋዮች ቢሆኑ ፈጽመው ይገደሉ፤ በድንጋይ ይውገሩአቸው፤ ደማቸው በላያቸው ነው።" (ዘሌ 20 : 27)


(መምሕር ዲያቆን ወሰን የለው በሃሩ )


SARE SARE

https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
3.9K views✞£iŧsûm✞, edited  14:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ